📢 አስደሳች ዜና 🆕
⭐️ታላቅ የቁርአን ሒፍዝ ምርቃት ፕሮግራም⭐️
⏩መርከዝ አቡ ሙሳ አል አሽዐሪ የቁርአን ሒፍዝ ማእከል በበጋና በክረምት ሲያስተምራቸው የቆዩ ተማሪዎችን እሁድ ነሀሴ 25/20117 ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በደማቅ ፕሮግራም እንደሚያስመርቅ ስናበስረዎ በታላቅ ደስታ ነው ።
🔈በፕሮግራሙም ላይ የተላያዩ መሻዪኾችና ኡስታዞች የሙሐደራ ግብዣ ይኖራቸዋል ።
በመሆኑም እርሶ የፕሮግራሙ ተካፋይ እንዲሆኑ በክብር ተጋብዘዋል ።
🗂አድራሻ: አጠና ተራ እፎይታ የገቢያ ማእከል አዳራሽ
❗️ማሳሰቢያ: የ አዳራሽ መግቢያ ምንም አይነት ክፍያ ስለሌለው ቦታ ሳይሞላባቹህ ቀድማቹህ እንድትገኙ ሰንል እናሳስባለን .
☹️😭🙁🙁🙁🙁🙁🙁
✉️ የመርከዙ የቴሌግራም አድራሻ
⤵️
https://www.tgoop.com/merkezabumussa1
https://www.tgoop.com/merkezabumussa1
⭐️ታላቅ የቁርአን ሒፍዝ ምርቃት ፕሮግራም⭐️
⏩መርከዝ አቡ ሙሳ አል አሽዐሪ የቁርአን ሒፍዝ ማእከል በበጋና በክረምት ሲያስተምራቸው የቆዩ ተማሪዎችን እሁድ ነሀሴ 25/20117 ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በደማቅ ፕሮግራም እንደሚያስመርቅ ስናበስረዎ በታላቅ ደስታ ነው ።
🔈በፕሮግራሙም ላይ የተላያዩ መሻዪኾችና ኡስታዞች የሙሐደራ ግብዣ ይኖራቸዋል ።
በመሆኑም እርሶ የፕሮግራሙ ተካፋይ እንዲሆኑ በክብር ተጋብዘዋል ።
🗂አድራሻ: አጠና ተራ እፎይታ የገቢያ ማእከል አዳራሽ
❗️ማሳሰቢያ: የ አዳራሽ መግቢያ ምንም አይነት ክፍያ ስለሌለው ቦታ ሳይሞላባቹህ ቀድማቹህ እንድትገኙ ሰንል እናሳስባለን .
☹️😭🙁🙁🙁🙁🙁🙁
✉️ የመርከዙ የቴሌግራም አድራሻ
⤵️
https://www.tgoop.com/merkezabumussa1
https://www.tgoop.com/merkezabumussa1
የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
“ሶሐቦቼን የተሳደበ አላህ ከእዝነቱ ያርቀው” ብለዋልና። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 5111]
=
ቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
“ሶሐቦቼን የተሳደበ አላህ ከእዝነቱ ያርቀው” ብለዋልና። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 5111]
=
ቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
የመውሊድ አደጋዎች
~
ከመውሊድ ቢድዐ የምናስጠነቅቀው መነዛነዝ ስለሚያምረን፣ በአጉል ቡድንተኝነት ተነሳስተን ወይም በሌላ ምክንያት ሳይሆን እነዚህ አደጋዎች ስላሉበት ወገናችን እንዲነቃ በማሰብ ነው።
1. መውሊድን ማክበር የነብዩን ﷺ እና የምርጥ ትውልዶቻቸውን ፈለግ መጣስ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፡-
(وَمَن يُشَاقِقِ ٱلرَّسُولَ مِنۢ بَعۡدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ ٱلۡهُدَىٰ وَيَتَّبِعۡ غَيۡرَ سَبِيلِ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ نُوَلِّهِۦ مَا تَوَلَّىٰ وَنُصۡلِهِۦ جَهَنَّمَۖ وَسَآءَتۡ مَصِيرًا)
{ቅኑም መንገድ ከተገለፀለት በኋላ መልእክተኛውን የሚጨቃጨቅና ከአማኞቹም መንገድ ሌላ የሆነን የሚከተል ሰው በተሾመበት ላይ እንሾመዋለን። ጀሀነምንም እንከተዋለን። መጨረሻይቱም ከፋች።} [አኒሳእ፡ 115]
2. መውሊድ “ዒባዳ ነው” ብሎ የሚያስብ ሰው “ዲኑ ሙሉእ ነው” የሚለውን ጌታ እያስተባበለ፣ ነብዩ ﷺ አደራቸውን አልተወጡም እያለ እየሞገተ ነው። ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላሉ፡- “በኢስላም ውስጥ መልካም ናት ብሎ የሚያስባትን ቢድዐ የፈጠረ ሰው ሙሐመድ ﷺ ተልእኳቸው ላይ ሸፍጥ ሰርተዋል ብሎ እየሞገተ ነው። ምክንያቱም አላህ {ዛሬ ለናንተ ሃይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ} ብሏልና።” [ዳሪሚይ፡ 141]
ነብዩ ﷺ በመሰናበቻው ሐጅ ላይ “አጥብቃችሁ ከያዛችሁት ከሱ በኋላ የማትጠሙበትን ነገር በርግጥም ትቼላችኋለሁ፣ የአላህን ኪታብ። እናንተ ስለኔ ትጠየቃላችሁና ምንድን ነው የምትሉት?” ሲሉ ሶሐቦችም “አንተ በርግጥም እንዳደረስክ፣ አደራህን እንደተወጣህና እንደመከርክ ነው የምንመሰክረው” አሉ። ይህኔ አመልካች ጣታቸውን ወደ ሰማይ እያነሱ ከዚያም ወደ ሰዎቹ እየጠቆሙ “ጌታዬ ሆይ! መስክር” አሉ ሶስት ጊዜ በመደጋገም። [ሙስሊም፡ 3009]
3. የመውሊድ ቢድዐን የሚፈፅም ሰው የማይመነዳበትን ከንቱ ልፋት እየለፋ ነው ያለው። ነብዩ ﷺ “የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ እሱ (ስራው) ተመላሽ (ውድቅ) ነው” ብለዋል። [ቡኻሪ፡ 3/69] [ሙስሊም፡ 4590]
4. ይህን ቢድዐ የሚፈፅም ሰው ጥመት ላይ ነው። ነብዩ ﷺ “መጤ የሆኑ ነገሮችን ተጠንቀቁ። መጤ ፈሊጥ ሁሉ ፈጠራ ነው። ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው። ጥመት ሁሉ ወደ እሳት ነው” ብለዋል። [ኢርዋኡል ገሊል፡ 608]
5. መውሊድ የሚያከብርና እንዲከበር የሚሟገት ሰው ከሸሪዐዊ ነፀብራቆች ውስጥ አንዱ የሆነውን ነብዩን ﷺ የመውደድ ፅንሰ-ሀሳብን እያዛባ ነው። እሳቸውን ስለመውደድ፣ ስለማክበርና ስለመከተል የሚያትቱ ብዙ የቁርኣን አያዎችን፣ ሐዲሦችንና የሰለፎች ንግግሮችን ቀደምቶቻችን ባልተረዱት መልኩ በመተንተን እነሱ ላልፈፀሙት ቢድዐ ማስረጃ በማድረግ ነብዩን ﷺ መውደድ ማለት መውሊድን ማክበር፣ በሶለዋት ስም መጨፈር ተደርጎ እንዲሳል ተደርጓል። ይህ ምን ያክል እሳቸውን የመውደድ ሸሪዐዊ ነፀብራቅ እየተዛባ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።
6. መውሊድን ማክበር በአንድምታ ቀደምቶቻችንን በነገር መውጋት አለበት። ሶሐቦችና ተከታዮቻቸው ከኛ በበለጠ ነብዩን ﷺ የሚወዱ ከመሆናቸው ጋር መውሊድን አላከበሩም። ዛሬ መውሊድን የሚያከብረው የነብዩ ﷺ ወዳጅ፣ የሚቃወመው ደግሞ የሳቸው ጠላት ተደርጎ እየተሳለ ነው። በነዚህ ሰዎች አረዳድ መሰረት ቀደምት ሰለፎች ነብዩን ﷺ “አይወዱም ነበር” ማለት ነው። ይሄ አደገኛ ነገር ነው። እነዚያ ለነብዩ ﷺ ሲሉ አጥንታቸውን የከሰከሱ፣ ደማቸውን ያፈሰሱ፣ ቤታቸውን ያፈረሱ፣ ገንዘባቸውን የለገሱ ሶሐቦች መውሊድን ስላላከበሩ እሳቸውን “አይወዱም” ቢባል ማን ያምናል?!
7. መውሊድ በአብዛኛው ከባባድ የሆኑ ሺርኮች ይፈፀሙበታል። ቀብር ጦዋፍ የሚያደርጉ፣ ለቀብር ሱጁድ የሚወርዱ፣ ለቀብር የሚሳሉ፣ የቀብር አፈር ለበረካና ለፈውስ የሚወስዱ፣ በጥብጠው የሚጠጡ፣ ስለት የሚወስዱ፣... አሉ። መንዙማዎቹ እራሳቸው በሺርክ የታጨቁ ናቸው። {አላህ በርሱ ማጋራትን በፍፁም አይምርም።} [አኒሳእ፡ 48]
8. መውሊድ ከክርስቲያኖች ጋር መመሳሰል አለበት። የነብይን ልደት በዓል አድርጎ መያዝ ክርስቲያናዊ ሱና ነው። ክርስቲያኖች ገናን የሚያከብሩት የዒሳ ልደት ነው በሚል እንደሆነ የሚታወቅ ነው። ነብዩ ﷺ “ከሆኑ ሰዎች ጋር የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል። [ኢርዋኡል ገሊል፡ 1269]
9. መውሊድ ውስጥ ብዙ አይነት ድንበር ማለፍ አለ። በነብዩ ﷺ ላይ፣ በሌሎችም ሙታኖች ላይ ድንበር ማለፍ ይፈፀማል። ይሄ በእለቱ በሚነበቡ ግጥሞች፣ መንዙማዎችና ዶሪሖች ላይ በሰፊው የሚንፀባረቅ ነው። ነብዩ ﷺ ግን “ክርስቲያኖች የመርየምን ልጅ ዒሳን ድንበር አልፈው እንዳወደሱት አታወድሱኝ” ይላሉ። [ጋየቱል መራም፡ 123]
አንዳንዶች በድፍረት የመውሊድ ሌሊት ከለይለተል ቀድር የበለጠ ነው ብለው እስከሚሞግቱ ደርሰዋል። [አልመዋሂቡ ለዱንያህ፡ 1/135] ሱብሓነላህ! ይህ ሁሉ የሚባለው እንግዲህ የተወለዱበት ቀን አወዛጋቢ ከመሆኑ ጋር ነው። ይህ ሁሉ የሚሆነው የተወለዱት በሌሊት እንደሆነ የሚጠቁም መረጃ በሌለበት ነው። በዚያ ላይ የተወለዱበት ጊዜ ከ 14 ከፍለ-ዘመናት በፊት ያለፈ እንጂ እንደ ለይለተል ቀድር በያመቱ የሚመላለስ አይደለም። ዐልዩል ቃሪ (1014 ዓ. ሂ.) “(የለይለተል ቀድር) በላጭነት ዒባዳ በሷ ውስጥ በላጭ ስለሆነ እንጂ በሌላ ምክንያት አይደለም። ይህም {መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺህ ወር በላጭ ናት} በሚለው ቁርኣናዊ ምስክርነት ነው። ለመውሊዳቸው ግን ይህቺ ብልጫ ከቁርኣንም፣ ከሱናም፣ ከሙስሊሙ ህዝብ ዑለማዎች ከአንድም አትታወቅም!!” ይላሉ። [አልመውሪዱ ረዊይ፡ 97]
10. መውሊድን ከኢስላማዊ በአላት ውስጥ ማካተት ሁለት አመታዊ በዓል ያደረጉልንን ነብይ ትእዛዝ መጣስ ነው። ነብዩ ﷺ መዲና ሲገቡ ነዋሪዎቿ የሚጫወቱባቸው ሁለት ቀናት ነበሯቸው። “ምንድን ናቸው እነዚህ ሁለት ቀናት?” ሲሉ ጠየቁ። “በጃሂሊያው ጊዜ እንጫወትባቸው ነበርን” አሉ። ይህኔ “የላቀው አላህ ከነሱ በላጭ በሆኑ ሁለት ቀናት ተክቶላችኋል። እነሱም የአድሓ ቀን እና የፊጥር ቀን ናቸው” አሉ። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1039]
11. የመውሊድ በዓልን ማክበር ለሌሎች የቢድዐ በዓላት በር መክፈት ነው። የወልዮች ልደት እያሉ በመቃብር ዙሪያ ለሚልከሰከሱ፣ የልጆች አመታዊ ልደት ለሚያከብሩ ሰዎችና ለሌሎችም ምርኩዝ ማቀበል ነው።
12. የመውሊድ ኪታቦችና የመውሊድ ድግሶች በነብዩ ﷺ ስም በሚነገሩ የውሸት ቂሷዎች የታጨቁ ናቸው። “አብዛኛው በመውሊድ ደስኳሪዎች እጅ ያለው ውሸትና ቅጥፈት ነው” ይላሉ መውሊድ ደጋፊ የሆኑት ሰኻዊ። [አልመውሊዱ ረዊይ፡ 32] መልእክተኛው ﷺ ግን “በኔ ላይ ሆን ብሎ የዋሸ ሰው መቀመጫውን ከእሳት ያዘጋጅ” ይላሉ። [ቡኻሪ፡ 1291] [ሙስሊም፡ 5]
13. በመውሊድ የቢድዐ ድግስ ላይ ነብዩ ﷺ “ከጭፈራው ይታደማሉ” የሚል ሰቅጣጭ እምነት አለ። የቅጥፈታቸው ቅጥፈት የመውሊዱ ሌሊት ላይ “ነብዩ መጡ” እያሉ ከተቀመጡበት መነሳታቸው ነው። በነገራችን ላይ ነብዩ ﷺ ከሞቱ በኋላ ቀርቶ በህይወት እያሉ እንኳን ሲመጡ ሶሐቦች አይነሱላቸውም ነበር። [አሶሒሐ፡ 358] ሀይተሚ እንዲህ ይላል፡“የዚህ አምሳያው ብዙዎች የነብዩ ﷺ ልደትና እናታቸው እሳቸውን መውለዷ ሲወሳ የሚያደርጉት መቆም ሲሆን ይህም ምንም አይነት መረጃ ያልመጣበት ቢድዐ ነው።” [አልፈታወል ሐዲሢያህ፡ 58]
~
ከመውሊድ ቢድዐ የምናስጠነቅቀው መነዛነዝ ስለሚያምረን፣ በአጉል ቡድንተኝነት ተነሳስተን ወይም በሌላ ምክንያት ሳይሆን እነዚህ አደጋዎች ስላሉበት ወገናችን እንዲነቃ በማሰብ ነው።
1. መውሊድን ማክበር የነብዩን ﷺ እና የምርጥ ትውልዶቻቸውን ፈለግ መጣስ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፡-
(وَمَن يُشَاقِقِ ٱلرَّسُولَ مِنۢ بَعۡدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ ٱلۡهُدَىٰ وَيَتَّبِعۡ غَيۡرَ سَبِيلِ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ نُوَلِّهِۦ مَا تَوَلَّىٰ وَنُصۡلِهِۦ جَهَنَّمَۖ وَسَآءَتۡ مَصِيرًا)
{ቅኑም መንገድ ከተገለፀለት በኋላ መልእክተኛውን የሚጨቃጨቅና ከአማኞቹም መንገድ ሌላ የሆነን የሚከተል ሰው በተሾመበት ላይ እንሾመዋለን። ጀሀነምንም እንከተዋለን። መጨረሻይቱም ከፋች።} [አኒሳእ፡ 115]
2. መውሊድ “ዒባዳ ነው” ብሎ የሚያስብ ሰው “ዲኑ ሙሉእ ነው” የሚለውን ጌታ እያስተባበለ፣ ነብዩ ﷺ አደራቸውን አልተወጡም እያለ እየሞገተ ነው። ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላሉ፡- “በኢስላም ውስጥ መልካም ናት ብሎ የሚያስባትን ቢድዐ የፈጠረ ሰው ሙሐመድ ﷺ ተልእኳቸው ላይ ሸፍጥ ሰርተዋል ብሎ እየሞገተ ነው። ምክንያቱም አላህ {ዛሬ ለናንተ ሃይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ} ብሏልና።” [ዳሪሚይ፡ 141]
ነብዩ ﷺ በመሰናበቻው ሐጅ ላይ “አጥብቃችሁ ከያዛችሁት ከሱ በኋላ የማትጠሙበትን ነገር በርግጥም ትቼላችኋለሁ፣ የአላህን ኪታብ። እናንተ ስለኔ ትጠየቃላችሁና ምንድን ነው የምትሉት?” ሲሉ ሶሐቦችም “አንተ በርግጥም እንዳደረስክ፣ አደራህን እንደተወጣህና እንደመከርክ ነው የምንመሰክረው” አሉ። ይህኔ አመልካች ጣታቸውን ወደ ሰማይ እያነሱ ከዚያም ወደ ሰዎቹ እየጠቆሙ “ጌታዬ ሆይ! መስክር” አሉ ሶስት ጊዜ በመደጋገም። [ሙስሊም፡ 3009]
3. የመውሊድ ቢድዐን የሚፈፅም ሰው የማይመነዳበትን ከንቱ ልፋት እየለፋ ነው ያለው። ነብዩ ﷺ “የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ እሱ (ስራው) ተመላሽ (ውድቅ) ነው” ብለዋል። [ቡኻሪ፡ 3/69] [ሙስሊም፡ 4590]
4. ይህን ቢድዐ የሚፈፅም ሰው ጥመት ላይ ነው። ነብዩ ﷺ “መጤ የሆኑ ነገሮችን ተጠንቀቁ። መጤ ፈሊጥ ሁሉ ፈጠራ ነው። ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው። ጥመት ሁሉ ወደ እሳት ነው” ብለዋል። [ኢርዋኡል ገሊል፡ 608]
5. መውሊድ የሚያከብርና እንዲከበር የሚሟገት ሰው ከሸሪዐዊ ነፀብራቆች ውስጥ አንዱ የሆነውን ነብዩን ﷺ የመውደድ ፅንሰ-ሀሳብን እያዛባ ነው። እሳቸውን ስለመውደድ፣ ስለማክበርና ስለመከተል የሚያትቱ ብዙ የቁርኣን አያዎችን፣ ሐዲሦችንና የሰለፎች ንግግሮችን ቀደምቶቻችን ባልተረዱት መልኩ በመተንተን እነሱ ላልፈፀሙት ቢድዐ ማስረጃ በማድረግ ነብዩን ﷺ መውደድ ማለት መውሊድን ማክበር፣ በሶለዋት ስም መጨፈር ተደርጎ እንዲሳል ተደርጓል። ይህ ምን ያክል እሳቸውን የመውደድ ሸሪዐዊ ነፀብራቅ እየተዛባ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።
6. መውሊድን ማክበር በአንድምታ ቀደምቶቻችንን በነገር መውጋት አለበት። ሶሐቦችና ተከታዮቻቸው ከኛ በበለጠ ነብዩን ﷺ የሚወዱ ከመሆናቸው ጋር መውሊድን አላከበሩም። ዛሬ መውሊድን የሚያከብረው የነብዩ ﷺ ወዳጅ፣ የሚቃወመው ደግሞ የሳቸው ጠላት ተደርጎ እየተሳለ ነው። በነዚህ ሰዎች አረዳድ መሰረት ቀደምት ሰለፎች ነብዩን ﷺ “አይወዱም ነበር” ማለት ነው። ይሄ አደገኛ ነገር ነው። እነዚያ ለነብዩ ﷺ ሲሉ አጥንታቸውን የከሰከሱ፣ ደማቸውን ያፈሰሱ፣ ቤታቸውን ያፈረሱ፣ ገንዘባቸውን የለገሱ ሶሐቦች መውሊድን ስላላከበሩ እሳቸውን “አይወዱም” ቢባል ማን ያምናል?!
7. መውሊድ በአብዛኛው ከባባድ የሆኑ ሺርኮች ይፈፀሙበታል። ቀብር ጦዋፍ የሚያደርጉ፣ ለቀብር ሱጁድ የሚወርዱ፣ ለቀብር የሚሳሉ፣ የቀብር አፈር ለበረካና ለፈውስ የሚወስዱ፣ በጥብጠው የሚጠጡ፣ ስለት የሚወስዱ፣... አሉ። መንዙማዎቹ እራሳቸው በሺርክ የታጨቁ ናቸው። {አላህ በርሱ ማጋራትን በፍፁም አይምርም።} [አኒሳእ፡ 48]
8. መውሊድ ከክርስቲያኖች ጋር መመሳሰል አለበት። የነብይን ልደት በዓል አድርጎ መያዝ ክርስቲያናዊ ሱና ነው። ክርስቲያኖች ገናን የሚያከብሩት የዒሳ ልደት ነው በሚል እንደሆነ የሚታወቅ ነው። ነብዩ ﷺ “ከሆኑ ሰዎች ጋር የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል። [ኢርዋኡል ገሊል፡ 1269]
9. መውሊድ ውስጥ ብዙ አይነት ድንበር ማለፍ አለ። በነብዩ ﷺ ላይ፣ በሌሎችም ሙታኖች ላይ ድንበር ማለፍ ይፈፀማል። ይሄ በእለቱ በሚነበቡ ግጥሞች፣ መንዙማዎችና ዶሪሖች ላይ በሰፊው የሚንፀባረቅ ነው። ነብዩ ﷺ ግን “ክርስቲያኖች የመርየምን ልጅ ዒሳን ድንበር አልፈው እንዳወደሱት አታወድሱኝ” ይላሉ። [ጋየቱል መራም፡ 123]
አንዳንዶች በድፍረት የመውሊድ ሌሊት ከለይለተል ቀድር የበለጠ ነው ብለው እስከሚሞግቱ ደርሰዋል። [አልመዋሂቡ ለዱንያህ፡ 1/135] ሱብሓነላህ! ይህ ሁሉ የሚባለው እንግዲህ የተወለዱበት ቀን አወዛጋቢ ከመሆኑ ጋር ነው። ይህ ሁሉ የሚሆነው የተወለዱት በሌሊት እንደሆነ የሚጠቁም መረጃ በሌለበት ነው። በዚያ ላይ የተወለዱበት ጊዜ ከ 14 ከፍለ-ዘመናት በፊት ያለፈ እንጂ እንደ ለይለተል ቀድር በያመቱ የሚመላለስ አይደለም። ዐልዩል ቃሪ (1014 ዓ. ሂ.) “(የለይለተል ቀድር) በላጭነት ዒባዳ በሷ ውስጥ በላጭ ስለሆነ እንጂ በሌላ ምክንያት አይደለም። ይህም {መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺህ ወር በላጭ ናት} በሚለው ቁርኣናዊ ምስክርነት ነው። ለመውሊዳቸው ግን ይህቺ ብልጫ ከቁርኣንም፣ ከሱናም፣ ከሙስሊሙ ህዝብ ዑለማዎች ከአንድም አትታወቅም!!” ይላሉ። [አልመውሪዱ ረዊይ፡ 97]
10. መውሊድን ከኢስላማዊ በአላት ውስጥ ማካተት ሁለት አመታዊ በዓል ያደረጉልንን ነብይ ትእዛዝ መጣስ ነው። ነብዩ ﷺ መዲና ሲገቡ ነዋሪዎቿ የሚጫወቱባቸው ሁለት ቀናት ነበሯቸው። “ምንድን ናቸው እነዚህ ሁለት ቀናት?” ሲሉ ጠየቁ። “በጃሂሊያው ጊዜ እንጫወትባቸው ነበርን” አሉ። ይህኔ “የላቀው አላህ ከነሱ በላጭ በሆኑ ሁለት ቀናት ተክቶላችኋል። እነሱም የአድሓ ቀን እና የፊጥር ቀን ናቸው” አሉ። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1039]
11. የመውሊድ በዓልን ማክበር ለሌሎች የቢድዐ በዓላት በር መክፈት ነው። የወልዮች ልደት እያሉ በመቃብር ዙሪያ ለሚልከሰከሱ፣ የልጆች አመታዊ ልደት ለሚያከብሩ ሰዎችና ለሌሎችም ምርኩዝ ማቀበል ነው።
12. የመውሊድ ኪታቦችና የመውሊድ ድግሶች በነብዩ ﷺ ስም በሚነገሩ የውሸት ቂሷዎች የታጨቁ ናቸው። “አብዛኛው በመውሊድ ደስኳሪዎች እጅ ያለው ውሸትና ቅጥፈት ነው” ይላሉ መውሊድ ደጋፊ የሆኑት ሰኻዊ። [አልመውሊዱ ረዊይ፡ 32] መልእክተኛው ﷺ ግን “በኔ ላይ ሆን ብሎ የዋሸ ሰው መቀመጫውን ከእሳት ያዘጋጅ” ይላሉ። [ቡኻሪ፡ 1291] [ሙስሊም፡ 5]
13. በመውሊድ የቢድዐ ድግስ ላይ ነብዩ ﷺ “ከጭፈራው ይታደማሉ” የሚል ሰቅጣጭ እምነት አለ። የቅጥፈታቸው ቅጥፈት የመውሊዱ ሌሊት ላይ “ነብዩ መጡ” እያሉ ከተቀመጡበት መነሳታቸው ነው። በነገራችን ላይ ነብዩ ﷺ ከሞቱ በኋላ ቀርቶ በህይወት እያሉ እንኳን ሲመጡ ሶሐቦች አይነሱላቸውም ነበር። [አሶሒሐ፡ 358] ሀይተሚ እንዲህ ይላል፡“የዚህ አምሳያው ብዙዎች የነብዩ ﷺ ልደትና እናታቸው እሳቸውን መውለዷ ሲወሳ የሚያደርጉት መቆም ሲሆን ይህም ምንም አይነት መረጃ ያልመጣበት ቢድዐ ነው።” [አልፈታወል ሐዲሢያህ፡ 58]
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
14. በመውሊድ በዓላት የተከበሩ የአላህ ቤቶች በጭብጨባ፣ በውዝዋዜና በጭፈራ ክብራቸው ይረከሳል። ይሄ ደግሞ አላህ ከሃዲዎችን እንዲህ ሲል ከወቀሰባቸው ነገሮች ውስጥ ነው፡-
(وَمَا كَانَ صَلَاتُهُمۡ عِندَ ٱلۡبَيۡتِ إِلَّا مُكَآءٗ وَتَصۡدِيَةٗۚ)
{በቤቱ ዘንድም ስግደታቸው ማፏጨትና ማጨብጨብ እንጂ ሌላ አልነበረም።} [አልአንፋል፡ 35]
ሃያሉ ጌታ እንዲከበሩና ስሙ እንዲወሳባቸው ባዘዘባቸው መስጂዶች ውስጥ ድቤ መደብደብ፣ ማጨብጨብና መጨፈር በአራቱም መዝሀብ የተወገዘ እጅግ አስነዋሪ ተግባር ነው። ይህን ቆሻሻ ተግባር መቃረቢያ አድርጎ ማሰብ ደግሞ የለየለት ጥመት ነው። ኢብኑል ጀውዚይ፡ “ዳንስን ወደ ላቀው አላህ መቃረቢያ ነው ብሎ የሞገተ ሰው ከኢስላም እንደሚወጣ የዑለማዎች ኢጅማዕ ተቋጭቷል” ብሏል። [ሶይዱል ኻጢር፡ 168]
15. ብዙ የመውሊድ ዝግጅቶች የሴትና የወንድ ቅልቅል በብዛት አለባቸው። የብል -ግና መናሃሪያ እየሆኑም ነው። በእለቱ እቃ እያዞሩ የሚሸጡ ሰዎች ሲጋራ፣ ኮንዶምና መሰል ነገሮችን እንደሚይዙ ተጨባጭ መረጃ አለ። በአንዳንድ አካባቢዎች ሴተኛ አዳሪዎች መውሊድ በሚከበርበት አካባቢ የተለያዩ ነገሮችን ለመሸጥ በሚል ሽፋን ጊዜያዊ ዳስ በመቀለስ ለጥፋት እንደሚሰማሩ ከሰበሰብኳቸው መረጃዎች አረጋግጫለሁ።
መቅሪዚይ በ790 ሂጅሪያ በዒማዱል አንባኒ በተዘጋጀው መውሊድ ላይ የታዘበውን እንዲህ ሲል ይገልፀዋል፡- “ሜዳው በዓሊሞች እስከሚጨናነቅ ህዝብ ጎረፈ። በዚያች ሌሊት ሴቶችና ወጣቶች ከባለጌዎች ጋር በመቀላቀላቸው ምክንያት ብዙ አይነት ብልግናዎች ተፈፀሙ። ማለዳ ላይ ሌሊቱን የተጠጡ ከሃምሳ በላይ የአስካሪ መጠጥ እንስራዎች በዛውያው ዙሪያ በነበሩ እርሻዎች ውስጥ ተጥለው እንደተገኙ፣ በርካታ ደናግላንም ክብረ-ንፅህናቸው እንደተገሰሰ፣ በጣም ብዙ ገንዘብ የወጣባቸው ሻማዎችም እንደተለኮሱ እጅግ በርካታ መረጃ ወጥቷል። በማግስቱ ጧት አላህ የንፋስ ጥቃት ላከባቸውና ከቦታው የነበሩ ሰዎችን ፊታቸውን አፈር አለበሳቸው። ድንኳኖቹንም ቆራረጣቸው። አንድም ሰው ባህር መሳፈር አልቻለም። ከዚያን ጊዜ በኋላ መውሊድ አልተዘጋጀም።” [ዱረሩል ዑቁዲል ፈሪዳህ፡ 2/501]
16. የመውሊድ ጨፋሪዎች በውዝውዛኔና መሰል ነገሮች ሰውነታቸው ዝሎ ሌሊቱን ገፍተው ስለሚተኙ አብዛኞቹ የፈጅር ሶላትን የተወሰኑት ደግሞ ዙህርንም ጭምር አይሰግዱም። ለነገሩ ክፍለ - ሃገር ላይ አብዛኛው ታዳሚ ከነጭራሹ ሶላት ሰጋጅ አይደለም።
17. መውሊድ ለማክበር አገር አቋርጠው ረጃጅም ርቀቶችን የሚጓዙ ሰዎች ሞልተዋል። ነብዩ ﷺ ግን ለቢድዐ ቀርቶ ለአላህ ታስቦ ለሚፈፀመው አምልኮት እንኳን ከሶስቱ መስጂዶች (መስጂደል ሐራም፣ መዲና የነብዩ መስጂድ እና አቅሷ) ውጭ አገር አቋርጦ መጓዝ እንደማይገባ አሳስበዋል። [ቡኻሪ፡ 1189] [ሙስሊም፡ 3450] አገር አቋርጠው ያለ መሕረም የሚጓዙ ሴቶችም ቀላል አይደሉም። ነብዩ ﷺ ግን “ማንኛዋም ሴት ከቅርብ ወንድ ቤተሰቧ ጋር እንጂ እንዳትጓዝ” ብለዋል። [ቡኻሪ፡ 1862]
18. መውሊድ የልዩነት መንሰኤ ነው። ለዚህም መውሊድ በተቃረበ ቁጥር የሚነሳውን ውዝግብ መስማቱ ብቻ በቂ ነው። በመውሊድ ላይ ስላልተጋሯቸው ብቻ “ወሃ ~ ቢ”፣ “የነቢ ጠ ^ላት”፣ “ከአይ ^ ሁድ በከፋ ዲን ያበላሹ” እያሉ ሙስሊሞችን መወንጀል የተለመደ ዘመቻ ነው። ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንደሚሉት “ቢድዐ ከልዩነት ጋር የተቆራኘ ነው።” ስለዚህ ቢድዐው እስካለ ድረስ መለያየቱ አይቀርም። ሸውካኒይ እንዲህ ይላሉ፡- “ደግሞም ይሄ መውሊድ ከተከሰተ በኋላ ውዝግቡ ተጧጡፏል። በዚህም ላይ የሚፃፉት ኪታቦች ከከልካዩም ከፈቃጁም በዝተዋል። … ከነሱ ውስጥ እንደማይፈቀድ ቁርጥ አድርጎ የተናገረ ሲኖር ከነሱ ቢድዐነቱን አምኖ መጥፎ ነገር ካልተቆራኘው በሚል መስፈርት የፈቀደው አለ፣ ምንም ማስረጃ ግን አላመጣም።” [አልፈትሑ ረባኒ፡ 2/1091-1095]
ጥፋቶቹ እነዚህ ብቻ አይደሉም። ይህን ሁሉ ጉድ አጭቆ የያዘ ቢድዐ ከጥቃቅን ነገሮች ነውን? ህሊና ያለው ይፍረድ። በርግጥ ከነዚህ ጥፋቶች ውስጥ ከፊሎቹን የሚርቁ አሉ። ግና አንደኛ ጥቂት ናቸው። ሁለትኛ እነዚህ እራሱ ድግሳቸውን በሺርክ የተቀላቀለ መንዙማ ባዮችን ይጋብዙበታል። ከሺርኩ ቢጠራም ድርጊቱ በራሱ መረጃ የለውምና ከቢድዐነት አይዘልም። ሶስተኛ በጥፋት የተወረረውን መውሊድ ሊያወግዙ ቀርቶ የሚያወግዙትን የሚነቅፉ ናቸው። ስለሆነም ጥፋታቸው ከነዚያኞቹ ጥፋት ብዙም የራቀ አይደለም።
=
ኢብኑ ሙነወር
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
(وَمَا كَانَ صَلَاتُهُمۡ عِندَ ٱلۡبَيۡتِ إِلَّا مُكَآءٗ وَتَصۡدِيَةٗۚ)
{በቤቱ ዘንድም ስግደታቸው ማፏጨትና ማጨብጨብ እንጂ ሌላ አልነበረም።} [አልአንፋል፡ 35]
ሃያሉ ጌታ እንዲከበሩና ስሙ እንዲወሳባቸው ባዘዘባቸው መስጂዶች ውስጥ ድቤ መደብደብ፣ ማጨብጨብና መጨፈር በአራቱም መዝሀብ የተወገዘ እጅግ አስነዋሪ ተግባር ነው። ይህን ቆሻሻ ተግባር መቃረቢያ አድርጎ ማሰብ ደግሞ የለየለት ጥመት ነው። ኢብኑል ጀውዚይ፡ “ዳንስን ወደ ላቀው አላህ መቃረቢያ ነው ብሎ የሞገተ ሰው ከኢስላም እንደሚወጣ የዑለማዎች ኢጅማዕ ተቋጭቷል” ብሏል። [ሶይዱል ኻጢር፡ 168]
15. ብዙ የመውሊድ ዝግጅቶች የሴትና የወንድ ቅልቅል በብዛት አለባቸው። የብል -ግና መናሃሪያ እየሆኑም ነው። በእለቱ እቃ እያዞሩ የሚሸጡ ሰዎች ሲጋራ፣ ኮንዶምና መሰል ነገሮችን እንደሚይዙ ተጨባጭ መረጃ አለ። በአንዳንድ አካባቢዎች ሴተኛ አዳሪዎች መውሊድ በሚከበርበት አካባቢ የተለያዩ ነገሮችን ለመሸጥ በሚል ሽፋን ጊዜያዊ ዳስ በመቀለስ ለጥፋት እንደሚሰማሩ ከሰበሰብኳቸው መረጃዎች አረጋግጫለሁ።
መቅሪዚይ በ790 ሂጅሪያ በዒማዱል አንባኒ በተዘጋጀው መውሊድ ላይ የታዘበውን እንዲህ ሲል ይገልፀዋል፡- “ሜዳው በዓሊሞች እስከሚጨናነቅ ህዝብ ጎረፈ። በዚያች ሌሊት ሴቶችና ወጣቶች ከባለጌዎች ጋር በመቀላቀላቸው ምክንያት ብዙ አይነት ብልግናዎች ተፈፀሙ። ማለዳ ላይ ሌሊቱን የተጠጡ ከሃምሳ በላይ የአስካሪ መጠጥ እንስራዎች በዛውያው ዙሪያ በነበሩ እርሻዎች ውስጥ ተጥለው እንደተገኙ፣ በርካታ ደናግላንም ክብረ-ንፅህናቸው እንደተገሰሰ፣ በጣም ብዙ ገንዘብ የወጣባቸው ሻማዎችም እንደተለኮሱ እጅግ በርካታ መረጃ ወጥቷል። በማግስቱ ጧት አላህ የንፋስ ጥቃት ላከባቸውና ከቦታው የነበሩ ሰዎችን ፊታቸውን አፈር አለበሳቸው። ድንኳኖቹንም ቆራረጣቸው። አንድም ሰው ባህር መሳፈር አልቻለም። ከዚያን ጊዜ በኋላ መውሊድ አልተዘጋጀም።” [ዱረሩል ዑቁዲል ፈሪዳህ፡ 2/501]
16. የመውሊድ ጨፋሪዎች በውዝውዛኔና መሰል ነገሮች ሰውነታቸው ዝሎ ሌሊቱን ገፍተው ስለሚተኙ አብዛኞቹ የፈጅር ሶላትን የተወሰኑት ደግሞ ዙህርንም ጭምር አይሰግዱም። ለነገሩ ክፍለ - ሃገር ላይ አብዛኛው ታዳሚ ከነጭራሹ ሶላት ሰጋጅ አይደለም።
17. መውሊድ ለማክበር አገር አቋርጠው ረጃጅም ርቀቶችን የሚጓዙ ሰዎች ሞልተዋል። ነብዩ ﷺ ግን ለቢድዐ ቀርቶ ለአላህ ታስቦ ለሚፈፀመው አምልኮት እንኳን ከሶስቱ መስጂዶች (መስጂደል ሐራም፣ መዲና የነብዩ መስጂድ እና አቅሷ) ውጭ አገር አቋርጦ መጓዝ እንደማይገባ አሳስበዋል። [ቡኻሪ፡ 1189] [ሙስሊም፡ 3450] አገር አቋርጠው ያለ መሕረም የሚጓዙ ሴቶችም ቀላል አይደሉም። ነብዩ ﷺ ግን “ማንኛዋም ሴት ከቅርብ ወንድ ቤተሰቧ ጋር እንጂ እንዳትጓዝ” ብለዋል። [ቡኻሪ፡ 1862]
18. መውሊድ የልዩነት መንሰኤ ነው። ለዚህም መውሊድ በተቃረበ ቁጥር የሚነሳውን ውዝግብ መስማቱ ብቻ በቂ ነው። በመውሊድ ላይ ስላልተጋሯቸው ብቻ “ወሃ ~ ቢ”፣ “የነቢ ጠ ^ላት”፣ “ከአይ ^ ሁድ በከፋ ዲን ያበላሹ” እያሉ ሙስሊሞችን መወንጀል የተለመደ ዘመቻ ነው። ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንደሚሉት “ቢድዐ ከልዩነት ጋር የተቆራኘ ነው።” ስለዚህ ቢድዐው እስካለ ድረስ መለያየቱ አይቀርም። ሸውካኒይ እንዲህ ይላሉ፡- “ደግሞም ይሄ መውሊድ ከተከሰተ በኋላ ውዝግቡ ተጧጡፏል። በዚህም ላይ የሚፃፉት ኪታቦች ከከልካዩም ከፈቃጁም በዝተዋል። … ከነሱ ውስጥ እንደማይፈቀድ ቁርጥ አድርጎ የተናገረ ሲኖር ከነሱ ቢድዐነቱን አምኖ መጥፎ ነገር ካልተቆራኘው በሚል መስፈርት የፈቀደው አለ፣ ምንም ማስረጃ ግን አላመጣም።” [አልፈትሑ ረባኒ፡ 2/1091-1095]
ጥፋቶቹ እነዚህ ብቻ አይደሉም። ይህን ሁሉ ጉድ አጭቆ የያዘ ቢድዐ ከጥቃቅን ነገሮች ነውን? ህሊና ያለው ይፍረድ። በርግጥ ከነዚህ ጥፋቶች ውስጥ ከፊሎቹን የሚርቁ አሉ። ግና አንደኛ ጥቂት ናቸው። ሁለትኛ እነዚህ እራሱ ድግሳቸውን በሺርክ የተቀላቀለ መንዙማ ባዮችን ይጋብዙበታል። ከሺርኩ ቢጠራም ድርጊቱ በራሱ መረጃ የለውምና ከቢድዐነት አይዘልም። ሶስተኛ በጥፋት የተወረረውን መውሊድ ሊያወግዙ ቀርቶ የሚያወግዙትን የሚነቅፉ ናቸው። ስለሆነም ጥፋታቸው ከነዚያኞቹ ጥፋት ብዙም የራቀ አይደለም።
=
ኢብኑ ሙነወር
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
ታቢዒዩ ሶፍዋን ብኑ ሱለይማን እንዲህ ብለዋል፦
ليأتين على الناس زمان ، تكون هِمّةُ أحدهم فيه : بطنُهُ،
ودينُهُ : هواه.
"በሰዎች ላይ ሀሳባቸው ሁሉ ሆዳቸው፣ ሃይማኖታቸው ደግሞ ስሜታቸው የሚሆንበት ጊዜ ይመጣል።"
[አልጁዕ፣ ኢብኑ አቢ ዱንያ ፡ 261]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
ليأتين على الناس زمان ، تكون هِمّةُ أحدهم فيه : بطنُهُ،
ودينُهُ : هواه.
"በሰዎች ላይ ሀሳባቸው ሁሉ ሆዳቸው፣ ሃይማኖታቸው ደግሞ ስሜታቸው የሚሆንበት ጊዜ ይመጣል።"
[አልጁዕ፣ ኢብኑ አቢ ዱንያ ፡ 261]
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
የ “ዘመን መለወጫ” ኮተቶች
~
ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። ይህን ክስተት ተከትሎ የሚፈፀሙ ከሃይማኖታችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ነገሮ አሉ። ከነዚህም ውስጥ:-
1. ድግምትና ጥንቆላ
በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሐሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ-ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ።
* ጥንቆላና ድግምት ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡
وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ
“በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይ ^ጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይ ^ጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [በቀራህ፡ 102]
ነብዩም ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል} ብለዋል። [አሶሒሐ፡ 3387]
* ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም” ብሏል። [ጠሃ፡ 69]
* ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም} ብለዋል። [ሙስሊም፡ 5957]
2. የጳጉሜ ዱዓእ የሚል አጉል ፈጠራ
በአንዳንድ አካባቢዎች የጳጉሜ ዱዓእ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) የሚል እምነት አለ። ይሄ አጉል እምነት ነው። በጣም የሚገርመው ለዱዓእ የሚጣዱት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ብለዋል።
3. እንቁጣጣሽ ማክበር
ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ በከንቱ የሚዳክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ሲበዛ ግልፅ ከመሆኑ ጋር በዚህ ላይ የሚሸወድ መኖሩ እጅጉን የሚደንቅ ነው። ብቻ ለማንም እንደማይሰወር ባስብም ለማስታወስ ያክል:-
* አቆጣጠሩ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው በሚሲዮናውያን መሆኑ፣
* አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” መባሉ፣
* የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ መሞገታቸው
* እንዲሁም ይበልጥ ለማረጋገጥ የ “ዘመን መለወጫ” ወቅት ላይ ለምሳሌ “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በአሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡
ይህንን ስንል የሚጎረብጣቸው አሉ። እኛኮ ዒድን አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ይልቁንም የኛን እምነታዊ መገለጫ ካላንፀባረቃችሁ ብሎ ሌሎችን መወረፍ አክራሪነት ነው። እምነታችን በሌሎች ህዝቦች መለያ በሆኑ እምነቶች፣ ባህሎችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 26/2007)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። ይህን ክስተት ተከትሎ የሚፈፀሙ ከሃይማኖታችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ነገሮ አሉ። ከነዚህም ውስጥ:-
1. ድግምትና ጥንቆላ
በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሐሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ-ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ።
* ጥንቆላና ድግምት ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡
وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ
“በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይ ^ጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይ ^ጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [በቀራህ፡ 102]
ነብዩም ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል} ብለዋል። [አሶሒሐ፡ 3387]
* ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም” ብሏል። [ጠሃ፡ 69]
* ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም} ብለዋል። [ሙስሊም፡ 5957]
2. የጳጉሜ ዱዓእ የሚል አጉል ፈጠራ
በአንዳንድ አካባቢዎች የጳጉሜ ዱዓእ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) የሚል እምነት አለ። ይሄ አጉል እምነት ነው። በጣም የሚገርመው ለዱዓእ የሚጣዱት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ብለዋል።
3. እንቁጣጣሽ ማክበር
ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ በከንቱ የሚዳክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ሲበዛ ግልፅ ከመሆኑ ጋር በዚህ ላይ የሚሸወድ መኖሩ እጅጉን የሚደንቅ ነው። ብቻ ለማንም እንደማይሰወር ባስብም ለማስታወስ ያክል:-
* አቆጣጠሩ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው በሚሲዮናውያን መሆኑ፣
* አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” መባሉ፣
* የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ መሞገታቸው
* እንዲሁም ይበልጥ ለማረጋገጥ የ “ዘመን መለወጫ” ወቅት ላይ ለምሳሌ “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በአሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡
ይህንን ስንል የሚጎረብጣቸው አሉ። እኛኮ ዒድን አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ይልቁንም የኛን እምነታዊ መገለጫ ካላንፀባረቃችሁ ብሎ ሌሎችን መወረፍ አክራሪነት ነው። እምነታችን በሌሎች ህዝቦች መለያ በሆኑ እምነቶች፣ ባህሎችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 26/2007)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ስለ መውሊድ የሚሰጠው ትምህርት ለበዛባቸው!
~
ከመውሊድ ቢድዐ ስናስጠነቅቅ በዝቶባቸው የተንገሸገሹ አካላትን እያየን ነው። በቁርጥ ለመናገር በዚህ ጉዳይ ላይ ሐቂቃውን እንጂ የሰዎችን ስሜት መለኪያ አናደርግም። ሐቂቃው የት ላይ ነው?
1. የጥፋቱ አራማጆች ሳይታክቱ ወደ ቢድዐቸው እየተጣሩ እያየን ነው። የአጥፊዎቹ ስብከትና ውትወታ ሳይበዛበት ማስጠንቀቂያው የሚረብሸው የችግሩ ደጋፊ የሆነን አካል ነው።
2. እነዚህ አካላት ከቢድዐው የሚያስጠነቅቅ ትምህርት የሚበዛባቸው ለጉዳዩ የሚሰጡት የረባ ትኩረት ስለሌላቸው ነው። እነሱ ጧት ማታ ቢዝነሳቸውን ሲያስተዋውቁ፣ ድለላቸው ላይ ሲሰማሩ፣ አርቲ ቡርቲ የኳስና የፖለቲካ ወሬ ሲለቀልቁ ሳይበዛባቸው በቁርኣንና ሐዲሥ፣ በዑልማእ ንግግር የታጀበ ትምህርት የሚበዛባቸው ለደዕዋ የሚሰጡት ትርጉም የቀለለ ወይም የተዛባ በመሆኑ ነው።
3. ነብያችን ﷺ ዘወትር በየ ኹጥባቸው ላይ አይናቸው ቀልቶ፣ ድምፃቸው ጎልቶ፣ ቁጣቸው በርትቶ ደጋግመው ከቢድዐ ያስጠነቅቁ ነበር። [ሙስሊም፡ 867] ይሄ እንግዲህ ቢድዐው እንደዛሬው ገና ሳይንሰራፋ ማለት ነው።
ሌላም ሐዲሥ አለ። ሶሐቢዩ አቡ ኡማማ አልባሂሊይ ረዲየላሁ ዐንሁ በደማስቆ መስጂድ አጠገብ በጦርነት የተገ ^ደሉ ኸዋ ^ ሪጆችን ጭንቅላቶች ተመለከቱና እንዲህ አሉ፦
كِلَابُ النَّارِ شَرُّ قَتْلَى تَحْتَ أَدِيمِ السَّمَاءِ، خَيْرُ قَتْلَى مَنْ قَتَلُوهُ ...
"የጀሀነም ው ^ ሾች! ከሰማይ በታች ከተገ ^ ደሉት ሁሉ የከፉ ናቸው። ከተገ ^ዳይ ሁሉ በላጩ እነሱ የገ. ደሉት ነው።" ...
አስተላላፊው አቡ ጋሊብ ለአቡ ኡማማ፡ "አንተ ግን ይህንን ያልከውን ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ሰምተሃልን?" ብለው ሲጠይቁ እንዲህ ብለው መለሱ፦
لَوْ لَمْ أَسْمَعْهُ إِلَّا مَرَّةً أَوْ مَرَّتَيْنِ أَوْ ثَلَاثًا أَوْ أَرْبَعًا - حَتَّى عَدَّ سَبْعًا - مَا حَدَّثْتُكُمُوهُ.
"አንድ ጊዜ፣ ሁለት ጊዜ፣ ሦስት ጊዜ፣ ወይም አራት፣ ... - ሰባት እስከሚቆጥሩ ድረስ - ይህን ያህል ጊዜ ብቻ እንጂ የሰማኋቸው ባልሆን ኖሮ ባልነገርኳችሁ ነበር!!" [ቲሪሚዚይ፡ 3000]
ምን ማለት ነው? ነብያችን ﷺ ከነዚህ የቢድዐ ኃይሎች ይህን ሁሉ ጊዜ ደግመው ደጋግመው ያስጠነቅቁ ነበር ማለት ነው። ልብ በሉ! በጊዜያቸው እነዚህ አካላት እንደ ቡድን ገና ያልመጡ ከመሆናቸው ጋር ነው በዚህ መልኩ የወተወቱት። ዛሬስ? የቢድዐ ባህር ውስጥ እየዋኙ ከዚያ ስለ ቢድዐው አትናገሩ ይላሉ። የተሞሉት ነገር ነው እንዲህ የሚያደርጋቸው። እስፖንጅ የያዘውን ነው የሚተፋው!!
ስለዚህ ደግመን ደጋግመን ከቢድዐ እናስጠነቅቃለን። በማስረጃ ብቻ!!
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ከመውሊድ ቢድዐ ስናስጠነቅቅ በዝቶባቸው የተንገሸገሹ አካላትን እያየን ነው። በቁርጥ ለመናገር በዚህ ጉዳይ ላይ ሐቂቃውን እንጂ የሰዎችን ስሜት መለኪያ አናደርግም። ሐቂቃው የት ላይ ነው?
1. የጥፋቱ አራማጆች ሳይታክቱ ወደ ቢድዐቸው እየተጣሩ እያየን ነው። የአጥፊዎቹ ስብከትና ውትወታ ሳይበዛበት ማስጠንቀቂያው የሚረብሸው የችግሩ ደጋፊ የሆነን አካል ነው።
2. እነዚህ አካላት ከቢድዐው የሚያስጠነቅቅ ትምህርት የሚበዛባቸው ለጉዳዩ የሚሰጡት የረባ ትኩረት ስለሌላቸው ነው። እነሱ ጧት ማታ ቢዝነሳቸውን ሲያስተዋውቁ፣ ድለላቸው ላይ ሲሰማሩ፣ አርቲ ቡርቲ የኳስና የፖለቲካ ወሬ ሲለቀልቁ ሳይበዛባቸው በቁርኣንና ሐዲሥ፣ በዑልማእ ንግግር የታጀበ ትምህርት የሚበዛባቸው ለደዕዋ የሚሰጡት ትርጉም የቀለለ ወይም የተዛባ በመሆኑ ነው።
3. ነብያችን ﷺ ዘወትር በየ ኹጥባቸው ላይ አይናቸው ቀልቶ፣ ድምፃቸው ጎልቶ፣ ቁጣቸው በርትቶ ደጋግመው ከቢድዐ ያስጠነቅቁ ነበር። [ሙስሊም፡ 867] ይሄ እንግዲህ ቢድዐው እንደዛሬው ገና ሳይንሰራፋ ማለት ነው።
ሌላም ሐዲሥ አለ። ሶሐቢዩ አቡ ኡማማ አልባሂሊይ ረዲየላሁ ዐንሁ በደማስቆ መስጂድ አጠገብ በጦርነት የተገ ^ደሉ ኸዋ ^ ሪጆችን ጭንቅላቶች ተመለከቱና እንዲህ አሉ፦
كِلَابُ النَّارِ شَرُّ قَتْلَى تَحْتَ أَدِيمِ السَّمَاءِ، خَيْرُ قَتْلَى مَنْ قَتَلُوهُ ...
"የጀሀነም ው ^ ሾች! ከሰማይ በታች ከተገ ^ ደሉት ሁሉ የከፉ ናቸው። ከተገ ^ዳይ ሁሉ በላጩ እነሱ የገ. ደሉት ነው።" ...
አስተላላፊው አቡ ጋሊብ ለአቡ ኡማማ፡ "አንተ ግን ይህንን ያልከውን ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ሰምተሃልን?" ብለው ሲጠይቁ እንዲህ ብለው መለሱ፦
لَوْ لَمْ أَسْمَعْهُ إِلَّا مَرَّةً أَوْ مَرَّتَيْنِ أَوْ ثَلَاثًا أَوْ أَرْبَعًا - حَتَّى عَدَّ سَبْعًا - مَا حَدَّثْتُكُمُوهُ.
"አንድ ጊዜ፣ ሁለት ጊዜ፣ ሦስት ጊዜ፣ ወይም አራት፣ ... - ሰባት እስከሚቆጥሩ ድረስ - ይህን ያህል ጊዜ ብቻ እንጂ የሰማኋቸው ባልሆን ኖሮ ባልነገርኳችሁ ነበር!!" [ቲሪሚዚይ፡ 3000]
ምን ማለት ነው? ነብያችን ﷺ ከነዚህ የቢድዐ ኃይሎች ይህን ሁሉ ጊዜ ደግመው ደጋግመው ያስጠነቅቁ ነበር ማለት ነው። ልብ በሉ! በጊዜያቸው እነዚህ አካላት እንደ ቡድን ገና ያልመጡ ከመሆናቸው ጋር ነው በዚህ መልኩ የወተወቱት። ዛሬስ? የቢድዐ ባህር ውስጥ እየዋኙ ከዚያ ስለ ቢድዐው አትናገሩ ይላሉ። የተሞሉት ነገር ነው እንዲህ የሚያደርጋቸው። እስፖንጅ የያዘውን ነው የሚተፋው!!
ስለዚህ ደግመን ደጋግመን ከቢድዐ እናስጠነቅቃለን። በማስረጃ ብቻ!!
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
ደዕዋ ላይ ላለኸው ወገኔ!
~
በአካባቢህ፣ በሰፈርህ የጥፋት ኃይሎች ጉልበት አውጥተውብሃል? ከጎንህ የሚቆም የሚርረዳህ አጋር አጥተሃል? በፍፁም በፍፁም እጅ እንዳትሰጥ። እንዳትርረታ። በቀላል የምትሰበር ከሆነ ሐቅን፣ ተውሒድን፣ ሱናን ትጎዳለህ። ታላቁ ዓሊም ሙሐመድ ብኑ ሷሊሕ አልዑሠይሚን (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፡-
إنْ كنت وحيداً في بلدك تدعو إلى السنّة واتّباع السلف ؛ وكُثَرَ الأعداء الذين يدعون إلى مذهبهم الباطل ؛*
*فالواجب ألّا تنهزم ؛* لأنك إذا انهزمت فقد هزمت الحق ؛ بل اثبُت ؛ وما أرعبَ أعداءك إذا رأوك ثابتاً )).
“በሃገርህ ውስጥ ወደ ሱና እና የሰለፎችን መንገድ ወደ መከተል የምትጣራ ብቸኛ ሰው ብትሆን እንኳ፣ ወደ ጥፋት መንገዳቸው የሚጣሩ ጠላቶች ብዙ ቢሆኑም፣ ፈፅሞ መሸነፍ የለብህም። ምክንያቱም አንተ ተሸነፍክ ማለት፣ ሐቅ ተሸነፈ ማለት ነው። ስለዚህ ፅና። ጠላቶችህን አንተን ፅኑ ሆነህ እንደማየት የሚያስፈራቸው ነገር የለም።”
📚 [ሸርሑል ካፊየቲ-ሻፊያ፡ 1/201]
በአላህ ላይ ተወኩል ይኑርህ። የሌሎች መብዛት አያስደንግጥህ። ከጎንህ ሰው ብታጣ ባይተዋርነት አይሰማህ። የነብዩን ﷺ የደዕዋ ታሪክ በተግባር ኑረው። በአላህ ላይ ተስፋ አድርግ። ኢንሻአላህ ነገሮች ይቀየራሉ ብለህ ከልብህ ተግተህ ስራ። ባንዴ ውጤት አትጠብቅ። እወቅ! ጠብታ ውሃ ድንጋይ ትበሳለች። መንፈሰ ልፍስፍስ አትሁን። ፈተና አይስበርህ። ገና ለጀማሪዎች የምታስተምራት ሠላሠቱል ኡሱል ኪታብ መግቢያ ላይ ያለውን "አሶብሩ ዐለል አዛ ፊሂ" የሚለውን ከስጋህ ከደምህ ጋር አዋህደው። መቼስ አንተ የማትኖረውን ሐቅ ለሌላ ማሻገር ከባድ እንደሆነ አይጠፋህም። ባይሆን ለአካባቢህም ለጊዜህም የሚመጥን፣ ኃላፊነት ያለበት ሰው ሆነህ ተገኝ። አዋዋልህን አሳምር። የዋዛ ፈዛዛ ሰው አትሁን። "ጦር ሜዳ ውስጥ ከተገኘ ወርቅ ጦር ሜዳ ውስጥ የተገኘ ብረት የተሻለ ዋጋ አለው" ይባላል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
በአካባቢህ፣ በሰፈርህ የጥፋት ኃይሎች ጉልበት አውጥተውብሃል? ከጎንህ የሚቆም የሚርረዳህ አጋር አጥተሃል? በፍፁም በፍፁም እጅ እንዳትሰጥ። እንዳትርረታ። በቀላል የምትሰበር ከሆነ ሐቅን፣ ተውሒድን፣ ሱናን ትጎዳለህ። ታላቁ ዓሊም ሙሐመድ ብኑ ሷሊሕ አልዑሠይሚን (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፡-
إنْ كنت وحيداً في بلدك تدعو إلى السنّة واتّباع السلف ؛ وكُثَرَ الأعداء الذين يدعون إلى مذهبهم الباطل ؛*
*فالواجب ألّا تنهزم ؛* لأنك إذا انهزمت فقد هزمت الحق ؛ بل اثبُت ؛ وما أرعبَ أعداءك إذا رأوك ثابتاً )).
“በሃገርህ ውስጥ ወደ ሱና እና የሰለፎችን መንገድ ወደ መከተል የምትጣራ ብቸኛ ሰው ብትሆን እንኳ፣ ወደ ጥፋት መንገዳቸው የሚጣሩ ጠላቶች ብዙ ቢሆኑም፣ ፈፅሞ መሸነፍ የለብህም። ምክንያቱም አንተ ተሸነፍክ ማለት፣ ሐቅ ተሸነፈ ማለት ነው። ስለዚህ ፅና። ጠላቶችህን አንተን ፅኑ ሆነህ እንደማየት የሚያስፈራቸው ነገር የለም።”
📚 [ሸርሑል ካፊየቲ-ሻፊያ፡ 1/201]
በአላህ ላይ ተወኩል ይኑርህ። የሌሎች መብዛት አያስደንግጥህ። ከጎንህ ሰው ብታጣ ባይተዋርነት አይሰማህ። የነብዩን ﷺ የደዕዋ ታሪክ በተግባር ኑረው። በአላህ ላይ ተስፋ አድርግ። ኢንሻአላህ ነገሮች ይቀየራሉ ብለህ ከልብህ ተግተህ ስራ። ባንዴ ውጤት አትጠብቅ። እወቅ! ጠብታ ውሃ ድንጋይ ትበሳለች። መንፈሰ ልፍስፍስ አትሁን። ፈተና አይስበርህ። ገና ለጀማሪዎች የምታስተምራት ሠላሠቱል ኡሱል ኪታብ መግቢያ ላይ ያለውን "አሶብሩ ዐለል አዛ ፊሂ" የሚለውን ከስጋህ ከደምህ ጋር አዋህደው። መቼስ አንተ የማትኖረውን ሐቅ ለሌላ ማሻገር ከባድ እንደሆነ አይጠፋህም። ባይሆን ለአካባቢህም ለጊዜህም የሚመጥን፣ ኃላፊነት ያለበት ሰው ሆነህ ተገኝ። አዋዋልህን አሳምር። የዋዛ ፈዛዛ ሰው አትሁን። "ጦር ሜዳ ውስጥ ከተገኘ ወርቅ ጦር ሜዳ ውስጥ የተገኘ ብረት የተሻለ ዋጋ አለው" ይባላል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
ደዕዋ ላይ ላለኸው ወገኔ
~
በደዕዋ ሂደትህ ላይ ጠላት አታብዛ። ከሁሉ ጋር አትጋጭ። በተለይ በአካባቢህ ደዕዋው ገና ዳዴ ላይ ከሆነ የማህበራዊ ሚዲያን ደዕዋ ወይም የተሻለ ድጋፍና መሰረት ያላቸውን አካባቢዎች አካሄድ ምሳሌ እንዳታደርግ። አቅምህን አገናዝብ። ደዕዋህን የፍጥጫ አታድርገው። የአካባቢህን ተጨባጭ ተረዳ። ተማሪዎችህ በችኮላ ለደዕዋው እንቅፋት እንዳይሆኑ ተቆጣጠር። ሁሉን ባንዴ አሳካለሁ ብለህ አታስብ። ብዙ ያሳደደ አንድ አይዝም።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
በደዕዋ ሂደትህ ላይ ጠላት አታብዛ። ከሁሉ ጋር አትጋጭ። በተለይ በአካባቢህ ደዕዋው ገና ዳዴ ላይ ከሆነ የማህበራዊ ሚዲያን ደዕዋ ወይም የተሻለ ድጋፍና መሰረት ያላቸውን አካባቢዎች አካሄድ ምሳሌ እንዳታደርግ። አቅምህን አገናዝብ። ደዕዋህን የፍጥጫ አታድርገው። የአካባቢህን ተጨባጭ ተረዳ። ተማሪዎችህ በችኮላ ለደዕዋው እንቅፋት እንዳይሆኑ ተቆጣጠር። ሁሉን ባንዴ አሳካለሁ ብለህ አታስብ። ብዙ ያሳደደ አንድ አይዝም።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ሁለት ሰዎች ብቻ በጀማዐ ሲሰግዱ ተከታዩ ከኢማሙ ትንሽ ወደ ኋላ መሆን ልክ ነውን?
~
ሁለት ሰዎች ብቻ ጀማዐ ሶላት የሚሰግዱ ከሆነ ተከታዩ ከኢማሙ ትንሽ ወደ ኋላ ሆኖ ሲቆም ማየት የተለመደ ነው። በርግጥ ይህንን የመረጡ ዓሊሞች አሉ። ይሁን እንጂ ትክክለኛው አፈፃፀም ተከታዩ ከኢማሙ ጋር እኩል ሆኖ መቆሙ ነው። ይሄ የብዙሃን ዑለማእ አቋም ነው። አልሓፊዝ ኢብኑ ረጀብም እንዲህ ብለዋል፦
" الإمام إذا لم يأتم به غير واحد، فإنه يقيمه عن يمينه بحذائه، ولو كان صبيا لم يبلغ الحلم. وهذا كالإجماع من أهل العلم.
وقد حكاه الترمذي فِي "جامعه" عَن أهل العلم من أصحاب النّبيّ - صلّى الله عليه وسلّم - فمن بعدهم، قالوا: إذا كان الرّجل مع الرّجل يقوم عن يمين الإمام. وحكاه ابن المنذر عَن أكثر أهل العلم... "
“አንድ ኢማም ከአንድ ሰው ውጭ የሚከተለው ከሌለ በቀጥታ ከቀኙ በኩል ሊያቆመው ይገባል። ለአቅመ ሃላፊነት ያልደረሰ ህፃን ቢሆን እንኳ። ይሄ የእውቀት ባለቤቶች ዘንድ ልክ እንደ ኢጅማዕ ነው። ቲርሚዚ በጃሚዐቸው ውስጥ ከነብዩ ﷺ ባልደረቦች እና ከነሱ በኋላ ከመጡ አዋቂዎች ጠቅሰውታል። አንድ ሰው ከአንድ ሰው ጋር ብቻ ከሆነ ከኢማሙ ቀኝ ይቆማል ብለዋል። ኢብኑል ሙንዚርም ከብዙ የእውቀት ባለቤቶች ጠቅሰውታል።” [ፈትሑል ባሪ፡ 6/197 – 198]
ኢማሙል ቡኻሪ ረሒመሁላህ በሶሒሕ ኪታባቸው ውስጥ እንዲህ የሚል ርእስ አስፍረዋል፦
" يَقُومُ عَنْ يَمِينِ الإمَامِ بحذائهِ سواءً، إذا كَاناَ اثْنَيْن".
“ከኢማሙ በቀኙ በኩል እኩል ሆኖ ይቆማል፣ ሁለት ከሆኑ።”
ከዚያም ተከታዩን የኢብኑ ዐባስን ረዲየላሁ ዐንሁማ ሐዲሥ አስፍረዋል፦
"بِتُّ فِي بَيْتِ خَالَتِي مَيْمُونَةَ، فَصَلَّى رَسُولُ اللَّهِ ﷺ العِشَاءَ، ثُمَّ جَاءَ فَصَلَّى أَرْبَعَ رَكَعَاتٍ، ثُمَّ نَامَ، ثُمَّ قَامَ، فَجِئْتُ فَقُمْتُ عَنْ يَسَارِهِ، فَجَعَلَنِي عَنْ يَمِينِهِ،... "
“ከየሹማዬ መይሙና ዘንድ አድሬ ነበር። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዒሻእን ሰገዱ። ከዚያም (እቤት) መጡና አራት ረከዐዎችን ሰገዱ። ከዚያም ተኙ። ከዚያም ለሶላት ቆሙ። በግራቸው በኩል ቆምኩኝ። በቀኛቸው አደረጉኝ።...” [ቡኻሪ፡ 697]
“ይሄ የኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ ሐዲሥ እኩል ሆኖ መቆምን ይጠቁማል ወይ?” ከተባለ “አዎ” ነው መልሱ። ኢብኑ ሐጀር “ከቀኝ ጎናቸው አደረጉኝ” የሚለውን የኢብኑ ዐባስን ንግግር ሲያብራሩ “ጉልህ መልእክቱ እኩል ሆኖ መቆም ነው” ብለዋል።
የቡኻሪን ርእስ አስመልክተውም እንዲህ ብለዋል፦
በዚህ ርእስ አሰጣጣቸው የፈለጉት በሶላት ውስጥ ኢማምና ተከታይ ብቻቸውን ከተገኙ ተከታዩ ከኢማሙ በቀኝ ጎን እኩል ሆኖ ማለትም በመቆሚያው ቦታ ላይ መቀደምም ሆነ መዘግየት ሳይኖር እኩል መሆናቸው ነው።” [ፈትሑል ባሪ፡ 6/197]
.
በሌላ ዘገባ ላይም ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል፦
" أَتَيْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ مِنْ آخِرِ اللَّيْلِ، فَصَلَّيْتُ خَلْفَهُ، فَأَخَذَ بِيَدِي، فَجَرَّنِي، فَجَعَلَنِي حِذَاءَهُ، فَلَمَّا أَقْبَلَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عَلَى صَلاتِهِ، خَنَسْتُ، فَصَلَّى رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَلَمَّا انْصَرَفَ قَالَ لِي: مَا شَأْنِي أَجْعَلُكَ حِذَائِي فَتَخْنِسُ؟
فَقُلْتُ: يَا رَسُولَ اللهِ! أَوَيَنْبَغِي لِأَحَدٍ أَنْ يُصَلِّيَ حِذَاءَكَ، وَأَنْتَ رَسُولُ اللهِ الَّذِي أَعْطَاكَ اللهُ؟
قَالَ: فَأَعْجَبْتُهُ، فَدَعَا اللهَ لِي أَنْ يَزِيدَنِي عِلْمًا وَفَهْمًا... "
“የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዘንድ የሌሊቱ መጨረሻ ላይ መጣሁኝ። ከኋላቸው ልሰግድ ቆምኩኝ። እጄን ይዘው በመጎተት ከሳቸው ጎን ትይዩ አቆሙኝ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሶላታቸው ላይ ሲያተኩሩ ጊዜ ወደኋላ አልኩኝ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሰገዱ። ባጠናቀቁ ጊዜ፦ ‘ምነው? እኔ በጎኔ ሳደርግህ ወደኋላ ትላለህሳ?’ አሉኝ።
‘የአላህ መልእክተኛ ሆይ! በአንተ ትይዩ ሆኖ ለማንስ ሊሰግድ ይገባዋልን? አንተ አላህ ያደለህ የአላህ መልእክተኛ ሆነህ ሳለ?’ አልኳቸው። ገረምኳቸው። እውቀትንና ግንዛቤን እንዲጨምረኝ አላህን ለመኑልኝ።” [አሶሒሐህ፡ 6/174 - 175]
ከጃቢርም ተመሳሳይ መልእክት ተላልፏል። [ሙስሊም፡ 3010]
በተጨማሪም ዐብዱላህ ብኑ ዑትባህ ብኒ መስዑድ እንዲህ ብለዋል፦
دخلت على عمر بن الخطاب رضي الله عنه بالهاجرة «فوجدته يسبح، فقمت وراءه. فقربني حتى جعلني حذاءه عن يمينه»
“ዑመር ብኑል ኸጧብ ረዲየላሁ ዐንሁ ዘንድ ቀትር ላይ ስገባ ሱና እየሰገዱ አገኘኋቸው። ከኋላቸው ቆምኩኝ። በቀኛቸው በኩል አድርገው አቀረቡኝ።” [ሙወጦእ ማሊክ፡ ሐዲሥ ቁ. 364]
በተጨማሪም ኢብኑ ጁረይጅ ረሒመሁላህ “ 'አንድ ሰው ከአንድ ሰው ጋር ብቻ ሆኖ የሚሰግድ ከሆነ ከየት በኩል ነው የሚሆነው?' ብየ ዐጧእን ጠይቄ ነበር” ይላሉ።
ዐጧእ፦ “በቀኙ በኩል” አሉ።
ኢብኑ ጁረይጅ፦ “አብሮት እስከሚሰለፍ ድረስ በሱው አቅጣጫ ነው የሚሆነው? አንዱ ሌላውን ሳይቀደም?”
ዐጧእ፦ “አዎ!”
ኢብኑ ጁረይጅ፦ “በመሃላቸው ክፍተት እስከማይኖር ድረስ?
ዐጧእ፦ “አዎ!” [ሙሶነፉ ዐብዲረዛቅ፡ ቁ. 3870]
ስለዚህ ሁለት ሆነው በሚሰግዱ ጊዜ ከኢማም ትንሽ ወደ ኋላ መቅረት ምንም እንኳ የደገፉት ዓሊሞች ቢኖሩም ማስረጃ የሚደግፈው ግን አይደለም። ይህንን ማድረግ የተወደደ ቢሆን ኖሮ ተጨባጭ መረጃ ከነብዩ ﷺ ይተላለፍ ነበር። ነገር ግን የለም። ከሶሐቦችም ይገኝ ነበር። ይህም የለም። መረጃ አለመኖሩ መሰረት እንደሌለው ያሳያል። እንደሚታወቀው ነብዩ ﷺ “ስሰግድ እንዳያችሁኝ ስገዱ” ብለዋል። [ቡኻሪ፡ 631] የሳቸው አሰጋገድ ውስጥ ደግሞ ከአንድ ተከታይ ጋር ብቻ ሆነው በሰገዱበት ላይ ትንሽ የተቀደሙበት አልተገኘም። ይልቁንም የተገኘው ከዚህ በተለየ እኩል ጎን ለጎን መቆም ነው። ይሄኛው አቋም ከዘመናችን ዓሊሞች ውስጥ የኢብኑ ባዝ፣ የአልባኒይ እና የኢብኑ ዑሠይሚን አቋም ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
ሁለት ሰዎች ብቻ ጀማዐ ሶላት የሚሰግዱ ከሆነ ተከታዩ ከኢማሙ ትንሽ ወደ ኋላ ሆኖ ሲቆም ማየት የተለመደ ነው። በርግጥ ይህንን የመረጡ ዓሊሞች አሉ። ይሁን እንጂ ትክክለኛው አፈፃፀም ተከታዩ ከኢማሙ ጋር እኩል ሆኖ መቆሙ ነው። ይሄ የብዙሃን ዑለማእ አቋም ነው። አልሓፊዝ ኢብኑ ረጀብም እንዲህ ብለዋል፦
" الإمام إذا لم يأتم به غير واحد، فإنه يقيمه عن يمينه بحذائه، ولو كان صبيا لم يبلغ الحلم. وهذا كالإجماع من أهل العلم.
وقد حكاه الترمذي فِي "جامعه" عَن أهل العلم من أصحاب النّبيّ - صلّى الله عليه وسلّم - فمن بعدهم، قالوا: إذا كان الرّجل مع الرّجل يقوم عن يمين الإمام. وحكاه ابن المنذر عَن أكثر أهل العلم... "
“አንድ ኢማም ከአንድ ሰው ውጭ የሚከተለው ከሌለ በቀጥታ ከቀኙ በኩል ሊያቆመው ይገባል። ለአቅመ ሃላፊነት ያልደረሰ ህፃን ቢሆን እንኳ። ይሄ የእውቀት ባለቤቶች ዘንድ ልክ እንደ ኢጅማዕ ነው። ቲርሚዚ በጃሚዐቸው ውስጥ ከነብዩ ﷺ ባልደረቦች እና ከነሱ በኋላ ከመጡ አዋቂዎች ጠቅሰውታል። አንድ ሰው ከአንድ ሰው ጋር ብቻ ከሆነ ከኢማሙ ቀኝ ይቆማል ብለዋል። ኢብኑል ሙንዚርም ከብዙ የእውቀት ባለቤቶች ጠቅሰውታል።” [ፈትሑል ባሪ፡ 6/197 – 198]
ኢማሙል ቡኻሪ ረሒመሁላህ በሶሒሕ ኪታባቸው ውስጥ እንዲህ የሚል ርእስ አስፍረዋል፦
" يَقُومُ عَنْ يَمِينِ الإمَامِ بحذائهِ سواءً، إذا كَاناَ اثْنَيْن".
“ከኢማሙ በቀኙ በኩል እኩል ሆኖ ይቆማል፣ ሁለት ከሆኑ።”
ከዚያም ተከታዩን የኢብኑ ዐባስን ረዲየላሁ ዐንሁማ ሐዲሥ አስፍረዋል፦
"بِتُّ فِي بَيْتِ خَالَتِي مَيْمُونَةَ، فَصَلَّى رَسُولُ اللَّهِ ﷺ العِشَاءَ، ثُمَّ جَاءَ فَصَلَّى أَرْبَعَ رَكَعَاتٍ، ثُمَّ نَامَ، ثُمَّ قَامَ، فَجِئْتُ فَقُمْتُ عَنْ يَسَارِهِ، فَجَعَلَنِي عَنْ يَمِينِهِ،... "
“ከየሹማዬ መይሙና ዘንድ አድሬ ነበር። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዒሻእን ሰገዱ። ከዚያም (እቤት) መጡና አራት ረከዐዎችን ሰገዱ። ከዚያም ተኙ። ከዚያም ለሶላት ቆሙ። በግራቸው በኩል ቆምኩኝ። በቀኛቸው አደረጉኝ።...” [ቡኻሪ፡ 697]
“ይሄ የኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ ሐዲሥ እኩል ሆኖ መቆምን ይጠቁማል ወይ?” ከተባለ “አዎ” ነው መልሱ። ኢብኑ ሐጀር “ከቀኝ ጎናቸው አደረጉኝ” የሚለውን የኢብኑ ዐባስን ንግግር ሲያብራሩ “ጉልህ መልእክቱ እኩል ሆኖ መቆም ነው” ብለዋል።
የቡኻሪን ርእስ አስመልክተውም እንዲህ ብለዋል፦
በዚህ ርእስ አሰጣጣቸው የፈለጉት በሶላት ውስጥ ኢማምና ተከታይ ብቻቸውን ከተገኙ ተከታዩ ከኢማሙ በቀኝ ጎን እኩል ሆኖ ማለትም በመቆሚያው ቦታ ላይ መቀደምም ሆነ መዘግየት ሳይኖር እኩል መሆናቸው ነው።” [ፈትሑል ባሪ፡ 6/197]
.
በሌላ ዘገባ ላይም ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል፦
" أَتَيْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ مِنْ آخِرِ اللَّيْلِ، فَصَلَّيْتُ خَلْفَهُ، فَأَخَذَ بِيَدِي، فَجَرَّنِي، فَجَعَلَنِي حِذَاءَهُ، فَلَمَّا أَقْبَلَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عَلَى صَلاتِهِ، خَنَسْتُ، فَصَلَّى رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَلَمَّا انْصَرَفَ قَالَ لِي: مَا شَأْنِي أَجْعَلُكَ حِذَائِي فَتَخْنِسُ؟
فَقُلْتُ: يَا رَسُولَ اللهِ! أَوَيَنْبَغِي لِأَحَدٍ أَنْ يُصَلِّيَ حِذَاءَكَ، وَأَنْتَ رَسُولُ اللهِ الَّذِي أَعْطَاكَ اللهُ؟
قَالَ: فَأَعْجَبْتُهُ، فَدَعَا اللهَ لِي أَنْ يَزِيدَنِي عِلْمًا وَفَهْمًا... "
“የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዘንድ የሌሊቱ መጨረሻ ላይ መጣሁኝ። ከኋላቸው ልሰግድ ቆምኩኝ። እጄን ይዘው በመጎተት ከሳቸው ጎን ትይዩ አቆሙኝ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሶላታቸው ላይ ሲያተኩሩ ጊዜ ወደኋላ አልኩኝ። የአላህ መልእክተኛ ﷺ ሰገዱ። ባጠናቀቁ ጊዜ፦ ‘ምነው? እኔ በጎኔ ሳደርግህ ወደኋላ ትላለህሳ?’ አሉኝ።
‘የአላህ መልእክተኛ ሆይ! በአንተ ትይዩ ሆኖ ለማንስ ሊሰግድ ይገባዋልን? አንተ አላህ ያደለህ የአላህ መልእክተኛ ሆነህ ሳለ?’ አልኳቸው። ገረምኳቸው። እውቀትንና ግንዛቤን እንዲጨምረኝ አላህን ለመኑልኝ።” [አሶሒሐህ፡ 6/174 - 175]
ከጃቢርም ተመሳሳይ መልእክት ተላልፏል። [ሙስሊም፡ 3010]
በተጨማሪም ዐብዱላህ ብኑ ዑትባህ ብኒ መስዑድ እንዲህ ብለዋል፦
دخلت على عمر بن الخطاب رضي الله عنه بالهاجرة «فوجدته يسبح، فقمت وراءه. فقربني حتى جعلني حذاءه عن يمينه»
“ዑመር ብኑል ኸጧብ ረዲየላሁ ዐንሁ ዘንድ ቀትር ላይ ስገባ ሱና እየሰገዱ አገኘኋቸው። ከኋላቸው ቆምኩኝ። በቀኛቸው በኩል አድርገው አቀረቡኝ።” [ሙወጦእ ማሊክ፡ ሐዲሥ ቁ. 364]
በተጨማሪም ኢብኑ ጁረይጅ ረሒመሁላህ “ 'አንድ ሰው ከአንድ ሰው ጋር ብቻ ሆኖ የሚሰግድ ከሆነ ከየት በኩል ነው የሚሆነው?' ብየ ዐጧእን ጠይቄ ነበር” ይላሉ።
ዐጧእ፦ “በቀኙ በኩል” አሉ።
ኢብኑ ጁረይጅ፦ “አብሮት እስከሚሰለፍ ድረስ በሱው አቅጣጫ ነው የሚሆነው? አንዱ ሌላውን ሳይቀደም?”
ዐጧእ፦ “አዎ!”
ኢብኑ ጁረይጅ፦ “በመሃላቸው ክፍተት እስከማይኖር ድረስ?
ዐጧእ፦ “አዎ!” [ሙሶነፉ ዐብዲረዛቅ፡ ቁ. 3870]
ስለዚህ ሁለት ሆነው በሚሰግዱ ጊዜ ከኢማም ትንሽ ወደ ኋላ መቅረት ምንም እንኳ የደገፉት ዓሊሞች ቢኖሩም ማስረጃ የሚደግፈው ግን አይደለም። ይህንን ማድረግ የተወደደ ቢሆን ኖሮ ተጨባጭ መረጃ ከነብዩ ﷺ ይተላለፍ ነበር። ነገር ግን የለም። ከሶሐቦችም ይገኝ ነበር። ይህም የለም። መረጃ አለመኖሩ መሰረት እንደሌለው ያሳያል። እንደሚታወቀው ነብዩ ﷺ “ስሰግድ እንዳያችሁኝ ስገዱ” ብለዋል። [ቡኻሪ፡ 631] የሳቸው አሰጋገድ ውስጥ ደግሞ ከአንድ ተከታይ ጋር ብቻ ሆነው በሰገዱበት ላይ ትንሽ የተቀደሙበት አልተገኘም። ይልቁንም የተገኘው ከዚህ በተለየ እኩል ጎን ለጎን መቆም ነው። ይሄኛው አቋም ከዘመናችን ዓሊሞች ውስጥ የኢብኑ ባዝ፣ የአልባኒይ እና የኢብኑ ዑሠይሚን አቋም ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
አካባቢን፣ ዘርን፣ ቋንቋን፣ ... መሰረት ያደረገ ጥላቻ እና አጉል ውግንና የጃሂሊያ ባህሪ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ለምንድን ነው የመውሊድ ተቃውሞ ኢኽዋኖችን ምቾት የሚነሳቸው?
~
በርካታ የኢኽዋነል ሙስሊሚን አስተሳሰብ አራማጆች በመውሊድ ቢድዐ ላይ የሚደረገው ዘመቻ ክፉኛ ሲረብሻቸው ይታያሉ፡፡ አብዛኛው የመውሊድ አፈፃፀም ውስጥ ሺርክ እንዳለበት እያወቁ "ለምን በትንንሽ ነገሮች እንጨቃጨቃለን?" ይላሉ። የሺርክ ጉዳይ ለነሱ ከትንንሽ ነገሮች ውስጥ ነው። የተውሒድ ዋጋው ከነሱ ቡድናዊ አላማ በታች ነው። ራሳቸውን መካከለኛ ለማድረግ የመውሊድ ፅንፈኛ ደጋፊዎችን በስሱ ከነኩ በኋላ (እሱም ከስንት አንዴ ከኖረ ነው) ያለ የሌለ ሃይላቸውን መውሊድን በሚነቅፉት ላይ ነው የሚያደርጉት፡፡ መውሊድ ላይ የሚሰነዘረው ተቃውሞ ክፉኛ እንዲረብሻቸው የሚያደርጓቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያክል፡-
1. ኢኽዋነል ሙስሊሚን እንደ ቡድን መሰረቱ ሱፊያ ነው፡፡ የቡድኑ መስራች ሐሰን አልበና የሻዚሊያ ጦሪቃ ቅርንጫፍ የሆነው የ“ሐሷፊያ ጦሪቃ” ተከታይ የነበረ ሲሆን ራሱ እንደገለፀው “የሐሷፊያን አስተሳሰብ የጠገብኩ ሆኜ ወደ ደመንሁር ወረድኩ” ይላል፡፡ [ሙዘኪራቱ ዳዕዋ ወዳዒያ፡ 31 - 34] ከቡድኑ አመራሮች አንዱ የሆነው ሰዒድ ሐዋ “የኢኽዋነል ሙስሊሚን ንቅናቄ ራሱ ሱፊ ነው የመሰረተው፡፡ አሉታዊ ጎኖቹን በመተው የተሶውፍን እውነታ ወስዷል” ይላል፡፡ [ጀውለቱን ፊልፊቅሀይን፡ 154]
አንዳንዶች ይሄኛው አቋሙ ከመመለሱ በፊት የነበረበት ነው ቢሉም እውነታው ግን እንደዚያ አይደለም። እስከ ፍፃሜው ተሶውፍ ላይ እንደዘለቀ ታላላቅ የኢኽዋን ቁንጮዎች መስክረዋል፡፡ ስለዚህ ዛሬ የኢኽዋን ፀሐፊዎች በተለያየ ስልት ከሱፍዮች የሚከላከሉት ከራሳቸው፣ ከመሪዎቻቸው እና ከቡድናቸው ለመከላከል ነው፡፡ ሱፍያ ተነካ ማለት ኢኽዋን ተነካ ማለት ነው፡፡ ሙስሊሞች ሱፍያን ተፀየፉ ማለት የኢኽዋን መሰረቱ ተናጋ ማለት ነው፡፡
አንዳንዶች “እነሱ ነፍስን ማጥራት ላይ የሚያተኩረውን፣ ንፁሁን ተሶውፍ ነው የተከተሉት” ይላሉ፡፡ እውነታው እንደዚያ እንዳልሆነና ተሶውፍን ከነሺርኩ ከነ ግሳንግሱ የሚያራምዱ እንደሆኑ በተከታዮቹ ነጥቦች የምናይ ይሆናል።
2. የቡድኑ መስራች ሐሰን አልበና ረቢዑል አወል አንድ ካለ ጀምሮ እስከ 12 ድረስ መውሊድን ያከብር እንደነበር ራሱ ፅፏል፡፡ [ሙዘኪራ፡ 58] ዛሬም ድረስ ለመውሊድ ሽንጣቸውን ገትረው የሚሟገቱ ኢኽዋኖችን የምናየው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡
3. በርካታ ሱፍዮች ዘንድ ነብዩ ﷺ ከመውሊዱ ጭፈራ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይታመናል፡፡ ነብዩ ﷺ ፈፅሞ ከእንዲህ አይነቱ የባእድ አምልኮ ድግስ ላይ አይገኙም፡፡ ይሄ ቅጥፈታዊ እምነት በኢኽዋነል ሙስሊሚን መስራቹ ሐሰን አልበናም ጭምር ሲስተጋባ የነበረ ነው፡፡ ይሄው እነ ሐሰን አልበና መውሊድ ላይ ሲያንጎራጉሯቸው ከነበሩ ስንኞች ውስጥ እንዲህ የሚል ይገኝበታል፡-
هذا الحبيب مع الأحباب قد حضرا …
… لا شك أن حبيب القوم قد حضرا
“ይህ ወዳጃችን ከወዳጆች ጋር ተገኝቷል።
…
… ያለጥርጥር የሰዎቹ ወዳጅ ተገኝቷል፡፡” [ሐሰን አልበናህ ቢአቅላሚ ተላሚዘቲሂ ወሙዓሲሪሂ፡ 71-72]
ይህ እምነት ዛሬም ድረስ ከሱፍዮች ዘንድ በሰፊው ያለ ነው፡፡ በመውሊድ ጭፈራቸው መሃል መብራት አጥፍተው ነብዩ መጡ ይሉና “መርሐባ ነቢ መርሐባ! መርሐባ!” እያሉ ይዘፍናሉ፡፡ በዚህን ጊዜ ታዳሚው እንዳለ ይቆማል፡፡ ክቡሩ ነቢይ ﷺ የነሱን በሺርክ የተጨማለቀ፣ በውዝዋዜ የታጀበ ድግስ ሊታደሙ መሆኑ ነው፡፡ “አይ ይሄ'ኮ ስማቸው ሲወሳ ለአክብሮት ያክል የሚፈፀም እንጂ ቦታው ላይ ይገኛሉ ተብሎ አይደለም” የሚል ሊኖር ይችላል፡፡ ቦታው ላይ ይገኛሉ የሚል እምነት እንዳለማ ይሄው የሐሰን አልበናን ንግግር አጣቀስኩልህ፡፡ በሃገራችንም በሰፊው የሚታወቅ እምነት ስለሆነ መወሻሸት አያስፈልግም፡፡ ደግሞስ በየደዕዋው ላይ፣ በየ መስጂዱ፣ በየ መድረኩ ስማቸው ሲወሳ ትቆማላችሁ እንዴ? ውሸት!
በነገራችን ላይ ነብዩ ﷺ በህይወት ሳሉ ማንም እንዲቆምላቸው አይወዱም ነበር፡፡ አነስ ብኑ ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- “እነሱ (ሶሐቦች) ዘንድ ዱንያ ውስጥ እንደ ነብዩ ﷺ ሊያዩት የሚወዱት ሰው አልነበራቸውም፡፡ ሆኖም ግን መጥላታቸውን ስለሚያውቁ ለሳቸው አይቆሙም ነበር፡፡” [አሶሒሐ፡ 358]
ሌላ በነገራችን ላይ! ይህንን ነብዩ መጡ እያሉ መነሳትን - የሚሰማ ጠፋ እንጂ - ከመውሊድ አክባሪዎች ውስጥ ሳይቀር የኮነኑት ነበሩ፡፡ ሀይተሚ እንዲህ ይላል፡-“የዚህ አምሳያው ብዙዎች የነብዩ ﷺ ልደትና እናታቸው እሳቸውን መውለዷ ሲወሳ የሚያደርጉት መቆም ሲሆን ይህም ምንም አይነት መረጃ ያልመጣበት ቢድዐ ነው፡፡ ሰዎች ይህን የሚያደርጉት እሳቸውን ﷺ ለማላቅ ነው፡፡ መሃይማኑ ከአዋቂዎቹ በተለየ በዚህ ድርጊታቸው ይታለፋሉ።” [አልፈታዋ አልሐዲሢያ፡ 58]
4. መውሊድን ያክል እጅግ በርካታ ቢድዐዎችን አቅፎ የያዘን ቢድዐ አቅልሎ ማቅረብ ቡድናዊ ስሜት እየጋረዳቸው እንጂ ላስተዋለ ሁሉ በቀላሉ የሚታይ ነው፡፡ በስፍራዎቹ የሚፈፀሙትን አላስፈላጊ የወንድና የሴት ቅልቅል፣ በመስጂድ ውስጥ መጨፈር፣ መስጂዶችን በጫትና በተረፈ ምግብ ማቆሸሽ፣ ዝሙት፣ … ይቅርና ብዙ ከባባድ ሺርክ ይፈፀማል፡፡ ግና በርካታ ኢኽዋኖችን የሺርክ ጉዳይ ሲያስጨንቃቸው አይታይም፡፡ እንጂማ በነቢዩ ﷺ እና በ“ወልዮች” ላይ ብዙ ድንበር ይታለፋል፡፡ በመውሊድ ቦታዎች ላይ ብዙ አይነት ሺርክ ይፈፀማል፡፡ ለቀብር ሱጁድ ይወረዳል፡፡ ጦዋፍ ይደረጋል፡፡ ለበረካ እየተባለ የቀብር አፈር እየተበጠበጠ ይጠጣል፡፡ ከዘመናት በፊት ያለፉ ሙታኖችን ሰዎች ይማፀናሉ፡፡ ስለት ይፈፅማሉ፡፡ ያርዳሉ፡፡ በሺርክ የተሞሉ መንዙማዎች ይቀነቀናሉ፡፡
ይህን ሁሉ ጥፋት አጭቆ የያዘን ቢድዐ የሚያወግዙ ሰዎችን ነው እንደ ጠርዘኛ የሚስሉት፡፡ መውሊድ በመጣ ቁጥር ሰዎችን ከዚህ ጥፋት ስላስጠነቀቁ ነው ጨቅጫቃ የሚያደርጉት፡፡ “ረቢዕን የመጨቃጨቂያ ወር አደረጉት” ይላሉ፡፡ የጥፋቱን ጠንሳሾችና አራጋቢዎች እንዳላዩ እያለፉ ከሺርክና ቢድዐ የሚያስጠነቅቁ ሰዎችን ማብጠልጠል መንስኤው ምን እንደሆነ አይጠፋንም፡፡ እውነት ለህዝብ ብትቆረቆሩ ኖሮ ወገናችንን ከዚህ በሺርክ ከተወረረ በዓል ለማዳን ድርሻ በነበራችሁ ነበር፡፡ “ወላኪን ላ ሐያተ ሊመን ቱናዲ!”
“ይህን ሁሉ ጉድ እያወቁ እንዴት ለመውሊድ ይሟገታሉ?” የሚሉ የዋሆች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ጉዳዩ ከራስ የመከላከል ጉዳይ ነው። የኢኽዋን ቡድን መስራች ሐሰን አልበናና ጭፍሮቹ መውሊድ ላይ ሲያቀነቅኑት ከነበሩ ዜማዎች ውስጥ እነዚህ ነበሩ፡-
هذا الحبيب مع الأحباب قد حضرا - وسامح الكل فيما قد مضى وجرى
“ይህ ወዳጃችን ከወዳጆች ጋር ተገኝቷል፡፡
#ያለፈ_የሆነውን_ሁሉ_ይቅር_ብሏል፡፡” [ሐሰን አልበናህ፡ 71-72]
ይሄ ከኢስላም የሚያስወጣ ትልቁ ሺርክ አይደለምን? ከአላህ ውጭ ወንጀልን የሚምር አለ ወይ?! አላህ ምን እንዳለ አስተውሉ፡-
وَمَنْ يَغْفِرُ الذُّنُوبَ إلاَّ اللهُ
“ከአላህ በስተቀር ወንጀሎችን የሚምረው ማነው?” [ኣሊ ዒምራን፡ 135]
ነብዩም ﷺ "አላህ ሆይ! ... ካንተ በስተቀር ወንጀሎችን የሚምር የለም" ይላሉ። [አልቡኻሪይ፡ 8585] [ሙስሊም፡ 2705]
ኢኽዋን ለተውሒድ ደዕዋ እንቅፋት የሚሆነው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ጉዳዩ የሺርክና የቢድዐ ጉዳይ እንደሆነ እያዩ ''በትንንሽ ነገሮች አንጨቃጨቅ" እውነታውን የሚያስቀይሱበት ምክንያቱ ከዚህ የመነጨ ነው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 28/2012)
=
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
በርካታ የኢኽዋነል ሙስሊሚን አስተሳሰብ አራማጆች በመውሊድ ቢድዐ ላይ የሚደረገው ዘመቻ ክፉኛ ሲረብሻቸው ይታያሉ፡፡ አብዛኛው የመውሊድ አፈፃፀም ውስጥ ሺርክ እንዳለበት እያወቁ "ለምን በትንንሽ ነገሮች እንጨቃጨቃለን?" ይላሉ። የሺርክ ጉዳይ ለነሱ ከትንንሽ ነገሮች ውስጥ ነው። የተውሒድ ዋጋው ከነሱ ቡድናዊ አላማ በታች ነው። ራሳቸውን መካከለኛ ለማድረግ የመውሊድ ፅንፈኛ ደጋፊዎችን በስሱ ከነኩ በኋላ (እሱም ከስንት አንዴ ከኖረ ነው) ያለ የሌለ ሃይላቸውን መውሊድን በሚነቅፉት ላይ ነው የሚያደርጉት፡፡ መውሊድ ላይ የሚሰነዘረው ተቃውሞ ክፉኛ እንዲረብሻቸው የሚያደርጓቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያክል፡-
1. ኢኽዋነል ሙስሊሚን እንደ ቡድን መሰረቱ ሱፊያ ነው፡፡ የቡድኑ መስራች ሐሰን አልበና የሻዚሊያ ጦሪቃ ቅርንጫፍ የሆነው የ“ሐሷፊያ ጦሪቃ” ተከታይ የነበረ ሲሆን ራሱ እንደገለፀው “የሐሷፊያን አስተሳሰብ የጠገብኩ ሆኜ ወደ ደመንሁር ወረድኩ” ይላል፡፡ [ሙዘኪራቱ ዳዕዋ ወዳዒያ፡ 31 - 34] ከቡድኑ አመራሮች አንዱ የሆነው ሰዒድ ሐዋ “የኢኽዋነል ሙስሊሚን ንቅናቄ ራሱ ሱፊ ነው የመሰረተው፡፡ አሉታዊ ጎኖቹን በመተው የተሶውፍን እውነታ ወስዷል” ይላል፡፡ [ጀውለቱን ፊልፊቅሀይን፡ 154]
አንዳንዶች ይሄኛው አቋሙ ከመመለሱ በፊት የነበረበት ነው ቢሉም እውነታው ግን እንደዚያ አይደለም። እስከ ፍፃሜው ተሶውፍ ላይ እንደዘለቀ ታላላቅ የኢኽዋን ቁንጮዎች መስክረዋል፡፡ ስለዚህ ዛሬ የኢኽዋን ፀሐፊዎች በተለያየ ስልት ከሱፍዮች የሚከላከሉት ከራሳቸው፣ ከመሪዎቻቸው እና ከቡድናቸው ለመከላከል ነው፡፡ ሱፍያ ተነካ ማለት ኢኽዋን ተነካ ማለት ነው፡፡ ሙስሊሞች ሱፍያን ተፀየፉ ማለት የኢኽዋን መሰረቱ ተናጋ ማለት ነው፡፡
አንዳንዶች “እነሱ ነፍስን ማጥራት ላይ የሚያተኩረውን፣ ንፁሁን ተሶውፍ ነው የተከተሉት” ይላሉ፡፡ እውነታው እንደዚያ እንዳልሆነና ተሶውፍን ከነሺርኩ ከነ ግሳንግሱ የሚያራምዱ እንደሆኑ በተከታዮቹ ነጥቦች የምናይ ይሆናል።
2. የቡድኑ መስራች ሐሰን አልበና ረቢዑል አወል አንድ ካለ ጀምሮ እስከ 12 ድረስ መውሊድን ያከብር እንደነበር ራሱ ፅፏል፡፡ [ሙዘኪራ፡ 58] ዛሬም ድረስ ለመውሊድ ሽንጣቸውን ገትረው የሚሟገቱ ኢኽዋኖችን የምናየው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡
3. በርካታ ሱፍዮች ዘንድ ነብዩ ﷺ ከመውሊዱ ጭፈራ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይታመናል፡፡ ነብዩ ﷺ ፈፅሞ ከእንዲህ አይነቱ የባእድ አምልኮ ድግስ ላይ አይገኙም፡፡ ይሄ ቅጥፈታዊ እምነት በኢኽዋነል ሙስሊሚን መስራቹ ሐሰን አልበናም ጭምር ሲስተጋባ የነበረ ነው፡፡ ይሄው እነ ሐሰን አልበና መውሊድ ላይ ሲያንጎራጉሯቸው ከነበሩ ስንኞች ውስጥ እንዲህ የሚል ይገኝበታል፡-
هذا الحبيب مع الأحباب قد حضرا …
… لا شك أن حبيب القوم قد حضرا
“ይህ ወዳጃችን ከወዳጆች ጋር ተገኝቷል።
…
… ያለጥርጥር የሰዎቹ ወዳጅ ተገኝቷል፡፡” [ሐሰን አልበናህ ቢአቅላሚ ተላሚዘቲሂ ወሙዓሲሪሂ፡ 71-72]
ይህ እምነት ዛሬም ድረስ ከሱፍዮች ዘንድ በሰፊው ያለ ነው፡፡ በመውሊድ ጭፈራቸው መሃል መብራት አጥፍተው ነብዩ መጡ ይሉና “መርሐባ ነቢ መርሐባ! መርሐባ!” እያሉ ይዘፍናሉ፡፡ በዚህን ጊዜ ታዳሚው እንዳለ ይቆማል፡፡ ክቡሩ ነቢይ ﷺ የነሱን በሺርክ የተጨማለቀ፣ በውዝዋዜ የታጀበ ድግስ ሊታደሙ መሆኑ ነው፡፡ “አይ ይሄ'ኮ ስማቸው ሲወሳ ለአክብሮት ያክል የሚፈፀም እንጂ ቦታው ላይ ይገኛሉ ተብሎ አይደለም” የሚል ሊኖር ይችላል፡፡ ቦታው ላይ ይገኛሉ የሚል እምነት እንዳለማ ይሄው የሐሰን አልበናን ንግግር አጣቀስኩልህ፡፡ በሃገራችንም በሰፊው የሚታወቅ እምነት ስለሆነ መወሻሸት አያስፈልግም፡፡ ደግሞስ በየደዕዋው ላይ፣ በየ መስጂዱ፣ በየ መድረኩ ስማቸው ሲወሳ ትቆማላችሁ እንዴ? ውሸት!
በነገራችን ላይ ነብዩ ﷺ በህይወት ሳሉ ማንም እንዲቆምላቸው አይወዱም ነበር፡፡ አነስ ብኑ ማሊክ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- “እነሱ (ሶሐቦች) ዘንድ ዱንያ ውስጥ እንደ ነብዩ ﷺ ሊያዩት የሚወዱት ሰው አልነበራቸውም፡፡ ሆኖም ግን መጥላታቸውን ስለሚያውቁ ለሳቸው አይቆሙም ነበር፡፡” [አሶሒሐ፡ 358]
ሌላ በነገራችን ላይ! ይህንን ነብዩ መጡ እያሉ መነሳትን - የሚሰማ ጠፋ እንጂ - ከመውሊድ አክባሪዎች ውስጥ ሳይቀር የኮነኑት ነበሩ፡፡ ሀይተሚ እንዲህ ይላል፡-“የዚህ አምሳያው ብዙዎች የነብዩ ﷺ ልደትና እናታቸው እሳቸውን መውለዷ ሲወሳ የሚያደርጉት መቆም ሲሆን ይህም ምንም አይነት መረጃ ያልመጣበት ቢድዐ ነው፡፡ ሰዎች ይህን የሚያደርጉት እሳቸውን ﷺ ለማላቅ ነው፡፡ መሃይማኑ ከአዋቂዎቹ በተለየ በዚህ ድርጊታቸው ይታለፋሉ።” [አልፈታዋ አልሐዲሢያ፡ 58]
4. መውሊድን ያክል እጅግ በርካታ ቢድዐዎችን አቅፎ የያዘን ቢድዐ አቅልሎ ማቅረብ ቡድናዊ ስሜት እየጋረዳቸው እንጂ ላስተዋለ ሁሉ በቀላሉ የሚታይ ነው፡፡ በስፍራዎቹ የሚፈፀሙትን አላስፈላጊ የወንድና የሴት ቅልቅል፣ በመስጂድ ውስጥ መጨፈር፣ መስጂዶችን በጫትና በተረፈ ምግብ ማቆሸሽ፣ ዝሙት፣ … ይቅርና ብዙ ከባባድ ሺርክ ይፈፀማል፡፡ ግና በርካታ ኢኽዋኖችን የሺርክ ጉዳይ ሲያስጨንቃቸው አይታይም፡፡ እንጂማ በነቢዩ ﷺ እና በ“ወልዮች” ላይ ብዙ ድንበር ይታለፋል፡፡ በመውሊድ ቦታዎች ላይ ብዙ አይነት ሺርክ ይፈፀማል፡፡ ለቀብር ሱጁድ ይወረዳል፡፡ ጦዋፍ ይደረጋል፡፡ ለበረካ እየተባለ የቀብር አፈር እየተበጠበጠ ይጠጣል፡፡ ከዘመናት በፊት ያለፉ ሙታኖችን ሰዎች ይማፀናሉ፡፡ ስለት ይፈፅማሉ፡፡ ያርዳሉ፡፡ በሺርክ የተሞሉ መንዙማዎች ይቀነቀናሉ፡፡
ይህን ሁሉ ጥፋት አጭቆ የያዘን ቢድዐ የሚያወግዙ ሰዎችን ነው እንደ ጠርዘኛ የሚስሉት፡፡ መውሊድ በመጣ ቁጥር ሰዎችን ከዚህ ጥፋት ስላስጠነቀቁ ነው ጨቅጫቃ የሚያደርጉት፡፡ “ረቢዕን የመጨቃጨቂያ ወር አደረጉት” ይላሉ፡፡ የጥፋቱን ጠንሳሾችና አራጋቢዎች እንዳላዩ እያለፉ ከሺርክና ቢድዐ የሚያስጠነቅቁ ሰዎችን ማብጠልጠል መንስኤው ምን እንደሆነ አይጠፋንም፡፡ እውነት ለህዝብ ብትቆረቆሩ ኖሮ ወገናችንን ከዚህ በሺርክ ከተወረረ በዓል ለማዳን ድርሻ በነበራችሁ ነበር፡፡ “ወላኪን ላ ሐያተ ሊመን ቱናዲ!”
“ይህን ሁሉ ጉድ እያወቁ እንዴት ለመውሊድ ይሟገታሉ?” የሚሉ የዋሆች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ጉዳዩ ከራስ የመከላከል ጉዳይ ነው። የኢኽዋን ቡድን መስራች ሐሰን አልበናና ጭፍሮቹ መውሊድ ላይ ሲያቀነቅኑት ከነበሩ ዜማዎች ውስጥ እነዚህ ነበሩ፡-
هذا الحبيب مع الأحباب قد حضرا - وسامح الكل فيما قد مضى وجرى
“ይህ ወዳጃችን ከወዳጆች ጋር ተገኝቷል፡፡
#ያለፈ_የሆነውን_ሁሉ_ይቅር_ብሏል፡፡” [ሐሰን አልበናህ፡ 71-72]
ይሄ ከኢስላም የሚያስወጣ ትልቁ ሺርክ አይደለምን? ከአላህ ውጭ ወንጀልን የሚምር አለ ወይ?! አላህ ምን እንዳለ አስተውሉ፡-
وَمَنْ يَغْفِرُ الذُّنُوبَ إلاَّ اللهُ
“ከአላህ በስተቀር ወንጀሎችን የሚምረው ማነው?” [ኣሊ ዒምራን፡ 135]
ነብዩም ﷺ "አላህ ሆይ! ... ካንተ በስተቀር ወንጀሎችን የሚምር የለም" ይላሉ። [አልቡኻሪይ፡ 8585] [ሙስሊም፡ 2705]
ኢኽዋን ለተውሒድ ደዕዋ እንቅፋት የሚሆነው ያለ ምክንያት አይደለም፡፡ ጉዳዩ የሺርክና የቢድዐ ጉዳይ እንደሆነ እያዩ ''በትንንሽ ነገሮች አንጨቃጨቅ" እውነታውን የሚያስቀይሱበት ምክንያቱ ከዚህ የመነጨ ነው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 28/2012)
=
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
ሸይኽ ዐብዱረዛቅ አልበድር - አላህ ከክፉ ይጠበቃቸውና - እንዲህ ብለዋል፦
*إنّ فاقد التوحيد ميّت ولو كان يمشي على الأرض ومحقّق التوحيد هو الذي يحيا الحياة الحقيقية
*يقول الله -جلّ وعلا-: {أَوَ مَن كَانَ مَيْتاً فَأَحْيَيْنَاهُ} [الأنعام:١٢٢]. أي أحييناه بالإيمان والتوحيد"*
“ተውሒድ የሌለው ሰው፣ ምድር ላይ የሚንቀሳቀስ ቢሆን እንኳ፣ የሞተ ነው። እውነተኛውን ህይወት የሚኖረው ተውሒድን ያረጋገጠ ነው። የላቀውና ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ብሏል፡-
“ሙት የነበረና ሕያው ያደረግነው ሰው…” [አል-አንዓም፡ 122]
ይህም ማለት፡- “በኢማንና በተውሒድ ሕያው አደረግነው” ማለት ነው።
🎙️[“የተውሒድ ደረጃ በሙስሊም ህይወት ውስጥ” ከሚል ኹጥባ የተወሰደ።]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
*إنّ فاقد التوحيد ميّت ولو كان يمشي على الأرض ومحقّق التوحيد هو الذي يحيا الحياة الحقيقية
*يقول الله -جلّ وعلا-: {أَوَ مَن كَانَ مَيْتاً فَأَحْيَيْنَاهُ} [الأنعام:١٢٢]. أي أحييناه بالإيمان والتوحيد"*
“ተውሒድ የሌለው ሰው፣ ምድር ላይ የሚንቀሳቀስ ቢሆን እንኳ፣ የሞተ ነው። እውነተኛውን ህይወት የሚኖረው ተውሒድን ያረጋገጠ ነው። የላቀውና ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ብሏል፡-
“ሙት የነበረና ሕያው ያደረግነው ሰው…” [አል-አንዓም፡ 122]
ይህም ማለት፡- “በኢማንና በተውሒድ ሕያው አደረግነው” ማለት ነው።
🎙️[“የተውሒድ ደረጃ በሙስሊም ህይወት ውስጥ” ከሚል ኹጥባ የተወሰደ።]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
የሌሎችን የቅንጦት ህይወት መከታተል መዘዝ አለው
~
በዱንያ ቅንጦት የሚንደላቀቁ ሰዎችን ህይወት መከታተል፣ በቅንጦት ህይወታቸው ላይ መመስጠት ጉዳት አለው።
1ኛ፦ አላህ የዋለልንን ኒዕማ እንድንክድ ወይም እንድንንቅ በር ይከፍታል። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
انْظُرُوا إِلَى مَنْ أَسْفَلَ مِنْكُمْ ، وَلاَ تَنْظُرُوا إِلَى مَنْ هُوَ فَوْقَكُمْ ، فَهُوَ أَجْدَرُ أَنْ لاَ تَزْدَرُوا نِعْمَةَ اللَّهِ.
"ከናንተ በታች ወደሆኑት ተመልከቱ። እንጂ ከናንተ በላይ ወደሆኑት አትመልከቱ። ይሄ በናንተ ላይ ያለውን የአላህን ፀጋ እንዳታናንቁ ዘንድ የተገባ ነውና።" [ሙስሊም ፡ 7540]
2ኛ፦ በወንጀል ሃብት ያጋበሱ ወይም ባልተገባ መልኩ ገንዘባቸውን የሚያወጡ ሰዎችን የቅንጦት አኗኗር መከታተል፣ በቅንጦታቸው መመሰጥ የነሱን ሁኔታ መውደድን፣ እንደነሱ የመሆን ምኞትን ያወርሳል። ይሄ ደግሞ ቀጥታ ባልፈፀሙት ወንጀል ተጠያቂ መሆንን ነው የሚያስከትለው። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
وَعَبْدٌ رَزَقَهُ اللَّهُ مَالًا وَلَمْ يَرْزُقْهُ عِلْمًا، فَهُوَ يَخْبِطُ فِي مَالِهِ بِغَيْرِ عِلْمٍ، لَا يَتَّقِي فِيهِ رَبَّهُ، وَلَا يَصِلُ فِيهِ رَحِمَهُ، وَلَا يَعْلَمُ لِلَّهِ فِيهِ حَقَّهُ، فَهَذَا بِأَخْبَثِ الْمَنَازِلِ» قَالَ: " وَعَبْدٌ لَمْ يَرْزُقْهُ اللَّهُ مَالًا، وَلَا عِلْمًا فَهُوَ يَقُولُ: لَوْ كَانَ لِي مَالٌ لَعَمِلْتُ بِعَمَلِ فُلَانٍ، قَالَ: هِيَ نِيَّتُهُ، فَوِزْرُهُمَا فِيهِ سَوَاءٌ "
"አላህ ገንዘብን የሰጠው ነገር ግን እውቀትን ያልሰጠው ባሪያ አለ። ገንዘቡን ያለ እውቀት ያባክናል። በገንዘቡ ውስጥ ጌታውን አይፈራም፣ ዝምድናን አይቀጥልም፣ እንዲሁም የአላህን ሐቅ አያውቅም። ይህ ሰው በጣም መጥፎ በሆነ ደረጃ ላይ ይገኛል።”
ከዚያም እንዲህ አሉ፦
“ሌላ ደግሞ አላህ ገንዘብንም ሆነ እውቀትን ያልሰጠው ባሪያ አለ። ‘ገንዘብ ቢኖረኝ ኖሮ እንደዚያ ሰው እሠራ ነበር’ ይላል። ይህ ሰው የኒያውን (የሞኞቱን) ያገኛል። ስለዚህ፣ ሁለቱም ኃጢአታቸው (ወንጀላቸው) እኩል ነው።” [ሙስነድ አሕመድ፡ 18031]
ያ ብልሹ በሆነ መልኩ በዱንያ ፀጋ የሚቀናጣው በዱንያ እየተጣቀመ ነው። እዚያ ሳይደርስ በባዶ የሱን አይነት ህይወት የሚመኘው ግን በምኞቱ ብቻ ወንጀለኛ ስለሚሆን ከሁለት ያጣ ጎመን ነው የሚሆነው።
3ኛ፦ እንዲህ አይነት ህይወት ያላቸውን ሰዎች በፊልም፣ በድራማ መከታተል እነሱን መውደድን ሊያስከትል ይችላል። ልብ በሉ! ሰዎችን መውደድ በኸይርም ይሁን በሸር ጎታች ነው። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
المَرْءُ مع مَن أحَبَّ
"ሰው ከሚወደው ጋር ነው።" [ቡኻሪ ፡ 6168] [ሙስሊም ፡ 2640]
4ኛ፦ ደግሞ ደጋግሞ በሌሎች ህይወት ላይ መመሰጥ ለምቀኝነት ሊያጋልጥም ይችላል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
~
በዱንያ ቅንጦት የሚንደላቀቁ ሰዎችን ህይወት መከታተል፣ በቅንጦት ህይወታቸው ላይ መመስጠት ጉዳት አለው።
1ኛ፦ አላህ የዋለልንን ኒዕማ እንድንክድ ወይም እንድንንቅ በር ይከፍታል። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
انْظُرُوا إِلَى مَنْ أَسْفَلَ مِنْكُمْ ، وَلاَ تَنْظُرُوا إِلَى مَنْ هُوَ فَوْقَكُمْ ، فَهُوَ أَجْدَرُ أَنْ لاَ تَزْدَرُوا نِعْمَةَ اللَّهِ.
"ከናንተ በታች ወደሆኑት ተመልከቱ። እንጂ ከናንተ በላይ ወደሆኑት አትመልከቱ። ይሄ በናንተ ላይ ያለውን የአላህን ፀጋ እንዳታናንቁ ዘንድ የተገባ ነውና።" [ሙስሊም ፡ 7540]
2ኛ፦ በወንጀል ሃብት ያጋበሱ ወይም ባልተገባ መልኩ ገንዘባቸውን የሚያወጡ ሰዎችን የቅንጦት አኗኗር መከታተል፣ በቅንጦታቸው መመሰጥ የነሱን ሁኔታ መውደድን፣ እንደነሱ የመሆን ምኞትን ያወርሳል። ይሄ ደግሞ ቀጥታ ባልፈፀሙት ወንጀል ተጠያቂ መሆንን ነው የሚያስከትለው። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
وَعَبْدٌ رَزَقَهُ اللَّهُ مَالًا وَلَمْ يَرْزُقْهُ عِلْمًا، فَهُوَ يَخْبِطُ فِي مَالِهِ بِغَيْرِ عِلْمٍ، لَا يَتَّقِي فِيهِ رَبَّهُ، وَلَا يَصِلُ فِيهِ رَحِمَهُ، وَلَا يَعْلَمُ لِلَّهِ فِيهِ حَقَّهُ، فَهَذَا بِأَخْبَثِ الْمَنَازِلِ» قَالَ: " وَعَبْدٌ لَمْ يَرْزُقْهُ اللَّهُ مَالًا، وَلَا عِلْمًا فَهُوَ يَقُولُ: لَوْ كَانَ لِي مَالٌ لَعَمِلْتُ بِعَمَلِ فُلَانٍ، قَالَ: هِيَ نِيَّتُهُ، فَوِزْرُهُمَا فِيهِ سَوَاءٌ "
"አላህ ገንዘብን የሰጠው ነገር ግን እውቀትን ያልሰጠው ባሪያ አለ። ገንዘቡን ያለ እውቀት ያባክናል። በገንዘቡ ውስጥ ጌታውን አይፈራም፣ ዝምድናን አይቀጥልም፣ እንዲሁም የአላህን ሐቅ አያውቅም። ይህ ሰው በጣም መጥፎ በሆነ ደረጃ ላይ ይገኛል።”
ከዚያም እንዲህ አሉ፦
“ሌላ ደግሞ አላህ ገንዘብንም ሆነ እውቀትን ያልሰጠው ባሪያ አለ። ‘ገንዘብ ቢኖረኝ ኖሮ እንደዚያ ሰው እሠራ ነበር’ ይላል። ይህ ሰው የኒያውን (የሞኞቱን) ያገኛል። ስለዚህ፣ ሁለቱም ኃጢአታቸው (ወንጀላቸው) እኩል ነው።” [ሙስነድ አሕመድ፡ 18031]
ያ ብልሹ በሆነ መልኩ በዱንያ ፀጋ የሚቀናጣው በዱንያ እየተጣቀመ ነው። እዚያ ሳይደርስ በባዶ የሱን አይነት ህይወት የሚመኘው ግን በምኞቱ ብቻ ወንጀለኛ ስለሚሆን ከሁለት ያጣ ጎመን ነው የሚሆነው።
3ኛ፦ እንዲህ አይነት ህይወት ያላቸውን ሰዎች በፊልም፣ በድራማ መከታተል እነሱን መውደድን ሊያስከትል ይችላል። ልብ በሉ! ሰዎችን መውደድ በኸይርም ይሁን በሸር ጎታች ነው። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
المَرْءُ مع مَن أحَبَّ
"ሰው ከሚወደው ጋር ነው።" [ቡኻሪ ፡ 6168] [ሙስሊም ፡ 2640]
4ኛ፦ ደግሞ ደጋግሞ በሌሎች ህይወት ላይ መመሰጥ ለምቀኝነት ሊያጋልጥም ይችላል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
https://www.tgoop.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور