Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ግዕዝ ለምን?
~
ግዕዝን የማስተማር አስፈላጊነቱ ምንድነው? በተደጋጋሚ የሚነሱ ማሳመኛ ነጥቦችን እንመልከት (ከአንድ ፖስት ላይ የወሰድኳቸው ናቸው)።
1/ "አብዝሃኞቹ በብራና ላይ የተፃፉ የኢትዮጲያ ሃገር በቀል የሆኑ እውቀቶች የተሰናዱባቸው ድርሳናት የተፃፉት በግእዝ ቋንቋ ነው።"
መልስ፦
ሀ - ሃገር በቀል የሆኑ እውቀቶች ምንድን ናቸው? በግዕዝ ድርሳናት ውስጥ ብቻ የሚገኙ ህዝብ የማያውቃቸው ሃገር በቀል እውቀቶች አሉ? እና እስከዛሬ ለምን ዝም አላችሁ? እውነቱን ለመናገር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ህፃናትን ለማዘጋጀት የሚጠይቁ ያልተጠኑ የግዕዝ ድርሳናት የሉም።
ለ - የምትሉት እውነት ከሆነ ይህንን የመመራመር እና ህያው ወደሆነ ቋንቋ የመተርጎሙ ኃላፊነት የምሁራን እንጂ የህፃናት አይደለም። በከፍተኛ ተቋማት የሚሰራ እንጂ ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የሚሰጥ አይደለም። ስለዚህ እነዚህን ህፃናትን እንዲያስተምሩ ከየገዳማቱ ልታመጧቸው የምታስቧቸውን ቄሶችና ዲያቆናት የጥናት አሰራር ስልጠና ስጧቸውና እዚያው ጨርሱ።
2/ "alternative medicines የሚባሉት የኢትዮጲያ ባህላዊ ህክምና የተመሠጠረባቸው የብራና ሰነዶችና ድርሳናት የተፃፉት በግእዝ ነው።"
መልስ፦
ሀ - ይህም ውሸት ነው። ግዕዙ ላይ ዋጋ ያለው የህክምና እውቀት ቢኖር መሪጌታዎች በድግምትና መተት ማስታወቂያ ባላጥለቀለቁን ነበር።
ለ - እውነት ነው ቢባል እንኳ ይህንን የማጥናት ኃላፊነቱ የህፃናት ሳይሆን የጤና ጥበቃ ሚንስቴር ነው።
3/ "በብራና ላይ ተፅፈው የተቀመጡ ሃገር በቀል የስነ ህዋና የስነ ፈለክ ወርጅናሌ ሃሳቦች የተፃፉት በግእዝ ነው።"
መልስ፦
ኧረ እየታፈረ! በዚህ ዘመን እንዲህ ዓይነት ህፃናት የሚያሳምን ውሸት መዋሸት ለምን? ሳይንሳዊ ውጤቶች ካሉ ለምን እስከዛሬ ደበቃችኋቸው? እውነትስ ቢሆን ይህንን የማጥናት ኃላፊነቱ የህፃናት ሳይሆን የኢትዮጵያ የህዋ ሳይንስ ማዕከልኮ ነው።
4/ በእንግሊዝና በአሜሪካ ሙዚየሞች ውስጥ ከኢትዮጲያ ተዘርፈው የተወሰዱ ( በተለይ ከመቅደላ የተዘረፉት) ለቁጥር የሚታክቱ የብራና ላይ መፅሃፍት የተፃፉት በግእዝ ነው ፤
መልስ፦
ለቁጥር የሚታክቱ? ይህም ውሸት ነው። ቢኖር እንኳ ከገድላትና ዜና መዋዕል አይዘልም። ጥቂት ከተገኘ አንድ ተቋም ጥናቱን ለጨርሰው ይችላል።
5/ "ለዘመናዊ ቴክኖሎጂ መነሻ የሆኑ አንዳንድ እሳቤዎች ከኢትዮጲያ የግእዙ የስነ ቁጥር (mathematics) ፅንሰ ሃሳብ እንደተወሰዱ ይነገራል። "
በግዕዝ የተደበቀ ህክምና፣ ህዋ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ የምትሉትን ቀልድ ተውት። የማይካደው ነገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሃገር ምስረታ ላይ፣ የፅህፈት ስራን በማዳበር ላይ (መነሻው ከኦርቶዶክስ በፊት ቢሆንም) ትልቅ አስተዋጽዖ አላት። ይህንን መካድ አይቻልም። ታሪክ ግን ታሪክ ነው። ሙገሳ ሙገሳውን እየመረጡ መውሰድ አይቻልም። በሃገሪቱ ታሪክ ላይ ጉልህ ሚና ያላት ተቋም አዎንታዊ ነጥቦችን ብቻ እየመረጡ ማስተጋባት ሐቀኛ የታሪክ አዘጋገብ አይደለም። ስለዚህ ለሃገሪቱ ኋላቀርነት፣ ህዝቦች ላይ ለደረሱ ጭቆናና ብዝበዛ፣ ለደረሱ ውድመቶችና ፍጅቶች ድርሻ እንዳላት ማመን ይገባል። ታሪክ ጣፈጠም መረረ እውነተኛ ክስተቶችን የምንዘግብበት እንጂ እንደ ብፌ ደስ ያሰኘንን እየመረጥን የምናነሳበት አይደለም።
እቅጩን ስንነጋገር ግዕዝን ማስተማር ምንም ዓይነት የህክምናም የቴክኖሎጂም የሌላ ዘመናዊ ስልጣኔ እድገትም ሆነ የተደበቀ እውቀት አያመጣም። የህዝብ ለህዝብ ትስስርም አይጨምርም። የሃገርን ሃብት ምንም እሴት በማይጨምር ነገር ከማባከን ዉጭ ለኢኮኖሚ እድገት ምንም አይነት አስተዋፅዖ የለውም። ሌላው ቀርቶ የረባ ሃይማኖታዊ ትርፍም አያመጣም። ይልቁንም ነፍጥ ያነሱ ተዋጊዎችን ልባቸውን ለማማለል ይውል ካልሆነ በስተቀር እንዲህ አይነት የጉልበት ፖሊሲ ጥላቻ ነው የሚያመጣው። ይልቁንም ላይሳካ ነገር እንዲህ አይነት የረባ ዋጋ የሌለው ቋንቋ ለመመለስ አጉል ከመዳከር የሃገር ውስጥ ቋንቋዎችን ወይም ለሚሰደዱ ዜጎቻችን የሚጠቅሙ የውጭ ቋንቋዎችን ማስተማር ነው የሚሻለው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ግዕዝን የማስተማር አስፈላጊነቱ ምንድነው? በተደጋጋሚ የሚነሱ ማሳመኛ ነጥቦችን እንመልከት (ከአንድ ፖስት ላይ የወሰድኳቸው ናቸው)።
1/ "አብዝሃኞቹ በብራና ላይ የተፃፉ የኢትዮጲያ ሃገር በቀል የሆኑ እውቀቶች የተሰናዱባቸው ድርሳናት የተፃፉት በግእዝ ቋንቋ ነው።"
መልስ፦
ሀ - ሃገር በቀል የሆኑ እውቀቶች ምንድን ናቸው? በግዕዝ ድርሳናት ውስጥ ብቻ የሚገኙ ህዝብ የማያውቃቸው ሃገር በቀል እውቀቶች አሉ? እና እስከዛሬ ለምን ዝም አላችሁ? እውነቱን ለመናገር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ህፃናትን ለማዘጋጀት የሚጠይቁ ያልተጠኑ የግዕዝ ድርሳናት የሉም።
ለ - የምትሉት እውነት ከሆነ ይህንን የመመራመር እና ህያው ወደሆነ ቋንቋ የመተርጎሙ ኃላፊነት የምሁራን እንጂ የህፃናት አይደለም። በከፍተኛ ተቋማት የሚሰራ እንጂ ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የሚሰጥ አይደለም። ስለዚህ እነዚህን ህፃናትን እንዲያስተምሩ ከየገዳማቱ ልታመጧቸው የምታስቧቸውን ቄሶችና ዲያቆናት የጥናት አሰራር ስልጠና ስጧቸውና እዚያው ጨርሱ።
2/ "alternative medicines የሚባሉት የኢትዮጲያ ባህላዊ ህክምና የተመሠጠረባቸው የብራና ሰነዶችና ድርሳናት የተፃፉት በግእዝ ነው።"
መልስ፦
ሀ - ይህም ውሸት ነው። ግዕዙ ላይ ዋጋ ያለው የህክምና እውቀት ቢኖር መሪጌታዎች በድግምትና መተት ማስታወቂያ ባላጥለቀለቁን ነበር።
ለ - እውነት ነው ቢባል እንኳ ይህንን የማጥናት ኃላፊነቱ የህፃናት ሳይሆን የጤና ጥበቃ ሚንስቴር ነው።
3/ "በብራና ላይ ተፅፈው የተቀመጡ ሃገር በቀል የስነ ህዋና የስነ ፈለክ ወርጅናሌ ሃሳቦች የተፃፉት በግእዝ ነው።"
መልስ፦
ኧረ እየታፈረ! በዚህ ዘመን እንዲህ ዓይነት ህፃናት የሚያሳምን ውሸት መዋሸት ለምን? ሳይንሳዊ ውጤቶች ካሉ ለምን እስከዛሬ ደበቃችኋቸው? እውነትስ ቢሆን ይህንን የማጥናት ኃላፊነቱ የህፃናት ሳይሆን የኢትዮጵያ የህዋ ሳይንስ ማዕከልኮ ነው።
4/ በእንግሊዝና በአሜሪካ ሙዚየሞች ውስጥ ከኢትዮጲያ ተዘርፈው የተወሰዱ ( በተለይ ከመቅደላ የተዘረፉት) ለቁጥር የሚታክቱ የብራና ላይ መፅሃፍት የተፃፉት በግእዝ ነው ፤
መልስ፦
ለቁጥር የሚታክቱ? ይህም ውሸት ነው። ቢኖር እንኳ ከገድላትና ዜና መዋዕል አይዘልም። ጥቂት ከተገኘ አንድ ተቋም ጥናቱን ለጨርሰው ይችላል።
5/ "ለዘመናዊ ቴክኖሎጂ መነሻ የሆኑ አንዳንድ እሳቤዎች ከኢትዮጲያ የግእዙ የስነ ቁጥር (mathematics) ፅንሰ ሃሳብ እንደተወሰዱ ይነገራል። "
በግዕዝ የተደበቀ ህክምና፣ ህዋ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ የምትሉትን ቀልድ ተውት። የማይካደው ነገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሃገር ምስረታ ላይ፣ የፅህፈት ስራን በማዳበር ላይ (መነሻው ከኦርቶዶክስ በፊት ቢሆንም) ትልቅ አስተዋጽዖ አላት። ይህንን መካድ አይቻልም። ታሪክ ግን ታሪክ ነው። ሙገሳ ሙገሳውን እየመረጡ መውሰድ አይቻልም። በሃገሪቱ ታሪክ ላይ ጉልህ ሚና ያላት ተቋም አዎንታዊ ነጥቦችን ብቻ እየመረጡ ማስተጋባት ሐቀኛ የታሪክ አዘጋገብ አይደለም። ስለዚህ ለሃገሪቱ ኋላቀርነት፣ ህዝቦች ላይ ለደረሱ ጭቆናና ብዝበዛ፣ ለደረሱ ውድመቶችና ፍጅቶች ድርሻ እንዳላት ማመን ይገባል። ታሪክ ጣፈጠም መረረ እውነተኛ ክስተቶችን የምንዘግብበት እንጂ እንደ ብፌ ደስ ያሰኘንን እየመረጥን የምናነሳበት አይደለም።
እቅጩን ስንነጋገር ግዕዝን ማስተማር ምንም ዓይነት የህክምናም የቴክኖሎጂም የሌላ ዘመናዊ ስልጣኔ እድገትም ሆነ የተደበቀ እውቀት አያመጣም። የህዝብ ለህዝብ ትስስርም አይጨምርም። የሃገርን ሃብት ምንም እሴት በማይጨምር ነገር ከማባከን ዉጭ ለኢኮኖሚ እድገት ምንም አይነት አስተዋፅዖ የለውም። ሌላው ቀርቶ የረባ ሃይማኖታዊ ትርፍም አያመጣም። ይልቁንም ነፍጥ ያነሱ ተዋጊዎችን ልባቸውን ለማማለል ይውል ካልሆነ በስተቀር እንዲህ አይነት የጉልበት ፖሊሲ ጥላቻ ነው የሚያመጣው። ይልቁንም ላይሳካ ነገር እንዲህ አይነት የረባ ዋጋ የሌለው ቋንቋ ለመመለስ አጉል ከመዳከር የሃገር ውስጥ ቋንቋዎችን ወይም ለሚሰደዱ ዜጎቻችን የሚጠቅሙ የውጭ ቋንቋዎችን ማስተማር ነው የሚሻለው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
إنَّ اللَّهَ يَغَارُ، وإنَّ المُؤْمِنَ يَغَارُ، وَغَيْرَةُ اللهِ أَنْ يَأْتِيَ المُؤْمِنُ ما حَرَّمَ عليه
"አላህ ይቀናል። አማኝም ይቀናል። የአላህ ቅናቱ አማኝ የሆነ ሰው ሐራም የተደረገበትን ነገር መፈፀሙ ነው።"
[አልቡኻሪ፡ 5223] [ሙስሊም፡ 2761]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
إنَّ اللَّهَ يَغَارُ، وإنَّ المُؤْمِنَ يَغَارُ، وَغَيْرَةُ اللهِ أَنْ يَأْتِيَ المُؤْمِنُ ما حَرَّمَ عليه
"አላህ ይቀናል። አማኝም ይቀናል። የአላህ ቅናቱ አማኝ የሆነ ሰው ሐራም የተደረገበትን ነገር መፈፀሙ ነው።"
[አልቡኻሪ፡ 5223] [ሙስሊም፡ 2761]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
ጭፈራ የነገሰበት የሱፍያ እምነት ከክርስትና ጋር ብዙ የሚመሳሰልበት ነገር አለው።
1⃣ ሁለቱም በምልጃ ስም በ "ቅዱሳን" ላይ ወሰን በማለፍ ፍጡር እየተማፀኑ በፈጣሪ ሐቅ ላይ ሺርክን (ማጋራትን፣ ባእድ አምልኮን) ይፈፅማሉ።
2⃣ ሁለቱም ጭፈራና መዝሙርን እንደ አምልኮ በመቁጠር በቤተ እምነቶች ውስጥ ይጨፍራሉ።
3⃣ ሁለቱም በየ ሃገራቸው የሚገኙ አጉል ባህላትን እምነታዊ ሽፋን በመስጠት ሃይማኖትን ያጠለሻሉ።
4⃣ ሁለቱም ገና ወይም መውሊድ ያከብራሉ።
5⃣ ሁለቱም ከመፅሀፋዊ ማስረጃ ይልቅ
ሸይኾቻቸውን / ቄሶቻቸውን በጭፍን ይከተላሉ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
1⃣ ሁለቱም በምልጃ ስም በ "ቅዱሳን" ላይ ወሰን በማለፍ ፍጡር እየተማፀኑ በፈጣሪ ሐቅ ላይ ሺርክን (ማጋራትን፣ ባእድ አምልኮን) ይፈፅማሉ።
2⃣ ሁለቱም ጭፈራና መዝሙርን እንደ አምልኮ በመቁጠር በቤተ እምነቶች ውስጥ ይጨፍራሉ።
3⃣ ሁለቱም በየ ሃገራቸው የሚገኙ አጉል ባህላትን እምነታዊ ሽፋን በመስጠት ሃይማኖትን ያጠለሻሉ።
4⃣ ሁለቱም ገና ወይም መውሊድ ያከብራሉ።
5⃣ ሁለቱም ከመፅሀፋዊ ማስረጃ ይልቅ
ሸይኾቻቸውን / ቄሶቻቸውን በጭፍን ይከተላሉ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
"ኑሩን ከኑሩ ኸለቀው ጀሊሉ"
~
ይሄ ንግግር ሱፊዮች አካባቢ ተደጋግሞ የሚሰማ ነው። ምን ማለታቸው ነው?
* "ኑሩን" ሲሉ ነብዩን ﷺ ማለታቸው ነው።
* "ጀሊሉ" ሲሉ አላህ ማለታቸው ነው።
* "ከኑሩ" ሲሉ ከአላህ ኑር ማለታቸው ነው።
* ኸለቀው = ፈጠረው
ጥቅል መልእክቱ:-
አላህ ነብዩን ﷺ ከራሱ ኑር (ብርሃን) ነው የፈጠራቸው እያሉ ነው።
አንዳንዶቹ ይህንን መነሻ በማድረግ በግልፅ ነብዩ ﷺ የአላህ ክፍል (ጁዝእ/ part) ናቸው ብለዋል። ይሄ መሰረተ-የለሽ እምነት ነው። ለዚህም በተለያዩ ነጥቦች ምላሽ መስጠት ይቻላል።
1- ነብዩ ﷺ ምንም አይነት መለኮታዊ ድርሻ የላቸውም። ፍጡር ናቸው። ባሪያ ናቸው። ባሪያ ደግሞ የአላህ ክፍል ሊሆን አይችልም። መልእክተኛ ናቸው።
2- ነብዩ ﷺ ከኑር (ከብርሃን) ነው የተፈጠሩት የሚሉ አካላት መሰረተ ቢስ ወሬ እንጂ አንድም የቁርኣንም ይሁን የሐዲሥ መረጃ ማቅረብ አይችሉም።
3- በአፈጣጠር በኩል ነብዩ ﷺ እንደሌላው የአደም ዘር ሰው ናቸው። እዚህ ላይ ጥርጣሬ ሊገባን አይገባም። አላህ እንዲህ ሲል አዋጅ እንዲናገሩ አዟቸዋል፦
{قُلۡ إِنَّمَاۤ أَنَا۠ بَشَرࣱ مِّثۡلُكُمۡ}
" 'እኔ ቢጤያችሁ ሰው ብቻ ነኝ' በላቸው።" [ከህፍ፡ 110]
4- ወላጆቻቸው እና ዘር ማንዘራቸውም የሚታወቁ ናቸው። እሳቸውን ጨምሮ ሁሉም እንደ ሌላው የሰው ዘር የአደም ዘር ናቸው። አደም ከጭቃ መፈጠራቸው ግልፅ ነው።
5- ነብዩ ﷺ ሞተዋል። ስለዚህ "ከአላህ ኑር ነው የተፈጠሩት፣ የሱ ክፍል (ጁዝእ/ part) ናቸው'' የሚል ሰው የአላህ ክፍል ሙቷል እያለ ነው። ይሄ ሰቅጣጭ ድምዳሜ ነው። ለነገሩ እነዚህ ሰዎች የነብዩን ﷺ መሞትም ሊከራከሩ ይችላሉ። የሱፊያ እምነት በብዙ ነጥቦች ከ0ቅል ጋር የተኳረፈ እምነት ነው። እንኳን ነብዩን ﷺ ፤ በየመንደሩ ያሉ ሸይኾች ሲሞቱ "አልሞቱም፤ ሌላ አገር ወጥተዋል" እያሉ የሚያምኑ ብዙ ናቸው። ለማንኛውም ነብዩ ﷺ መዲና ሞተው ሶሐቦች አጥበው፣ ከፍነው፣ ሶላተል ጀናዛ ከሰገዱባቸው በኋላ ዓኢሻ ቤት ውስጥ ቀብረዋቸል። አላህም ሟችነታቸውን እንዲህ ሲል አስረግጦ ተናግሯል:-
{إِنَّكَ مَیِّتࣱ وَإِنَّهُم مَّیِّتُونَ}
"አንተ ሟች ነህ፤ እነርሱም ሟቾች ናቸው።" [አዙመር: 30]
"ሲሞት እንገላገለዋለን" ሲሉ ለነበሩ ጠላቶችም ''እርማችሁን አውጡ እሱ አይሞትም" አይደለም ያላቸው። ይሄውና ምላሹ፦
{وَمَا جَعَلۡنَا لِبَشَرࣲ مِّن قَبۡلِكَ ٱلۡخُلۡدَۖ أَفَإِی۟ن مِّتَّ فَهُمُ ٱلۡخَـٰلِدُونَ (34) كُلُّ نَفۡسࣲ ذَاۤىِٕقَةُ ٱلۡمَوۡتِۗ}
"(ሙሐመድ ሆይ!) ካንተ በፊት ለማንም ሰው ዘለዓለም መኖርን አላደረግንም። ታዲያ ብትሞት እነሱ ዘውታሪዎች ናቸውን? ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት።" [አልአንቢያእ፡ 34-35]
ማምታቻ:-
-
ነብዩ ﷺ ከኑር (ከብርሃን) ነው የተፈጠሩት የሚሉ አካላት አንድ እንዲህ የሚል የሚያቀርቡት "ሐዲሥ" አላቸው፦
أولُ ما خلق اللهُ نور نبيِّكَ يا جابرُ
"መጀመሪያ አላህ የፈጠረው የነብይህን ኑር (ብርሃን) ነው፣ ጃቢር ሆይ!"
ግና ይሄ ወሬ በየትኛውም የሐዲሥ ድርሳናት ውስጥ የማይገኝ መሰረተ ቢስ ወሬ ነው። [አሓዲሡን ሙንተሺረህ ላ ተሲሕ፡ ቁ. 393]
ሱፊዩ አሕመድ አልጉማሪ ራሱ መሰረተ ቢስ የፈጠራ ወሬ እንደሆነ ገልጿል።
(ኢብኑ መነወር፣ መስከረም 16/ 2015)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ይሄ ንግግር ሱፊዮች አካባቢ ተደጋግሞ የሚሰማ ነው። ምን ማለታቸው ነው?
* "ኑሩን" ሲሉ ነብዩን ﷺ ማለታቸው ነው።
* "ጀሊሉ" ሲሉ አላህ ማለታቸው ነው።
* "ከኑሩ" ሲሉ ከአላህ ኑር ማለታቸው ነው።
* ኸለቀው = ፈጠረው
ጥቅል መልእክቱ:-
አላህ ነብዩን ﷺ ከራሱ ኑር (ብርሃን) ነው የፈጠራቸው እያሉ ነው።
አንዳንዶቹ ይህንን መነሻ በማድረግ በግልፅ ነብዩ ﷺ የአላህ ክፍል (ጁዝእ/ part) ናቸው ብለዋል። ይሄ መሰረተ-የለሽ እምነት ነው። ለዚህም በተለያዩ ነጥቦች ምላሽ መስጠት ይቻላል።
1- ነብዩ ﷺ ምንም አይነት መለኮታዊ ድርሻ የላቸውም። ፍጡር ናቸው። ባሪያ ናቸው። ባሪያ ደግሞ የአላህ ክፍል ሊሆን አይችልም። መልእክተኛ ናቸው።
2- ነብዩ ﷺ ከኑር (ከብርሃን) ነው የተፈጠሩት የሚሉ አካላት መሰረተ ቢስ ወሬ እንጂ አንድም የቁርኣንም ይሁን የሐዲሥ መረጃ ማቅረብ አይችሉም።
3- በአፈጣጠር በኩል ነብዩ ﷺ እንደሌላው የአደም ዘር ሰው ናቸው። እዚህ ላይ ጥርጣሬ ሊገባን አይገባም። አላህ እንዲህ ሲል አዋጅ እንዲናገሩ አዟቸዋል፦
{قُلۡ إِنَّمَاۤ أَنَا۠ بَشَرࣱ مِّثۡلُكُمۡ}
" 'እኔ ቢጤያችሁ ሰው ብቻ ነኝ' በላቸው።" [ከህፍ፡ 110]
4- ወላጆቻቸው እና ዘር ማንዘራቸውም የሚታወቁ ናቸው። እሳቸውን ጨምሮ ሁሉም እንደ ሌላው የሰው ዘር የአደም ዘር ናቸው። አደም ከጭቃ መፈጠራቸው ግልፅ ነው።
5- ነብዩ ﷺ ሞተዋል። ስለዚህ "ከአላህ ኑር ነው የተፈጠሩት፣ የሱ ክፍል (ጁዝእ/ part) ናቸው'' የሚል ሰው የአላህ ክፍል ሙቷል እያለ ነው። ይሄ ሰቅጣጭ ድምዳሜ ነው። ለነገሩ እነዚህ ሰዎች የነብዩን ﷺ መሞትም ሊከራከሩ ይችላሉ። የሱፊያ እምነት በብዙ ነጥቦች ከ0ቅል ጋር የተኳረፈ እምነት ነው። እንኳን ነብዩን ﷺ ፤ በየመንደሩ ያሉ ሸይኾች ሲሞቱ "አልሞቱም፤ ሌላ አገር ወጥተዋል" እያሉ የሚያምኑ ብዙ ናቸው። ለማንኛውም ነብዩ ﷺ መዲና ሞተው ሶሐቦች አጥበው፣ ከፍነው፣ ሶላተል ጀናዛ ከሰገዱባቸው በኋላ ዓኢሻ ቤት ውስጥ ቀብረዋቸል። አላህም ሟችነታቸውን እንዲህ ሲል አስረግጦ ተናግሯል:-
{إِنَّكَ مَیِّتࣱ وَإِنَّهُم مَّیِّتُونَ}
"አንተ ሟች ነህ፤ እነርሱም ሟቾች ናቸው።" [አዙመር: 30]
"ሲሞት እንገላገለዋለን" ሲሉ ለነበሩ ጠላቶችም ''እርማችሁን አውጡ እሱ አይሞትም" አይደለም ያላቸው። ይሄውና ምላሹ፦
{وَمَا جَعَلۡنَا لِبَشَرࣲ مِّن قَبۡلِكَ ٱلۡخُلۡدَۖ أَفَإِی۟ن مِّتَّ فَهُمُ ٱلۡخَـٰلِدُونَ (34) كُلُّ نَفۡسࣲ ذَاۤىِٕقَةُ ٱلۡمَوۡتِۗ}
"(ሙሐመድ ሆይ!) ካንተ በፊት ለማንም ሰው ዘለዓለም መኖርን አላደረግንም። ታዲያ ብትሞት እነሱ ዘውታሪዎች ናቸውን? ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት።" [አልአንቢያእ፡ 34-35]
ማምታቻ:-
-
ነብዩ ﷺ ከኑር (ከብርሃን) ነው የተፈጠሩት የሚሉ አካላት አንድ እንዲህ የሚል የሚያቀርቡት "ሐዲሥ" አላቸው፦
أولُ ما خلق اللهُ نور نبيِّكَ يا جابرُ
"መጀመሪያ አላህ የፈጠረው የነብይህን ኑር (ብርሃን) ነው፣ ጃቢር ሆይ!"
ግና ይሄ ወሬ በየትኛውም የሐዲሥ ድርሳናት ውስጥ የማይገኝ መሰረተ ቢስ ወሬ ነው። [አሓዲሡን ሙንተሺረህ ላ ተሲሕ፡ ቁ. 393]
ሱፊዩ አሕመድ አልጉማሪ ራሱ መሰረተ ቢስ የፈጠራ ወሬ እንደሆነ ገልጿል።
(ኢብኑ መነወር፣ መስከረም 16/ 2015)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
መውሊድ የማያከብር ሰው የሙሐመድ ﷺ ጠላት ከሆነ፣ ገና የማያከብር ሰው የዒሳ ጠላት ነው!
~
መውሊድ ቀደምት የኢስላም ትውልዶች ዘንድ የማይታወቅ መጤ ፈጠራ መሆኑን ራሳቸው የመውሊድ አክባሪ የሆኑ አካላት የመሰከሩትን አሳልፌያለሁ። እነዚሁ አካላት መውሊድ ከክርስቲያኖቹ ገና ተኮርጆ በፉክክር እንደሚከበር የተናገሩቱን ደግሞ እናያለን። ዘግይተው የመጡ አንዳንድ የነጋባቸው ሱፍዮች ግን “መውሊድ በሀይማኖታችን መረጃዎች መሰረት የተፈቀደ በመሆኑ ላይ ከተግባባን ከክርስቲያን ወይም ከሂንዱ እምነት ጋር ባጋጣሚ ተመሳስሎ ቢገኝ ችግር የለውም” ይላሉ። በሀይማኖታችን መሰረት ቢኖረውማ እነ ኢብኑ ሐጀር “የመውሊድ ተግባር መሰረቱ ቢድዐ ነው። በሶስቱ ክፍለ ዘመናት ከነበሩት መልካም ቀደምቶች ከአንድም አልተላለፈም” አይሉም ነበር።
እያከበሩ ያሉት ሌላ መልክ ያለው ገና ነው፣ chrismas ማለት ልደት ማለት ነው። ልደት ማለት ደግሞ በዐረብኛው መውሊድ ማለት ነው። ስለዚህ የሚከበረው ማንነት እንጂ የተለየው የሚያከብሩት ገናን ነው። የክርስቲያኖች ገና = የሱፍዮች መውሊድ! የክርስቲያኖች መውሊድ = የሱፍዮች ገና!
እንዲያውም መውሊድን የሚያከብሩት ከክርስቲያኖች ጋር ለመፎካከር ብለው ነው። የፉክክር ዒባዳ ማለት ነው! ይህንን ሐቅ በኪታብ ሳይቀር ያሰፈሩት አሉ። መረጃ እጠቅሳለሁ፡-
1. ሰኻዊ ምን እንደሚል ተመልከቱ፡- “ባለ መስቀሎቹ (ክርስቲያኖች) የነብያቸውን ልደት ትልቁ ዒዳቸው አድርገው የሚይዙ ከሆነ ሙስሊሞችም (ነብያቸውን) በማክበርና በማላቅ ይበልጥ የተገቡ ናቸው።” [አቲብሩል መስቡክ፡ 14]
2. ከጀዘሪም ቃል በቃል ተላልፏል።
3. አቡል ዐባስ አልአዘፊ (መውሊድን ለምዕራቡ ዐረቢያ ያስተዋወቀ ነው)፡- በክርስቲያን በዓላት ላይ የሚሳተፉ ወጣቶችን ለመመለስ ሲል እንደጀመረው በግልፅ ተናግሯል።
4. ዐብዱላህ አልሀረሪ (የአሕባሾቹ መሪ):- ንጉስ ሙዞፈር መውሊድን የጀመረው ክርስቲያኖች የመሲሕ ልደትን በዓል ሲያከብሩ ተመልክቶ ነው። በዚህም ሳቢያ ሰይዳችንን ሙሐመድን ﷺ ስላወጣልን አላህን ለማመስገን ሲል መውሊድን ጀመረ ይላል። [ኢዝሃሩል ዐቂደቲ ሱኒያህ፡ 240]
ተመልከቱ እንግዲህ ! እንዲህ ዓይነት አሳፋሪ አመክንዮ እየጠቀሱ የመውሊድ ቢድዐን የፈቀዱ አካላትን እየዘረዘሩ ነው በብዛት ሊያሳምኑ፣ ራሳቸውን ሸውደው ሌሎችን ሊሸውዱ የሚነሱት። ለማንኛውም የመውሊድ ቢድዐን በፉክክር የተለከፉ ሰዎች የፈጠሩት መጤ ፈሊጥ ነው። በዚህ መልኩ በሌሎች መመሳሰል የተወገዘ እንደሆነ ነብያችን ﷺ አጥብቀው አሳስበው ነበር።
* ማስረጃ አንድ፦
مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ
"አንድን ሕዝብ የተመሳሰለ (የተከተለ) ከእነርሱ ነው (እንደነርሱ ይቆጠራል)።" [አቡ ዳውድ ፡ 4031]
* ማስረጃ ሁለት፦
በሌላም ሐዲሥ ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
لتتَّبعنَّ سَننَ من كانَ قبلَكم حذو القُذَّةِ بالقُذَّةِ حتَّى لو دخلوا جحرَ ضبٍّ لدخلتُموه. قالوا: اليَهودُ والنَّصارى؟ قالَ: فمَن
“በርግጥ ከናንተ በፊት የነበሩ ሰዎችን ፈለጎች ስንዝር በስንዝር ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ። የወከሎ ጉድጓድ ቢገቡ እንኳን በርግጥም ትገቡታላችሁ!” ሲሉ “አይሁድና ክርስቲያኖችን ነው (ትከተላላችሁ) የምትለን?” ብለው ቢጠይቁ “ታዲያ ማንን ነው?!” አሉ። [ቡኻሪ፡ 7320]
የተናገሩት በትክክል ተፈፀመ። ለብዙ ጥፋቶች የሚያጋልጠው በዓል ከክርስቲያኖች ተኮርጆ በ"ፋጢሚያ" ሺዐዎች ተጠንስሶ፣ በሱፍዮች ተዛምቶ ብዙ ሙስሊም ሊዘፈቅበት በቅቷል።
የሚያሳፍረው “ክርስቲያኖቹ የነብያቸውን ልደት እያከበሩ የኛ ነብይ ከማን ያንሳሉ?” የሚሉት ነገር ነው። ሱብሓነላህ! ለመሆኑ ዒሳ የኢስላም ነብይ አይደሉም እንዴ?! ታዲያ ይሄ ምን የሚሉት አፀያፊ ሎጂክ ነው? ደግሞ ምንም ሳያፍሩ መውሊድን የሚቃወሙ ሙስሊሞችን “የነቢ ጠላቶች ናቸው!” እያሉ ከባድ ክስ ይከሳሉ። የነብዩን ﷺ መውሊድ አለማክበር እሳቸውን መጥላት ከሆነ እናንተም የክርስቲያኖቹን ገና (chrismasን) ባለማክበራችሁ የዒሳ ጠላቶች ናችሁ ማለት ነው። መውሊድን ማክበር ነብዩን ﷺ ማክበር ከሆነ የሌሎቹን ነብያት ልደቶች ስለማታከብሩ ለሌሎች ነብያት በሙሉ ክብር የሌላችሁ የነብያት ጠላቶች ናችሁ ማለት ነው። ከአንደበታችሁ በቀጥታ ባይወጣም አመክኗችሁ የሚሰጠው ይህንን ነው።
ኢብኑ ሙነወር
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
መውሊድ ቀደምት የኢስላም ትውልዶች ዘንድ የማይታወቅ መጤ ፈጠራ መሆኑን ራሳቸው የመውሊድ አክባሪ የሆኑ አካላት የመሰከሩትን አሳልፌያለሁ። እነዚሁ አካላት መውሊድ ከክርስቲያኖቹ ገና ተኮርጆ በፉክክር እንደሚከበር የተናገሩቱን ደግሞ እናያለን። ዘግይተው የመጡ አንዳንድ የነጋባቸው ሱፍዮች ግን “መውሊድ በሀይማኖታችን መረጃዎች መሰረት የተፈቀደ በመሆኑ ላይ ከተግባባን ከክርስቲያን ወይም ከሂንዱ እምነት ጋር ባጋጣሚ ተመሳስሎ ቢገኝ ችግር የለውም” ይላሉ። በሀይማኖታችን መሰረት ቢኖረውማ እነ ኢብኑ ሐጀር “የመውሊድ ተግባር መሰረቱ ቢድዐ ነው። በሶስቱ ክፍለ ዘመናት ከነበሩት መልካም ቀደምቶች ከአንድም አልተላለፈም” አይሉም ነበር።
እያከበሩ ያሉት ሌላ መልክ ያለው ገና ነው፣ chrismas ማለት ልደት ማለት ነው። ልደት ማለት ደግሞ በዐረብኛው መውሊድ ማለት ነው። ስለዚህ የሚከበረው ማንነት እንጂ የተለየው የሚያከብሩት ገናን ነው። የክርስቲያኖች ገና = የሱፍዮች መውሊድ! የክርስቲያኖች መውሊድ = የሱፍዮች ገና!
እንዲያውም መውሊድን የሚያከብሩት ከክርስቲያኖች ጋር ለመፎካከር ብለው ነው። የፉክክር ዒባዳ ማለት ነው! ይህንን ሐቅ በኪታብ ሳይቀር ያሰፈሩት አሉ። መረጃ እጠቅሳለሁ፡-
1. ሰኻዊ ምን እንደሚል ተመልከቱ፡- “ባለ መስቀሎቹ (ክርስቲያኖች) የነብያቸውን ልደት ትልቁ ዒዳቸው አድርገው የሚይዙ ከሆነ ሙስሊሞችም (ነብያቸውን) በማክበርና በማላቅ ይበልጥ የተገቡ ናቸው።” [አቲብሩል መስቡክ፡ 14]
2. ከጀዘሪም ቃል በቃል ተላልፏል።
3. አቡል ዐባስ አልአዘፊ (መውሊድን ለምዕራቡ ዐረቢያ ያስተዋወቀ ነው)፡- በክርስቲያን በዓላት ላይ የሚሳተፉ ወጣቶችን ለመመለስ ሲል እንደጀመረው በግልፅ ተናግሯል።
4. ዐብዱላህ አልሀረሪ (የአሕባሾቹ መሪ):- ንጉስ ሙዞፈር መውሊድን የጀመረው ክርስቲያኖች የመሲሕ ልደትን በዓል ሲያከብሩ ተመልክቶ ነው። በዚህም ሳቢያ ሰይዳችንን ሙሐመድን ﷺ ስላወጣልን አላህን ለማመስገን ሲል መውሊድን ጀመረ ይላል። [ኢዝሃሩል ዐቂደቲ ሱኒያህ፡ 240]
ተመልከቱ እንግዲህ ! እንዲህ ዓይነት አሳፋሪ አመክንዮ እየጠቀሱ የመውሊድ ቢድዐን የፈቀዱ አካላትን እየዘረዘሩ ነው በብዛት ሊያሳምኑ፣ ራሳቸውን ሸውደው ሌሎችን ሊሸውዱ የሚነሱት። ለማንኛውም የመውሊድ ቢድዐን በፉክክር የተለከፉ ሰዎች የፈጠሩት መጤ ፈሊጥ ነው። በዚህ መልኩ በሌሎች መመሳሰል የተወገዘ እንደሆነ ነብያችን ﷺ አጥብቀው አሳስበው ነበር።
* ማስረጃ አንድ፦
مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ
"አንድን ሕዝብ የተመሳሰለ (የተከተለ) ከእነርሱ ነው (እንደነርሱ ይቆጠራል)።" [አቡ ዳውድ ፡ 4031]
* ማስረጃ ሁለት፦
በሌላም ሐዲሥ ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
لتتَّبعنَّ سَننَ من كانَ قبلَكم حذو القُذَّةِ بالقُذَّةِ حتَّى لو دخلوا جحرَ ضبٍّ لدخلتُموه. قالوا: اليَهودُ والنَّصارى؟ قالَ: فمَن
“በርግጥ ከናንተ በፊት የነበሩ ሰዎችን ፈለጎች ስንዝር በስንዝር ክንድ በክንድ ትከተላላችሁ። የወከሎ ጉድጓድ ቢገቡ እንኳን በርግጥም ትገቡታላችሁ!” ሲሉ “አይሁድና ክርስቲያኖችን ነው (ትከተላላችሁ) የምትለን?” ብለው ቢጠይቁ “ታዲያ ማንን ነው?!” አሉ። [ቡኻሪ፡ 7320]
የተናገሩት በትክክል ተፈፀመ። ለብዙ ጥፋቶች የሚያጋልጠው በዓል ከክርስቲያኖች ተኮርጆ በ"ፋጢሚያ" ሺዐዎች ተጠንስሶ፣ በሱፍዮች ተዛምቶ ብዙ ሙስሊም ሊዘፈቅበት በቅቷል።
የሚያሳፍረው “ክርስቲያኖቹ የነብያቸውን ልደት እያከበሩ የኛ ነብይ ከማን ያንሳሉ?” የሚሉት ነገር ነው። ሱብሓነላህ! ለመሆኑ ዒሳ የኢስላም ነብይ አይደሉም እንዴ?! ታዲያ ይሄ ምን የሚሉት አፀያፊ ሎጂክ ነው? ደግሞ ምንም ሳያፍሩ መውሊድን የሚቃወሙ ሙስሊሞችን “የነቢ ጠላቶች ናቸው!” እያሉ ከባድ ክስ ይከሳሉ። የነብዩን ﷺ መውሊድ አለማክበር እሳቸውን መጥላት ከሆነ እናንተም የክርስቲያኖቹን ገና (chrismasን) ባለማክበራችሁ የዒሳ ጠላቶች ናችሁ ማለት ነው። መውሊድን ማክበር ነብዩን ﷺ ማክበር ከሆነ የሌሎቹን ነብያት ልደቶች ስለማታከብሩ ለሌሎች ነብያት በሙሉ ክብር የሌላችሁ የነብያት ጠላቶች ናችሁ ማለት ነው። ከአንደበታችሁ በቀጥታ ባይወጣም አመክኗችሁ የሚሰጠው ይህንን ነው።
ኢብኑ ሙነወር
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
ሙታንን፣ መቃብርን ማምለክ፣ እነሱን ድረሱልን ማለት፣ ለጭንቅ ለችግር እነሱን መጣራት የኺላፍ ርእስ ነው። የመካ ሙሽሪኮች እና ሙስሊሞች ተለያይተውበታል። በሰይፍ ተሞሻልቀውበታል።
ሙስሊሞቹ ይሄ የዘላለም ህይወትን የሚያበላሽ ትልቅ ሺርክ ነው ሲሉ እነ አቡ ጀህል ደግሞ ወደ አላህ መቃረቢያ ዒባዳ ነው ብለዋል። አንተ ከየትኛው ምድብ ነህ?
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
ሙስሊሞቹ ይሄ የዘላለም ህይወትን የሚያበላሽ ትልቅ ሺርክ ነው ሲሉ እነ አቡ ጀህል ደግሞ ወደ አላህ መቃረቢያ ዒባዳ ነው ብለዋል። አንተ ከየትኛው ምድብ ነህ?
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
አንዳንድ አካባቢ ከተማ ውስጥ ክላሽ ተሸክመው መስጂድ የሚገቡ ሰዎች አሉ። ተጨባጭ ስጋት ካልገጠመ በስተቀር ይሄ ተግባር ተገቢ አይደለም። መስጂድ ውስጥ ሰጋጆች ምንም አይነት ስጋት እንዲሰማቸው የሚያደርግ ነገር መኖር የለበትም። አንዳንዱ ሰው ምንም አይነት ስጋት በሌለበት እንዲሁ ለመታየት፣ ለጉራ ነው ጠመንጃ ተሸክሞ መስጂድ የሚመጣው። ይሄ አሳፋሪ ነገር ነው። እየታሰበ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
ኢብኑ ሙፍሊሕ አልሐንበሊይ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦
"ሰዎች ባንተ ላይ መናገራቸው አያሳዝንህ። የተናገሩብህ ውሸት ከሆነ ያልፈፀምከው በጎ ስራ ይያዝልሃል። እውነት ከሆነ ደግሞ ቅጣቱ የፈጠነብህ ሃጢአትህ ነው።"
[አልኣዳቡ ሸርዒየህ፡ 1/12]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
"ሰዎች ባንተ ላይ መናገራቸው አያሳዝንህ። የተናገሩብህ ውሸት ከሆነ ያልፈፀምከው በጎ ስራ ይያዝልሃል። እውነት ከሆነ ደግሞ ቅጣቱ የፈጠነብህ ሃጢአትህ ነው።"
[አልኣዳቡ ሸርዒየህ፡ 1/12]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Forwarded from عبدالكريم via @Qualitymovebot
🍃መውሊድን የተመለከተ🍂
{ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነውር }
የተዘጋጁ ፅሁፎች ስብስብ ከስር ርዕሳቸውን
በመጫን ታገኛላችሁ👇
{ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነውር }
የተዘጋጁ ፅሁፎች ስብስብ ከስር ርዕሳቸውን
በመጫን ታገኛላችሁ👇
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
የመውሊድ ደጋፊ ምሁራን ዝርዝር ሲፈተሽ
~
መውሊድን የፈቀዱ ዓሊሞች ብለው የስም ዝርዝር የሚለጥፉ ሰዎች አሉ። ይህን የሚያደርጉት ጉዳዩን ዝቅ ሲል ቀላል የፊቅህ ርእስ አድርገን እንድንመለከት፣ ከፍ ሲል ደግሞ የብዙሃን ዑለማእ ድጋፍ ያለው ለማስመሰል ነው። ሁለቱም ግን የሚያስኬድ አይደለም። ሁለቱንም ነጥቦች በየተራ እንመልከት።
1ኛ ነጥብ - መውሊድ ቀላል ጥፋት አይደለም።
አብዛኛው የመውሊድ አከባበር ላይ ግልፅ የሺርክ ተግባራት እና ሌሎች ጥፋቶች በሚፈፀሙበት እውነታ ጉዳዩን ቀላል የፊቅህ ልዩነት አድርጎ ማቅረብ እነዚህ አካላት ሺርክ የማይጎረብጣቸው እንደሆኑ፣ ባስ ሲልም የሺርክ ደጋፊዎች እንደሆኑ ነው የሚያሳየው። መውሊድ የሚፈፀምባቸው እጅግ ብዙ ቦታዎች ዶሪሕ አለባቸው። በቀብሩ ዙሪያና አካባቢው የሚፈፀሙ የሺርክ ተግባራት ሲበዛ ዘግናኝ ናቸው። ከመስጂድ ውስጥ ከሚያዜሟቸው መንዙማዎችም ውስጥ ሺርክ ያለባቸው ብዙ ናቸው። በመስጂድ ውስጥ የሚፈፀሙ ጭፈራዎችም ከመውሊድ ጋር እጅና ጓንት ሆነው የተሰፉ ናቸው። ባጭሩ መውሊድ ከነዚህ ጥፋቶች የመፅዳት እድሉ እጅግ የመነመነ እንደሆነ ከነቃፊ ባልተናነሰ ደጋፊ ዑለማዎች ሳይቀር የገለፁት ሐቅ ነው። ምሳሌ ልጥቀስ፡-
1. ሀይተሚ፡- “ከፊሎቹ (መውሊዶች) ሸር የለባቸውም። ግን ይሄ አልፎ አልፎ ነው ያለው” ይላል። [አልፈታወል ሐዲሢያህ፡ 109]
2. ሙሐመድ ዒሊሽ፡- “ለነብዩ ﷺ መውሊድ ማዘጋጀት የተወደደ አይደለም፣ በተለይ ደግሞ የድምፅን ቅላፄ ከፍ ዝቅ እያደረጉ እንደመቅራትና እንደ ዘፈን ያለ የተጠላ ነገር ያካተተ ከሆነ። በዚህ ዘመን ደግሞ ከዚህ ይቅርና ከዚህ የከፋ ከሆነም ነገር አይተርፍም።” [ፈትወል ዐልዪል ማሊክ፡ 1/171]
ጭፈራ ሲኖርስ? ሲዩጢ እንዲህ ይላል፡-
“ከነዚህም (ከቢድዐዎች) ውስጥ የሆነው በመስጂድ ውስጥ የሚፈፀም ጭፈራ፣ ዘፈን፣ ድቤ መምታት፣ መሰንቆና ሌሎችም የሙዚቃ መሳሪያዎች ናቸው። ይህንን ከመስጂድ ውስጥ የፈፀመ ሊባረርና ሊደ - በ ^ደብ የሚገባው ጠ ^ማ^ማ ሙብ ^ ተዲዕ ነው። ምክንያቱም አላህ እንዲልላቅ ያዘዘውን ነገር እያቃለለ ነውና። … (ከመስጂድ ውስጥ) የዘፈነ ወይም የጨፈረ ቅጣት የሚገባው የሆነ ጠሞ አጥ ^ማሚ ሙብ ^ተዲዕ ነው።” [ሐቂቀቱ ሱና ወልቢድዐ፡ 191]
በሃገራችን በታዋቂ ቦታዎች ያለው አከባበር ከሰሜን እስከ ደቡብ፤ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ እንዳለ ይሄ ነው። ከተበላ፣ ከተጠጣ፣ ጫት ከተቃመ በኋላ ከዚያ የሺርክ መንዙማ፣ ጭፈራ፣ የሴትና የወንድ ቅልቅል፣ ዝላይ፣ ማናፋት ነው የሚከተለው። ከዚያ አብዛኛው ሱብሒ የለ፣ ዙህር የለ ተኝቶ ነው የሚውለው።
አከባበሩ የተጠቀሱት ጥፋቶች ባይኖሩበት ራሱ ከቢድ0ነት አያልፍም። ማስረጃ የሌለው ዒባዳ ቢድዐ ነው። ቢድዐ ደግሞ በነብዩ ﷺ አንደበት ጥመት ተብሎ ተገልጿል። [ሙስሊም፡ 867] ኢብኑ ዑመር ረዲየላሁ ዐንሁ "ቢድዐ ሁሉ ጥመት ነው፤ ሰዎች መልካም አድርገው ቢያስቡትም" ብለዋል። [አልኢባናህ፡ 205] እንዲያውም የሆነ ሰው ከጎናቸው አስነጠሰውና "አልሐምዱ ሊላህ፣ ወሰላሙ ዐላ ረሱሊላህ!" አለ። በዚህን ጊዜ ኢብኑ ዑመር "እኔም ምስጋና ለአላህ፣ ሰላም ደግሞ ለአላህ መልእክተኛ ይሁን እላለሁ። ይሁን እንጂ የአላህ መልእክተኛ በዚህ መልኩ አይደለም (ስናስነጥስ እንድንል) ያስተማሩን። ይልቁንም በየትኛውም ሁኔታ 'አልሐምዱ ሊላህ' እንድንል ነው ያስተማሩን" አሉት። [ቲርሚዚ፡ 2738] ኢማሙ ማሊክም ለኢሕራም መነሻ ዘልሑለይፋን ጥሎ ከነብዩ ﷺ ቀብር ሊያደርግ ያሰበውን ሰው "እንደሱ አታድርግ፡፡ እኔ ፈተናን እፈራልሃለሁ!" ነው ያሉት። [ሒልየቱል አውሊያእ፡ 6326] እንጂ "ይሄ ቀላል ነው፤ ምን ችግር አለበት?" አይደለም ያሉት።
2ኛ ነጥብ - ዝርዝራቸው እርባና ያለው ማስረጃ አይደለም! ለምን?
[ሀ]:- መውሊድ የብዙሀን ዑለማእ ድጋፍ የለውም። እንዴት? በረጅሙ የኢስላም ታሪክ ቢፈተሽ:-
1- ድፍን የሶሐባ፣ የታቢዒይ እና የአትባዑ ታቢዒን ትውልድ መውሊድን አላከበረም። እነዚህ ሶስት ትውልዶች ማለት ነብያችን ﷺ "ከሰው ሁሉ በላጩ የኔ ትውልድ ነው። ከዚያም የሚቀጥለው፤ ከዚያም የሚቀጥለው" ብለው የመሰከሩላቸው ናቸው። [ቡኻሪ፡ 2652] [ሙስሊም፡ 2533]
2- እንደ ቡኻሪ፣ ሙስሊም፣ አቡ ዳውድ፣ ... ያለ ድፍን ቀደምት የሐዲሥ ምሁራን ትውልድ መውሊድን አላከበረም። ዛሬ እናንተ በጉልበት ለመውሊድ ማስረጃ የምታደርጓቸውን ሐዲሦች የዘገቧቸው እነዚህ ናቸው። ከናንተ በላይ የሚያውቁ፣ ከናንተ በላይ ነብዩን ﷺ የሚወዱ ከመሆናቸው ጋር አንዳቸውም መውሊድ አላከበሩም።
5- ከነ ኢብኑ ዐባስ፣ ሙጃሂድ፣ ይዞ አምስት፣ ስድስት ክፍለ ዘመን ብትቆጥሩ አንድም የቁርኣን ሙፈሲር መውሊድን አላከበሩም። ዛሬ እናንተ በፈጣጣ ለመውሊድ ማስረጃ የምታደርጓቸውን የቁርኣን አንቀፆች ከናንተ በላይ የሚያውቁ ከመሆናቸው ጋር አመታዊ ጭፈራ ልማዳቸው አልነበረም፡፡ ለነብዩ ﷺ የነበራቸው ውዴታ ከናንተ ያነሰ ሆኖ ይሆን?
6- የአራቱ መዝሀቦች ኢማሞች (አቡ ሐኒፋ፣ ማሊክ፣ ሻፊዒይ እና አሕመድ) መውሊድን አላከበሩም። በነሱም በተከታዮቻቸውም የፊቅህ ኪታቦች ውስጥ ስለ መውሊድ አከባበርና ዋጋው የሚያትት አንድ ርእስ (ባብ / ፈስል / ኪታብ) የለም። የናንተን ያህል ዲኑን ስለማያውቁት ይሆን?
7- በዘመናት ውስጥ ከተተካኩት የሙስሊሙ ዓለም መሪዎች ውስጥ:- ኹለፋኡ ራሺዲን፣ በኑ ኡመያ፣ መሰረታቸውን በግዳድ ላይ ያደረጉት በኑል ዐባስ፣ ሰልጁቆችም እንዳለ መውሊድን አላከበሩም።
8- እንደ አቡል ሐሰን አልአሽዐሪ፣ አቡ መንሱር አልማቱሪዲ፣ ... ያሉ የአሽዐሪያና የማቱሪዲያ መስራቾችና ቀደምት ተከታዮቻቸው መውሊድን አላከበሩም።
8- እንደ አቡ ዐብዲረሕማን አሱለሚ፣ ቁሸይሪ፣ አቡ ሓሚድ አልገዛሊ፣ ጀይላኒ፣ ... ያሉ ቀደም ያሉ ሱፍዮችም መውሊድን አላከበሩም። ለነብዩ ﷺ ውዴታ ስላልነበራቸው ይሆን?
9- የነብዩን ﷺ ሲራ የከተቡ ቀደምት ፀሐፊዎች ለምሳሌ ኢብኑ ኢስሓቅ፣ ኢብኑ ሂሻም፣ ዋቂዲ፣ ኢብኑ ሰዕድ፣ በላዙሪይ፣ ጦበሪ፣ ሱሃይሊይ፣ ... አንዳቸውም መውሊድን አላከበሩም። ጉዳዩን ስለማያውቁት? ወይስ ስለማይወዷቸው?
10- እንዲሁም ቀደም ብለው የነብዩን ﷺ ሸማኢሎች የከተቡ እንደ ቲርሚዚይ፣ አቡ ኑዐይም አልአስበሃኒ፣ ቃዲ ዒያድ፣ በይሀቂ፣ ወዘተ . አንዳቸውም መውሊድን አላከበሩም።
ይሄ ሁሉ እልፍ አእላፍ ዑለማእ ብዙሃን ሳይሆን የትኛው ዝርዝር ነው ብዙሃን የሚሆነው? የሰለፎቹን ኢጅማዕ በመጣል ከ7ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ የመጡ አካላትን እየዘረዘሩ "ብዙ ነን" የሚል የህፃናት እንቁልልጭ ውስጥ መግባት ሞኝነት ነው። የምትጠቅሷቸው ሁሉም ቢደመሩ ከሶሐባ ትውልድ ጋር የሚነፃፀር የላቸውም።
[ለ]፦ የምትዘረዝሯቸው ዓሊሞች ብዙሃን አይደሉም እንጂ ቢሆኑስ?
ከመቼ ጀምሮ ነው የቁጥር ብዛት መለኪያ የሆነው? እነ ሐሰን ታጁ፣ ኣደም ሙሐመድ እና ኢስሓቅ እሸቱ ያሉ ደፋሮች ከሰለፍ እስከ ኸለፍ ያለፉ ዑለማዎችን ረጋግጠው ለዘፈን ጥብቅና ሲቆሙ የብዙሃን ዑለማእ ተግሳፅ አልገታቸውም። ለመውሊድ የሚዘረዝሯቸው እንዳለ ሙዚቃን ያወግዛሉ። ቢሆንም ደንገጥ እንኳን አይሉም። እነዚህ የዘፈን ጠበቆዎች ደጋፊ ዓሊሞች ጭምር ቢድዐነቱን ለሚመሰክሩበት የመውሊድ ጉዳይ ግን ከሀሰተኛ "ብዙሃን" ጀርባ ያደፍጣሉ። ሁለቱም ቦታ ላይ ሚዛናቸው ስሜታቸው ነው። እንጂ ለማስረጃም ለብዙሃንም ደንታ ያላቸው አይደሉም። በተረፈ የዲን ጉዳይ በወሕይ እንጂ እንደ ፓርላማ በእጅ ብልጫ የሚወሰንበት አይደለም። አላህ እንዲህ ይላል:-
~
መውሊድን የፈቀዱ ዓሊሞች ብለው የስም ዝርዝር የሚለጥፉ ሰዎች አሉ። ይህን የሚያደርጉት ጉዳዩን ዝቅ ሲል ቀላል የፊቅህ ርእስ አድርገን እንድንመለከት፣ ከፍ ሲል ደግሞ የብዙሃን ዑለማእ ድጋፍ ያለው ለማስመሰል ነው። ሁለቱም ግን የሚያስኬድ አይደለም። ሁለቱንም ነጥቦች በየተራ እንመልከት።
1ኛ ነጥብ - መውሊድ ቀላል ጥፋት አይደለም።
አብዛኛው የመውሊድ አከባበር ላይ ግልፅ የሺርክ ተግባራት እና ሌሎች ጥፋቶች በሚፈፀሙበት እውነታ ጉዳዩን ቀላል የፊቅህ ልዩነት አድርጎ ማቅረብ እነዚህ አካላት ሺርክ የማይጎረብጣቸው እንደሆኑ፣ ባስ ሲልም የሺርክ ደጋፊዎች እንደሆኑ ነው የሚያሳየው። መውሊድ የሚፈፀምባቸው እጅግ ብዙ ቦታዎች ዶሪሕ አለባቸው። በቀብሩ ዙሪያና አካባቢው የሚፈፀሙ የሺርክ ተግባራት ሲበዛ ዘግናኝ ናቸው። ከመስጂድ ውስጥ ከሚያዜሟቸው መንዙማዎችም ውስጥ ሺርክ ያለባቸው ብዙ ናቸው። በመስጂድ ውስጥ የሚፈፀሙ ጭፈራዎችም ከመውሊድ ጋር እጅና ጓንት ሆነው የተሰፉ ናቸው። ባጭሩ መውሊድ ከነዚህ ጥፋቶች የመፅዳት እድሉ እጅግ የመነመነ እንደሆነ ከነቃፊ ባልተናነሰ ደጋፊ ዑለማዎች ሳይቀር የገለፁት ሐቅ ነው። ምሳሌ ልጥቀስ፡-
1. ሀይተሚ፡- “ከፊሎቹ (መውሊዶች) ሸር የለባቸውም። ግን ይሄ አልፎ አልፎ ነው ያለው” ይላል። [አልፈታወል ሐዲሢያህ፡ 109]
2. ሙሐመድ ዒሊሽ፡- “ለነብዩ ﷺ መውሊድ ማዘጋጀት የተወደደ አይደለም፣ በተለይ ደግሞ የድምፅን ቅላፄ ከፍ ዝቅ እያደረጉ እንደመቅራትና እንደ ዘፈን ያለ የተጠላ ነገር ያካተተ ከሆነ። በዚህ ዘመን ደግሞ ከዚህ ይቅርና ከዚህ የከፋ ከሆነም ነገር አይተርፍም።” [ፈትወል ዐልዪል ማሊክ፡ 1/171]
ጭፈራ ሲኖርስ? ሲዩጢ እንዲህ ይላል፡-
“ከነዚህም (ከቢድዐዎች) ውስጥ የሆነው በመስጂድ ውስጥ የሚፈፀም ጭፈራ፣ ዘፈን፣ ድቤ መምታት፣ መሰንቆና ሌሎችም የሙዚቃ መሳሪያዎች ናቸው። ይህንን ከመስጂድ ውስጥ የፈፀመ ሊባረርና ሊደ - በ ^ደብ የሚገባው ጠ ^ማ^ማ ሙብ ^ ተዲዕ ነው። ምክንያቱም አላህ እንዲልላቅ ያዘዘውን ነገር እያቃለለ ነውና። … (ከመስጂድ ውስጥ) የዘፈነ ወይም የጨፈረ ቅጣት የሚገባው የሆነ ጠሞ አጥ ^ማሚ ሙብ ^ተዲዕ ነው።” [ሐቂቀቱ ሱና ወልቢድዐ፡ 191]
በሃገራችን በታዋቂ ቦታዎች ያለው አከባበር ከሰሜን እስከ ደቡብ፤ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ እንዳለ ይሄ ነው። ከተበላ፣ ከተጠጣ፣ ጫት ከተቃመ በኋላ ከዚያ የሺርክ መንዙማ፣ ጭፈራ፣ የሴትና የወንድ ቅልቅል፣ ዝላይ፣ ማናፋት ነው የሚከተለው። ከዚያ አብዛኛው ሱብሒ የለ፣ ዙህር የለ ተኝቶ ነው የሚውለው።
አከባበሩ የተጠቀሱት ጥፋቶች ባይኖሩበት ራሱ ከቢድ0ነት አያልፍም። ማስረጃ የሌለው ዒባዳ ቢድዐ ነው። ቢድዐ ደግሞ በነብዩ ﷺ አንደበት ጥመት ተብሎ ተገልጿል። [ሙስሊም፡ 867] ኢብኑ ዑመር ረዲየላሁ ዐንሁ "ቢድዐ ሁሉ ጥመት ነው፤ ሰዎች መልካም አድርገው ቢያስቡትም" ብለዋል። [አልኢባናህ፡ 205] እንዲያውም የሆነ ሰው ከጎናቸው አስነጠሰውና "አልሐምዱ ሊላህ፣ ወሰላሙ ዐላ ረሱሊላህ!" አለ። በዚህን ጊዜ ኢብኑ ዑመር "እኔም ምስጋና ለአላህ፣ ሰላም ደግሞ ለአላህ መልእክተኛ ይሁን እላለሁ። ይሁን እንጂ የአላህ መልእክተኛ በዚህ መልኩ አይደለም (ስናስነጥስ እንድንል) ያስተማሩን። ይልቁንም በየትኛውም ሁኔታ 'አልሐምዱ ሊላህ' እንድንል ነው ያስተማሩን" አሉት። [ቲርሚዚ፡ 2738] ኢማሙ ማሊክም ለኢሕራም መነሻ ዘልሑለይፋን ጥሎ ከነብዩ ﷺ ቀብር ሊያደርግ ያሰበውን ሰው "እንደሱ አታድርግ፡፡ እኔ ፈተናን እፈራልሃለሁ!" ነው ያሉት። [ሒልየቱል አውሊያእ፡ 6326] እንጂ "ይሄ ቀላል ነው፤ ምን ችግር አለበት?" አይደለም ያሉት።
2ኛ ነጥብ - ዝርዝራቸው እርባና ያለው ማስረጃ አይደለም! ለምን?
[ሀ]:- መውሊድ የብዙሀን ዑለማእ ድጋፍ የለውም። እንዴት? በረጅሙ የኢስላም ታሪክ ቢፈተሽ:-
1- ድፍን የሶሐባ፣ የታቢዒይ እና የአትባዑ ታቢዒን ትውልድ መውሊድን አላከበረም። እነዚህ ሶስት ትውልዶች ማለት ነብያችን ﷺ "ከሰው ሁሉ በላጩ የኔ ትውልድ ነው። ከዚያም የሚቀጥለው፤ ከዚያም የሚቀጥለው" ብለው የመሰከሩላቸው ናቸው። [ቡኻሪ፡ 2652] [ሙስሊም፡ 2533]
2- እንደ ቡኻሪ፣ ሙስሊም፣ አቡ ዳውድ፣ ... ያለ ድፍን ቀደምት የሐዲሥ ምሁራን ትውልድ መውሊድን አላከበረም። ዛሬ እናንተ በጉልበት ለመውሊድ ማስረጃ የምታደርጓቸውን ሐዲሦች የዘገቧቸው እነዚህ ናቸው። ከናንተ በላይ የሚያውቁ፣ ከናንተ በላይ ነብዩን ﷺ የሚወዱ ከመሆናቸው ጋር አንዳቸውም መውሊድ አላከበሩም።
5- ከነ ኢብኑ ዐባስ፣ ሙጃሂድ፣ ይዞ አምስት፣ ስድስት ክፍለ ዘመን ብትቆጥሩ አንድም የቁርኣን ሙፈሲር መውሊድን አላከበሩም። ዛሬ እናንተ በፈጣጣ ለመውሊድ ማስረጃ የምታደርጓቸውን የቁርኣን አንቀፆች ከናንተ በላይ የሚያውቁ ከመሆናቸው ጋር አመታዊ ጭፈራ ልማዳቸው አልነበረም፡፡ ለነብዩ ﷺ የነበራቸው ውዴታ ከናንተ ያነሰ ሆኖ ይሆን?
6- የአራቱ መዝሀቦች ኢማሞች (አቡ ሐኒፋ፣ ማሊክ፣ ሻፊዒይ እና አሕመድ) መውሊድን አላከበሩም። በነሱም በተከታዮቻቸውም የፊቅህ ኪታቦች ውስጥ ስለ መውሊድ አከባበርና ዋጋው የሚያትት አንድ ርእስ (ባብ / ፈስል / ኪታብ) የለም። የናንተን ያህል ዲኑን ስለማያውቁት ይሆን?
7- በዘመናት ውስጥ ከተተካኩት የሙስሊሙ ዓለም መሪዎች ውስጥ:- ኹለፋኡ ራሺዲን፣ በኑ ኡመያ፣ መሰረታቸውን በግዳድ ላይ ያደረጉት በኑል ዐባስ፣ ሰልጁቆችም እንዳለ መውሊድን አላከበሩም።
8- እንደ አቡል ሐሰን አልአሽዐሪ፣ አቡ መንሱር አልማቱሪዲ፣ ... ያሉ የአሽዐሪያና የማቱሪዲያ መስራቾችና ቀደምት ተከታዮቻቸው መውሊድን አላከበሩም።
8- እንደ አቡ ዐብዲረሕማን አሱለሚ፣ ቁሸይሪ፣ አቡ ሓሚድ አልገዛሊ፣ ጀይላኒ፣ ... ያሉ ቀደም ያሉ ሱፍዮችም መውሊድን አላከበሩም። ለነብዩ ﷺ ውዴታ ስላልነበራቸው ይሆን?
9- የነብዩን ﷺ ሲራ የከተቡ ቀደምት ፀሐፊዎች ለምሳሌ ኢብኑ ኢስሓቅ፣ ኢብኑ ሂሻም፣ ዋቂዲ፣ ኢብኑ ሰዕድ፣ በላዙሪይ፣ ጦበሪ፣ ሱሃይሊይ፣ ... አንዳቸውም መውሊድን አላከበሩም። ጉዳዩን ስለማያውቁት? ወይስ ስለማይወዷቸው?
10- እንዲሁም ቀደም ብለው የነብዩን ﷺ ሸማኢሎች የከተቡ እንደ ቲርሚዚይ፣ አቡ ኑዐይም አልአስበሃኒ፣ ቃዲ ዒያድ፣ በይሀቂ፣ ወዘተ . አንዳቸውም መውሊድን አላከበሩም።
ይሄ ሁሉ እልፍ አእላፍ ዑለማእ ብዙሃን ሳይሆን የትኛው ዝርዝር ነው ብዙሃን የሚሆነው? የሰለፎቹን ኢጅማዕ በመጣል ከ7ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ የመጡ አካላትን እየዘረዘሩ "ብዙ ነን" የሚል የህፃናት እንቁልልጭ ውስጥ መግባት ሞኝነት ነው። የምትጠቅሷቸው ሁሉም ቢደመሩ ከሶሐባ ትውልድ ጋር የሚነፃፀር የላቸውም።
[ለ]፦ የምትዘረዝሯቸው ዓሊሞች ብዙሃን አይደሉም እንጂ ቢሆኑስ?
ከመቼ ጀምሮ ነው የቁጥር ብዛት መለኪያ የሆነው? እነ ሐሰን ታጁ፣ ኣደም ሙሐመድ እና ኢስሓቅ እሸቱ ያሉ ደፋሮች ከሰለፍ እስከ ኸለፍ ያለፉ ዑለማዎችን ረጋግጠው ለዘፈን ጥብቅና ሲቆሙ የብዙሃን ዑለማእ ተግሳፅ አልገታቸውም። ለመውሊድ የሚዘረዝሯቸው እንዳለ ሙዚቃን ያወግዛሉ። ቢሆንም ደንገጥ እንኳን አይሉም። እነዚህ የዘፈን ጠበቆዎች ደጋፊ ዓሊሞች ጭምር ቢድዐነቱን ለሚመሰክሩበት የመውሊድ ጉዳይ ግን ከሀሰተኛ "ብዙሃን" ጀርባ ያደፍጣሉ። ሁለቱም ቦታ ላይ ሚዛናቸው ስሜታቸው ነው። እንጂ ለማስረጃም ለብዙሃንም ደንታ ያላቸው አይደሉም። በተረፈ የዲን ጉዳይ በወሕይ እንጂ እንደ ፓርላማ በእጅ ብልጫ የሚወሰንበት አይደለም። አላህ እንዲህ ይላል:-
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
{ فَإِن تَنَـٰزَعۡتُمۡ فِی شَیۡءࣲ فَرُدُّوهُ إِلَى ٱللَّهِ وَٱلرَّسُولِ إِن كُنتُمۡ تُؤۡمِنُونَ بِٱللَّهِ وَٱلۡیَوۡمِ ٱلۡـَٔاخِرِۚ }
"በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ፣ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ከሆናችሁ (የተከራከራችሁበትን ነገር) ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት።" [አኒሳእ፡ 59]
መውሊድን ወደ ቁርኣንና ሐዲሥ ስንመልሰው አንድም መሰረት የለውም። ነገር ግን አይናቸውን በጨው አጥበው ሰለፎቹ የማያውቁትን የፈጠራ ትርጉም ይሰጣሉ። የሸሪዐ ማስረጃ ውስጥ ከሌለ ደግሞ ቢድዐ ነው ማለት ነው። ቢድዐ ደግሞ የፈለገ ቢያሽሞነሙኑት ጥመት ነው። ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላሉ፦
من ابتَدَعَ في الإسلامِ بِدعةً يَراها حَسنةً فقد زَعَمَ أنَّ مُحَمَّدًا خانَ الرِّسالةَ! لأنَّ اللهَ يَقولُ: الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ، فما لم يَكُن يومَئِذٍ دينًا فلا يَكونُ اليَومَ دينًا
“በኢስላም ውስጥ አዲስ ነገር (ቢድዐ) ፈጥሮ መልካም ነው ብሎ ያሰበ ሰው፣ በእርግጥ ሙሐመድ መልእክታቸውን አጉድለዋል ብሎ ሞግቷል። ምክንያቱም አላህ፡ ‘ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለእናንተ ሞላሁላችሁ’ ብሏልና። ስለዚህ በዚያን ጊዜ ሃይማኖት ያልነበረ ነገር፣ ዛሬ ሃይማኖት ሊሆን አይችልም።” [ዳሪሚ፡ 141]
መውሊድ ያኔ ዲን አልነበረም። ስለዚህ ዛሬ የዲን ክፍል ሊሆን አይችልም። ደግሞም ኋላ የመጡ ዓሊሞች ንግግር በተለየ ገላጋይ ዳኛ የሚሆንበት አመክንዮ የለም። የፈቃጆቹ ወሕይ፣ የከልካዮቹ ረእይ የሚሆንበት ሁኔታ የለም። አሁንም ኢማሙ ማሊክ ረሒመሁላህ “ከአላህ መልእክተኛ በኋላ ንግግሩ የሚያዝለትና የሚመለስበት ያልሆነ አንድም የለም” ይላሉ። [ጃሚዑ በያኒል ዒልሚ ወፈድሊሂ፡ 2/91]
[ሐ]፦ የፈቃጅ ዝርዝራቸው ራሱ ጤነኛ አይደለም!
* ከፊሎቹ ሶሐቦችን ጨምሮ እንደ ኢማሙ ማሊክ ያሉ ቀደምት አኢማዎችን በመሳደብ የሚታወቁ እንደ ከውሠሪ ያሉ ሙ ^ጅ ^ ሪም ጀ -ህ ^ሚዮች ናቸው። እነዚህን ማን ከቁም ነገር ይቆጥራል?! (ይህንንና ተከታዮቹን ነጥቦች እመለስባቸዋለሁ ኢንሻአለህ።)
* ከፊሎቹ ከመውሊድ በከፋ የአላህን ሲፋት ማስተባበል፣ ኢርጃእ፣ በቀደር ጉዳይ ላይ ጀብር፣ የመሳሰሉ ጥፋቶች ያሉባቸው አሻዒራዎች ናቸው። ካሉባቸው ከባባድ የዐቂዳ ችግሮች አንፃር መውሊድ ቀላሉ ነው ሊባል ይችላል። ልክ የ0ቂዳ ጥፋቶቻቸውን እንደማንቀበለው ቢደዐ የሚደግፉ ንግግሮቻቸውንም አሽቀንጥረን እንጥላለን። የቁርኣንና የሱናን ዟሂር መልእክት መውሰድ የኩ ^ f ^ር መሰረት ነው የሚሉ እንዲሁም ቁርኣን በሐቂቃ የአላህ ንግግር አይደለም የሚሉ አሻዒራዎች ጠሞ አጥ ^ማሚዎች ናቸው!
* ከፊሎቹ ለሙታን አምልኮ የሚሟገቱ፣ ኢብኑ ተይሚያንና ኢብኑል ቀዪምን ከኢስላም በማስወጣትና በመዝለፍ የሚታወቁ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዑለማኦች ያወገዙትን ኢብኑ ዐረቢና መሰሎቹን ታላላቅ የአላህ ወሊዮች ናቸው የሚሉ አፈን ^ ጋጮች ናቸው።
* ከፊሎቹ እንደ ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ከሢር ያሉ በስማቸው የተቀጠፈባቸው እንጂ የመውሊድ ድግስን ለመደገፋቸው ማስረጃ የማይቀርብባቸው ናቸው።
* ከፊሎቹ ቢድዐነቱን አስረግጠው የደገፉ ሲሆኑ እንደ ጭፈራ፣ የሴትና ወንድ ቅልቅል፣ ወዘተ ጥፋት ካለበት እንደማይደግፉ በግልፅ የተናገሩ ከመሆናቸው ጋር ነው ዛሬ ላለው ነውረኛ የመውሊድ አከባበር በስማቸው የሚነግዱባቸው።
ስለዚህ የነዚህ አካላት የመውሊድ ደጋፊዎች ዝርዝር እንዲሁ ቢከፍቱት ተልባ ነው። ከቁም ነገር የማይቆጠር። በመጨረሻም በታላቁ ኢማም አውዛዒይ አደራ ፅሁፌን እቋጫለሁ። እንዲህ ነበር ያሉት፦
اصبِرْ نَفسَكَ على السُّنَّة، وقِفْ حَيثُ وقَفَ القَومُ، وقُلْ بما قالوا، وكُفَّ عَمَّا كَفُّوا عنه، واسلُكْ سَبيلَ سَلَفِك الصَّالِحِ؛ فإنَّه يَسَعُكَ ما وَسِعَهم
"ራስህን በሱና ላይ አፅና። ሰዎቹ (ሶሐቦቹ) ከቆሙበት ቁም። እነሱ ያሉትን በል። ከታቀቡት ነገር ታቀብ። የደጋግ ቀደምቶችህን መንገድ ተጓዝ። ለነሱ የበቃቸው ይበቃሀልና።" [ሒልያ፡ 6/144]
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 12/1447]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
"በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ፣ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ከሆናችሁ (የተከራከራችሁበትን ነገር) ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት።" [አኒሳእ፡ 59]
መውሊድን ወደ ቁርኣንና ሐዲሥ ስንመልሰው አንድም መሰረት የለውም። ነገር ግን አይናቸውን በጨው አጥበው ሰለፎቹ የማያውቁትን የፈጠራ ትርጉም ይሰጣሉ። የሸሪዐ ማስረጃ ውስጥ ከሌለ ደግሞ ቢድዐ ነው ማለት ነው። ቢድዐ ደግሞ የፈለገ ቢያሽሞነሙኑት ጥመት ነው። ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላሉ፦
من ابتَدَعَ في الإسلامِ بِدعةً يَراها حَسنةً فقد زَعَمَ أنَّ مُحَمَّدًا خانَ الرِّسالةَ! لأنَّ اللهَ يَقولُ: الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ، فما لم يَكُن يومَئِذٍ دينًا فلا يَكونُ اليَومَ دينًا
“በኢስላም ውስጥ አዲስ ነገር (ቢድዐ) ፈጥሮ መልካም ነው ብሎ ያሰበ ሰው፣ በእርግጥ ሙሐመድ መልእክታቸውን አጉድለዋል ብሎ ሞግቷል። ምክንያቱም አላህ፡ ‘ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለእናንተ ሞላሁላችሁ’ ብሏልና። ስለዚህ በዚያን ጊዜ ሃይማኖት ያልነበረ ነገር፣ ዛሬ ሃይማኖት ሊሆን አይችልም።” [ዳሪሚ፡ 141]
መውሊድ ያኔ ዲን አልነበረም። ስለዚህ ዛሬ የዲን ክፍል ሊሆን አይችልም። ደግሞም ኋላ የመጡ ዓሊሞች ንግግር በተለየ ገላጋይ ዳኛ የሚሆንበት አመክንዮ የለም። የፈቃጆቹ ወሕይ፣ የከልካዮቹ ረእይ የሚሆንበት ሁኔታ የለም። አሁንም ኢማሙ ማሊክ ረሒመሁላህ “ከአላህ መልእክተኛ በኋላ ንግግሩ የሚያዝለትና የሚመለስበት ያልሆነ አንድም የለም” ይላሉ። [ጃሚዑ በያኒል ዒልሚ ወፈድሊሂ፡ 2/91]
[ሐ]፦ የፈቃጅ ዝርዝራቸው ራሱ ጤነኛ አይደለም!
* ከፊሎቹ ሶሐቦችን ጨምሮ እንደ ኢማሙ ማሊክ ያሉ ቀደምት አኢማዎችን በመሳደብ የሚታወቁ እንደ ከውሠሪ ያሉ ሙ ^ጅ ^ ሪም ጀ -ህ ^ሚዮች ናቸው። እነዚህን ማን ከቁም ነገር ይቆጥራል?! (ይህንንና ተከታዮቹን ነጥቦች እመለስባቸዋለሁ ኢንሻአለህ።)
* ከፊሎቹ ከመውሊድ በከፋ የአላህን ሲፋት ማስተባበል፣ ኢርጃእ፣ በቀደር ጉዳይ ላይ ጀብር፣ የመሳሰሉ ጥፋቶች ያሉባቸው አሻዒራዎች ናቸው። ካሉባቸው ከባባድ የዐቂዳ ችግሮች አንፃር መውሊድ ቀላሉ ነው ሊባል ይችላል። ልክ የ0ቂዳ ጥፋቶቻቸውን እንደማንቀበለው ቢደዐ የሚደግፉ ንግግሮቻቸውንም አሽቀንጥረን እንጥላለን። የቁርኣንና የሱናን ዟሂር መልእክት መውሰድ የኩ ^ f ^ር መሰረት ነው የሚሉ እንዲሁም ቁርኣን በሐቂቃ የአላህ ንግግር አይደለም የሚሉ አሻዒራዎች ጠሞ አጥ ^ማሚዎች ናቸው!
* ከፊሎቹ ለሙታን አምልኮ የሚሟገቱ፣ ኢብኑ ተይሚያንና ኢብኑል ቀዪምን ከኢስላም በማስወጣትና በመዝለፍ የሚታወቁ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዑለማኦች ያወገዙትን ኢብኑ ዐረቢና መሰሎቹን ታላላቅ የአላህ ወሊዮች ናቸው የሚሉ አፈን ^ ጋጮች ናቸው።
* ከፊሎቹ እንደ ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ከሢር ያሉ በስማቸው የተቀጠፈባቸው እንጂ የመውሊድ ድግስን ለመደገፋቸው ማስረጃ የማይቀርብባቸው ናቸው።
* ከፊሎቹ ቢድዐነቱን አስረግጠው የደገፉ ሲሆኑ እንደ ጭፈራ፣ የሴትና ወንድ ቅልቅል፣ ወዘተ ጥፋት ካለበት እንደማይደግፉ በግልፅ የተናገሩ ከመሆናቸው ጋር ነው ዛሬ ላለው ነውረኛ የመውሊድ አከባበር በስማቸው የሚነግዱባቸው።
ስለዚህ የነዚህ አካላት የመውሊድ ደጋፊዎች ዝርዝር እንዲሁ ቢከፍቱት ተልባ ነው። ከቁም ነገር የማይቆጠር። በመጨረሻም በታላቁ ኢማም አውዛዒይ አደራ ፅሁፌን እቋጫለሁ። እንዲህ ነበር ያሉት፦
اصبِرْ نَفسَكَ على السُّنَّة، وقِفْ حَيثُ وقَفَ القَومُ، وقُلْ بما قالوا، وكُفَّ عَمَّا كَفُّوا عنه، واسلُكْ سَبيلَ سَلَفِك الصَّالِحِ؛ فإنَّه يَسَعُكَ ما وَسِعَهم
"ራስህን በሱና ላይ አፅና። ሰዎቹ (ሶሐቦቹ) ከቆሙበት ቁም። እነሱ ያሉትን በል። ከታቀቡት ነገር ታቀብ። የደጋግ ቀደምቶችህን መንገድ ተጓዝ። ለነሱ የበቃቸው ይበቃሀልና።" [ሒልያ፡ 6/144]
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 12/1447]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ዶሪሖችን ማስወገድ
~
የባሰ ፊትና የማይከሰት ከሆነ ከአላህ ውጭ የሚመለኩ ቀብር ላይ የተገነቡ ቤቶችን፣ ግንባታዎችን፣ ዛፎችን፣ ... አፈራርሶ ማስወገድ ይገባል። ይሄ ነው የነብያት ሱና። ይሄ ነው የነብዩ'ላህ ኢብራሂም ተግባር። ለሙሽ ^ሪኮች ምን ነበር ያሏቸው?
{ وَتَٱللَّهِ لَأَكِیدَنَّ أَصۡنَـٰمَكُم بَعۡدَ أَن تُوَلُّوا۟ مُدۡبِرِینَ (57)}
እነሱ ዞር ሲሉ ሊያፈራርሱላቸው በመሀላ አስረግጠው ነገሯቸው። አውርተው አልቀሩም። ይሄውና፡
فَجَعَلَهُمۡ جُذَ ٰذًا إِلَّا كَبِیرࣰا لَّهُمۡ لَعَلَّهُمۡ إِلَیۡهِ یَرۡجِعُونَ (58)}
"(ዘወር ሲሉ) ስብርባሪዎች አደረጋቸው፡፡ ለእነሱ የሆነ አንድ ታላቅ (ጣዖት) ብቻ ሲቀር ወደርሱ ይመለሱ ዘንድ (እርሱን ተወው)፡፡" [አልአንቢያእ፡ 57 - 58]
የነብያችን ﷺ አስተምሮትም እንዲሁ ነበር። የሰለፎቻችንም ተግባር እንዲሁ ነበር። አቡል ሀያጅ አል አሰዲይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
قَالَ لِي عَلِيُّ بْنُ أَبِي طَالِبٍ : أَلَا أَبْعَثُكَ عَلَى مَا بَعَثَنِي عَلَيْهِ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ ؟ ( ... وَلَا قَبْرًا مُشْرِفًا إِلَّا سَوَّيْتَهُ)
"0ሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ እንዲህ ብሎኛል፦ 'የአላህ መልእክተኛ ﷺ በላኩብኝ አምሳያ አልክህምን? { ...ከፍ ያለ ቀብር አይተህ (ከሌሎች ቀብሮች ጋር እኩል) ሳታስተካክለው እንዳታልፍ!}' " [ሙስሊም፡ 969]
ባይሆን በደመ ነፍስ መወሰን አይገባም። እርምጃ ከመውሰድ በፊት ጉዳዩ ምን ሊያስከትል እንደሚችል በደንብ ማጤን ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
የባሰ ፊትና የማይከሰት ከሆነ ከአላህ ውጭ የሚመለኩ ቀብር ላይ የተገነቡ ቤቶችን፣ ግንባታዎችን፣ ዛፎችን፣ ... አፈራርሶ ማስወገድ ይገባል። ይሄ ነው የነብያት ሱና። ይሄ ነው የነብዩ'ላህ ኢብራሂም ተግባር። ለሙሽ ^ሪኮች ምን ነበር ያሏቸው?
{ وَتَٱللَّهِ لَأَكِیدَنَّ أَصۡنَـٰمَكُم بَعۡدَ أَن تُوَلُّوا۟ مُدۡبِرِینَ (57)}
እነሱ ዞር ሲሉ ሊያፈራርሱላቸው በመሀላ አስረግጠው ነገሯቸው። አውርተው አልቀሩም። ይሄውና፡
فَجَعَلَهُمۡ جُذَ ٰذًا إِلَّا كَبِیرࣰا لَّهُمۡ لَعَلَّهُمۡ إِلَیۡهِ یَرۡجِعُونَ (58)}
"(ዘወር ሲሉ) ስብርባሪዎች አደረጋቸው፡፡ ለእነሱ የሆነ አንድ ታላቅ (ጣዖት) ብቻ ሲቀር ወደርሱ ይመለሱ ዘንድ (እርሱን ተወው)፡፡" [አልአንቢያእ፡ 57 - 58]
የነብያችን ﷺ አስተምሮትም እንዲሁ ነበር። የሰለፎቻችንም ተግባር እንዲሁ ነበር። አቡል ሀያጅ አል አሰዲይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
قَالَ لِي عَلِيُّ بْنُ أَبِي طَالِبٍ : أَلَا أَبْعَثُكَ عَلَى مَا بَعَثَنِي عَلَيْهِ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ ؟ ( ... وَلَا قَبْرًا مُشْرِفًا إِلَّا سَوَّيْتَهُ)
"0ሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ እንዲህ ብሎኛል፦ 'የአላህ መልእክተኛ ﷺ በላኩብኝ አምሳያ አልክህምን? { ...ከፍ ያለ ቀብር አይተህ (ከሌሎች ቀብሮች ጋር እኩል) ሳታስተካክለው እንዳታልፍ!}' " [ሙስሊም፡ 969]
ባይሆን በደመ ነፍስ መወሰን አይገባም። እርምጃ ከመውሰድ በፊት ጉዳዩ ምን ሊያስከትል እንደሚችል በደንብ ማጤን ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ተምረህ ሞተሃል!
~
ተምረህ ነው ለካ
ጤናን ሚያቃውስ - ቅጠል የምትበላ
ቢድዐ 'ሚያማልህ - ሱናን የምትጠላ
ተምረህ ነው ለካ
ሙታን የምታመልክ ሺርክ 'ምታቦካ
ከማስረጃ ያልቅ አጉል ፍልስፍና ያደረገህ ነካ
ተምረህ ነው ለካ
ተውሒድ ሚያልብህ ሱና 'ሚወብቅህ
ተምረህ ነው ለካ
ሺርክ 'ሚጣፍጥህ መረጃ የሚያንቅህ
ተምረህ ነው ለካ
ደሊል 'ሚከብድህ - ሐቅ 'ሚያስጨንቅህ
ተምረህ ነው ለካ
ወንጀል እንደ ጀብዱ ውጭ የምታሰጣ
ኹራፋ ምታሳድ፣ ባዳ 'ምትሳለም የሆንከው ፈጣጣ
ተምረህ ነው ለካ እምነትና ባህል የምታደባልቅ
ተምረህ ነው ለካ
ራስህን በከንቱ፣ አጉል 'ምትቆልል፣ ሌሎችን የምትንቅ
ተምረሃል ለካ!
መማርህ ነው ለካ!
አረቄ ሆኖብህ የሚያወላግድህ
ጉራ የሚንጥህ ፅንፍ 'ሚያስረግድህ
ተምረህ ነው አሉ
ራስህ ፀንፈህ፣ ሁሌ ባንድ አቅጣጫ፣ በፅንፍ የምትከሰው
የራስህን ጀሌ፣ እሽሩሩ እያልከው፣ ሌላውን ከማዶ የምታራክሰው
ቢመርህም ዋጠው!
መማር ይጥቀም እንጂ፣ አይሆንም ዋስትና፣ ለማያስተውሉ
ጠፍጥፈው ለሰሩት፣ ግዑዝ ቁስ አም ^ላኪ፣ ስንት ሊቆች አሉ?
ለላም የሚሰ ^ግዱ፣ ኮምፓስ ጠፍቶባቸው፣ የሚን ቀ ዋለሉ።
ተምረህ ሞተሃልi ድንቄም መማርii
l
ማስታወሻነቱ መማራቸው አረቄ ሆኖባቸው ጥንብዝ፣ ጥብርር ላደረጋቸው፣ እኛ ያላማሰልነው ወጥ አይጣፍጥም ለሚሉ ሁሉ ይሁን።
* ምስሉ ላይ ያለው የአሳ ዝርያ በአማርኛ እንፉሌ በእንግሊዝኛው Blowfish ይባላል። ስያሜው የመጣው ባላንጣዎቹን ለማስፈራራት ራሱን እንደ ፊኛ በአየር ወይም በውሃ ወጥሮ ከትክክለኛ ቁመናው የበለጠ ግዙፍ መስሎ ለመታየት የሚሞክር በመሆኑ ነው። ውስጡ ግን ባዶ ነው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 13/1447)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ተምረህ ነው ለካ
ጤናን ሚያቃውስ - ቅጠል የምትበላ
ቢድዐ 'ሚያማልህ - ሱናን የምትጠላ
ተምረህ ነው ለካ
ሙታን የምታመልክ ሺርክ 'ምታቦካ
ከማስረጃ ያልቅ አጉል ፍልስፍና ያደረገህ ነካ
ተምረህ ነው ለካ
ተውሒድ ሚያልብህ ሱና 'ሚወብቅህ
ተምረህ ነው ለካ
ሺርክ 'ሚጣፍጥህ መረጃ የሚያንቅህ
ተምረህ ነው ለካ
ደሊል 'ሚከብድህ - ሐቅ 'ሚያስጨንቅህ
ተምረህ ነው ለካ
ወንጀል እንደ ጀብዱ ውጭ የምታሰጣ
ኹራፋ ምታሳድ፣ ባዳ 'ምትሳለም የሆንከው ፈጣጣ
ተምረህ ነው ለካ እምነትና ባህል የምታደባልቅ
ተምረህ ነው ለካ
ራስህን በከንቱ፣ አጉል 'ምትቆልል፣ ሌሎችን የምትንቅ
ተምረሃል ለካ!
መማርህ ነው ለካ!
አረቄ ሆኖብህ የሚያወላግድህ
ጉራ የሚንጥህ ፅንፍ 'ሚያስረግድህ
ተምረህ ነው አሉ
ራስህ ፀንፈህ፣ ሁሌ ባንድ አቅጣጫ፣ በፅንፍ የምትከሰው
የራስህን ጀሌ፣ እሽሩሩ እያልከው፣ ሌላውን ከማዶ የምታራክሰው
ቢመርህም ዋጠው!
መማር ይጥቀም እንጂ፣ አይሆንም ዋስትና፣ ለማያስተውሉ
ጠፍጥፈው ለሰሩት፣ ግዑዝ ቁስ አም ^ላኪ፣ ስንት ሊቆች አሉ?
ለላም የሚሰ ^ግዱ፣ ኮምፓስ ጠፍቶባቸው፣ የሚን ቀ ዋለሉ።
ተምረህ ሞተሃልi ድንቄም መማርii
l
ማስታወሻነቱ መማራቸው አረቄ ሆኖባቸው ጥንብዝ፣ ጥብርር ላደረጋቸው፣ እኛ ያላማሰልነው ወጥ አይጣፍጥም ለሚሉ ሁሉ ይሁን።
* ምስሉ ላይ ያለው የአሳ ዝርያ በአማርኛ እንፉሌ በእንግሊዝኛው Blowfish ይባላል። ስያሜው የመጣው ባላንጣዎቹን ለማስፈራራት ራሱን እንደ ፊኛ በአየር ወይም በውሃ ወጥሮ ከትክክለኛ ቁመናው የበለጠ ግዙፍ መስሎ ለመታየት የሚሞክር በመሆኑ ነው። ውስጡ ግን ባዶ ነው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 13/1447)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور