Forwarded from የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
ቋሚ ሲኖዶስ ልዩልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ።
***********************************
ሚያዚያ ፳፪ ቀን ፳፻ ፲ዘ፯ ዓ.ም
+++++++++++++++++++
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
"""""""""""""""""""""""""""
ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል።
በዚህም መሰረት ቋማ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣
2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ፣
3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ፣
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይደረግ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ የዕለቱን ጉባኤ በቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬ አጠናቋል።
መረጃው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ/Department of Public Relation ,EOTC ነው።
***********************************
ሚያዚያ ፳፪ ቀን ፳፻ ፲ዘ፯ ዓ.ም
+++++++++++++++++++
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
"""""""""""""""""""""""""""
ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል።
በዚህም መሰረት ቋማ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣
2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ፣
3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ፣
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይደረግ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ የዕለቱን ጉባኤ በቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬ አጠናቋል።
መረጃው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ/Department of Public Relation ,EOTC ነው።
#ሆናዋለች #ቤዛ
በአምላኳ ተመርጣ ፤ ያውም ለናትነት
ባሪያው ነኝ እያለች ፤ የምታዘዝለት
በሄዋን ትዕቢት ፤ የተዘጋው ገነት
ዳግም ተከፈተ ፤ በማርያም ቅንነት።
እንግዳ የሆነን ፤ የሥጋዌ ሚስጥር
አምና ተቀብላ ፤ በሄዋን ጥርጥር
ዳቢሎስ ካስገባን ፤ የገሀነምወህኒ
ማርያም አሶጣችን ፤ ብላ ይኩነኒ።
ዳግሚት ሰማዩ ፤ ዙፋኑ ለመሆን
የተገባች ሆና ፤ ልጁ ልጇ እንዲሆን
ሄዋን ያጣችውን ፤ ቅድስና ይዛ
ማርያም ለዓለሙ ፤ ሆናዋለች ቤዛ።
✍ አቤል ታደለ
@Melik_weg_gitim
@Melik_weg_gitim
@Melik_weg_gitim
በአምላኳ ተመርጣ ፤ ያውም ለናትነት
ባሪያው ነኝ እያለች ፤ የምታዘዝለት
በሄዋን ትዕቢት ፤ የተዘጋው ገነት
ዳግም ተከፈተ ፤ በማርያም ቅንነት።
እንግዳ የሆነን ፤ የሥጋዌ ሚስጥር
አምና ተቀብላ ፤ በሄዋን ጥርጥር
ዳቢሎስ ካስገባን ፤ የገሀነምወህኒ
ማርያም አሶጣችን ፤ ብላ ይኩነኒ።
ዳግሚት ሰማዩ ፤ ዙፋኑ ለመሆን
የተገባች ሆና ፤ ልጁ ልጇ እንዲሆን
ሄዋን ያጣችውን ፤ ቅድስና ይዛ
ማርያም ለዓለሙ ፤ ሆናዋለች ቤዛ።
✍ አቤል ታደለ
@Melik_weg_gitim
@Melik_weg_gitim
@Melik_weg_gitim
ክርስቶስ ተንስዓ እሙታን***በዓቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን*** አግዓዞ ለአዳም
ሰላም***እም ይእዜስ
ኮነ***ፍስሃ ወሰላም
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!†††
#እንኳን_አምላክን_ለወለደች_ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_ዓመታዊ_የልደት_በዓል_በሰላም_አደረሳችሁ_አደረሰን
በግንቦት አንድ በዚህችም ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት፡፡ ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ። ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ፤ በዚያ ወራት የመካኖችን መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና ። እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኀዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር ። ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለአለም ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም ሐሳባቸውን ተመለከተ ።ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለም ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው ። ነፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ ለተመሰገነች ሚስቱም ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት፤ ቃሉ እውነት እንደሆነች እርሷም አመነች ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ።የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች። ከዚህም በኋላ ይቺን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች ስሟንም ማርያም ብላ ሰየመቻት ትርጓሜውም እመቤት ነው ደግሞም ሀብትና ስጦታ ማለት ነው ። በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ናት ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን ።
©ስንክሳር ዘወርኀ ግንቦት ፩
አሰሮ ለሰይጣን*** አግዓዞ ለአዳም
ሰላም***እም ይእዜስ
ኮነ***ፍስሃ ወሰላም
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!†††
#እንኳን_አምላክን_ለወለደች_ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም_ዓመታዊ_የልደት_በዓል_በሰላም_አደረሳችሁ_አደረሰን
በግንቦት አንድ በዚህችም ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት፡፡ ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ። ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ፤ በዚያ ወራት የመካኖችን መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና ። እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኀዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር ። ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለአለም ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም ሐሳባቸውን ተመለከተ ።ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለም ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው ። ነፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ ለተመሰገነች ሚስቱም ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት፤ ቃሉ እውነት እንደሆነች እርሷም አመነች ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ።የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች። ከዚህም በኋላ ይቺን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች ስሟንም ማርያም ብላ ሰየመቻት ትርጓሜውም እመቤት ነው ደግሞም ሀብትና ስጦታ ማለት ነው ። በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ናት ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋራ ለዘላለሙ ይኑር አሜን ።
©ስንክሳር ዘወርኀ ግንቦት ፩
#ማርያም_ተወለደች
በዚች እለት
ከሐናና ከኢያቄም ፤ እድሜያቸው ካረጀ
ልዑል ለማደሪያው ፤ መቅደስ አዘጋጀ
ከዕሴይ የዘር ግንድ ፤ እቤቱን አነፀ
ከማይነቅዝ እንጨት ፤ ታቦቱን ቀረፀ።
በዚች እለት
እንደ እንግዳ ደራሽ ፤ ድንገት ያላየናት
አስቀድሞ ትንቢት ፤ የተነገረላት
በሊባኖስ አድባር ፤ ተወለደች ሴት ልጅ
ፊቷ የሚያበራ ፤ ከፀሐይ ሰባት እጅ ።
በዚች እለት
በነፍስም በሥጋ ፤ ነውር የሌለባት
መልክና ደም ግባት ፤ የተባበረላት
ጸጋን የተመላች ፤ በዕንቁ ያጌጠች
የመመኪያችን ዘውድ ፤ ማርያም ተወለደች።
ታዲያ ይህችን እለት ፤
እንዴት እናክብራት ፤ በምን ያህል ድምቀት
አይደለም የሌላ ፤ የተራ ሰው ልደት
እንዴት ባለ ቅኔ ፤ ጠቢቡስ ያገልግል
ልደቷ ብቻውን ፤ ድንቅ ነው የድንግል።
እንኳን አደረሳችሁ!
✍️ አቤል ታደለ @abeltadele
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
በዚች እለት
ከሐናና ከኢያቄም ፤ እድሜያቸው ካረጀ
ልዑል ለማደሪያው ፤ መቅደስ አዘጋጀ
ከዕሴይ የዘር ግንድ ፤ እቤቱን አነፀ
ከማይነቅዝ እንጨት ፤ ታቦቱን ቀረፀ።
በዚች እለት
እንደ እንግዳ ደራሽ ፤ ድንገት ያላየናት
አስቀድሞ ትንቢት ፤ የተነገረላት
በሊባኖስ አድባር ፤ ተወለደች ሴት ልጅ
ፊቷ የሚያበራ ፤ ከፀሐይ ሰባት እጅ ።
በዚች እለት
በነፍስም በሥጋ ፤ ነውር የሌለባት
መልክና ደም ግባት ፤ የተባበረላት
ጸጋን የተመላች ፤ በዕንቁ ያጌጠች
የመመኪያችን ዘውድ ፤ ማርያም ተወለደች።
ታዲያ ይህችን እለት ፤
እንዴት እናክብራት ፤ በምን ያህል ድምቀት
አይደለም የሌላ ፤ የተራ ሰው ልደት
እንዴት ባለ ቅኔ ፤ ጠቢቡስ ያገልግል
ልደቷ ብቻውን ፤ ድንቅ ነው የድንግል።
እንኳን አደረሳችሁ!
✍️ አቤል ታደለ @abeltadele
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
አጠገብህ ልሆን ደሞ ርቅሀለሁ
ወይ ገብቼ አልሞቀኝ የመለኮት ክንድህ
ምን ያህል ይርቃል ልቤ ከመንገድህ
አለምንም ቀረብ
አምላኬንም ቀረብ
ደግሞ ጠጋ ማለት ደግሞ እሸሻለሁ
ሀጥያቴን አልተዉም መፅደቅም እሻለሁ
ምን ጉድ ነኝ ?
ምንጉድ ነኝ?
ምን ጉድ ነዉ ይሄ መሀል መሆን
ምን ድረስ ነዉ የሚያስጉዘኝ
እስከመጨረሻዉ መች ነዉ የምትይዘኝ
አይበቃኝም ወይ?
አይበቃኝም ወይ መሠባበሬ
ከቤቴ ይበልጣል የፍርሀት አጥሬ
ትዕቢቴ ልቤን አንቆ
የቱጋ ነዉ የምሰብረኝ?
እራቀብኝ ያ ደማስቆ
እምን ጋ ነዉ ምደነግጥ
በነዉሬ በኋጢያቴ
ወየዉልኝ ለጥጋቤ ወየዉልኝ ለትዕቢቴ
ድካም ለሊቱን እንባ እየጋተኝ
የሰበረኝን ይህንዓለም መጣል ያቃተኝ
በአንድ ሰዉነቴ ሁለት መልክ ያለኝ
ጌታዬ ንገረኝ እኔ የትኛዉ ነኝ?
✍ ኤልያስ ሽታሑን
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
#Join_and_Share🙏
ወይ ገብቼ አልሞቀኝ የመለኮት ክንድህ
ምን ያህል ይርቃል ልቤ ከመንገድህ
አለምንም ቀረብ
አምላኬንም ቀረብ
ደግሞ ጠጋ ማለት ደግሞ እሸሻለሁ
ሀጥያቴን አልተዉም መፅደቅም እሻለሁ
ምን ጉድ ነኝ ?
ምንጉድ ነኝ?
ምን ጉድ ነዉ ይሄ መሀል መሆን
ምን ድረስ ነዉ የሚያስጉዘኝ
እስከመጨረሻዉ መች ነዉ የምትይዘኝ
አይበቃኝም ወይ?
አይበቃኝም ወይ መሠባበሬ
ከቤቴ ይበልጣል የፍርሀት አጥሬ
ትዕቢቴ ልቤን አንቆ
የቱጋ ነዉ የምሰብረኝ?
እራቀብኝ ያ ደማስቆ
እምን ጋ ነዉ ምደነግጥ
በነዉሬ በኋጢያቴ
ወየዉልኝ ለጥጋቤ ወየዉልኝ ለትዕቢቴ
ድካም ለሊቱን እንባ እየጋተኝ
የሰበረኝን ይህንዓለም መጣል ያቃተኝ
በአንድ ሰዉነቴ ሁለት መልክ ያለኝ
ጌታዬ ንገረኝ እኔ የትኛዉ ነኝ?
✍ ኤልያስ ሽታሑን
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
#Join_and_Share🙏
#ያ_ውሻ ...
ሰዎች ያባረሩት
ከመንደር ያስወጡት የሌለው መድረሻ
አቻውን ፍለጋ ሚንከራተት ዘውትር
በጫካ በጥሻ ....
የጭንቅ አማላጇ
ምህረት ተጠምቶ ጫማሽን ሚናፍቅ
እኔ ነኝ ያ ውሻ .....
:
መቼ ትመጫለሽ
መች ታልፍያለሽ በዚያ በተጣልኩበት በር
መባዘን መድከሜ ፊትሽን አይቼ
መቼ ነው የሚቀር ???
ረዘመ ቀኑ ....
መላው ጠፋ ሀሳቤ አላልቅ አለኝ ሌቱ
ጉልበቴ ሲደክም .....
ወዜ ሲንጠፈጠፍ በረታ እንግልቱ
ከወርቁ ጫማሽ ላይ
ውሃ ምታጠጭኝ
መች ነው አዛኝቱ ?
መከረኛው ልጅሽ ጥቂት ቅድስና
ወይ ምግባር የሌለኝ
ባውቅም እንደ ግብሬ
ጫማሽን ልነካ አቅም እንደሌለኝ
አምናለሁ ስጠራሽ አልፈሽኝ አትሄጂም
አትጨክኚብኝም
ለውሻ ሚራራ እንስፍስፍ አንጀትሽ
ጥርኝ አይነሳኝም !
:
ግን ደግሞ ከብዶኛል
ግን ደግሞ ጠምቶኛል
ውሃ ልታጠጪኝ መቼ ትመጫለሽ
ያ ጫማሽ ናፍቆኛል 😔😔
By @Kiyorna
( ፲፱ - ፮ - ፳፲፮ )
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
#Join_and_Share 🙏
ሰዎች ያባረሩት
ከመንደር ያስወጡት የሌለው መድረሻ
አቻውን ፍለጋ ሚንከራተት ዘውትር
በጫካ በጥሻ ....
የጭንቅ አማላጇ
ምህረት ተጠምቶ ጫማሽን ሚናፍቅ
እኔ ነኝ ያ ውሻ .....
:
መቼ ትመጫለሽ
መች ታልፍያለሽ በዚያ በተጣልኩበት በር
መባዘን መድከሜ ፊትሽን አይቼ
መቼ ነው የሚቀር ???
ረዘመ ቀኑ ....
መላው ጠፋ ሀሳቤ አላልቅ አለኝ ሌቱ
ጉልበቴ ሲደክም .....
ወዜ ሲንጠፈጠፍ በረታ እንግልቱ
ከወርቁ ጫማሽ ላይ
ውሃ ምታጠጭኝ
መች ነው አዛኝቱ ?
መከረኛው ልጅሽ ጥቂት ቅድስና
ወይ ምግባር የሌለኝ
ባውቅም እንደ ግብሬ
ጫማሽን ልነካ አቅም እንደሌለኝ
አምናለሁ ስጠራሽ አልፈሽኝ አትሄጂም
አትጨክኚብኝም
ለውሻ ሚራራ እንስፍስፍ አንጀትሽ
ጥርኝ አይነሳኝም !
:
ግን ደግሞ ከብዶኛል
ግን ደግሞ ጠምቶኛል
ውሃ ልታጠጪኝ መቼ ትመጫለሽ
ያ ጫማሽ ናፍቆኛል 😔😔
By @Kiyorna
( ፲፱ - ፮ - ፳፲፮ )
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
#Join_and_Share 🙏
#ልዩ_ምሥክር_ናት
እንደ ከዚህ ቀደም ፤ አብሳሪው መልአክ
ለሌሎች እንዳለው ፤ ከአርያም ሲላክ
ሠምቶሻል እግዚአብሔር ፤ የልብሽ መሻቱን
አላለም ለድንግል ፤ ሲጀምር ብሥራቱን ።
ምክንያቱም እሷ ፤
ለምና አታውቅም ፤ ሥለትም ተስላ
የፈጣሪ እናት ፤ እኔ ልሁን ብላ ።
ምክንያቱም እሷ ፤
እንደ ደናግላን ፤ ድንገት አሁን ካሁን
ጠብቃ አታውቅም ፤ ለመውለድ መሲሁን ።
ምክንያቱም እሷ ፤
እንደነ ኤልሳቤጥ ፤ ወይም እንደ ሐና
ልጅ እንኳን ለማግኘት ፤ አታውቅም ተማፅና ።
ምክንያቱም እሷ ፤
መሆኑ አልገባት ፤ እንድትሆን እልፍኙ
ገና በልጅነት ፤ ያረጋት መናኙ ።
ምክንያቱም እሷ ፤
በልቧ ጸንሳው ፤ መኖርን ነው እንጂ
መባል አታስብም ፤ አምላክን ውለጂ ።
ምክንያቱም እሷ ፤
ምረጠኝ ሳትለው ፤ ወዶ የመረጣት
አንዳችም ሳትሻ ፤ ሁሉ የተሰጣት
የእርሱ ድንቅ ሥራ ፤ ልዩ ምሥክር ናት ።
✍ አቤል ታደለ
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
JoinandShare🙏
እንደ ከዚህ ቀደም ፤ አብሳሪው መልአክ
ለሌሎች እንዳለው ፤ ከአርያም ሲላክ
ሠምቶሻል እግዚአብሔር ፤ የልብሽ መሻቱን
አላለም ለድንግል ፤ ሲጀምር ብሥራቱን ።
ምክንያቱም እሷ ፤
ለምና አታውቅም ፤ ሥለትም ተስላ
የፈጣሪ እናት ፤ እኔ ልሁን ብላ ።
ምክንያቱም እሷ ፤
እንደ ደናግላን ፤ ድንገት አሁን ካሁን
ጠብቃ አታውቅም ፤ ለመውለድ መሲሁን ።
ምክንያቱም እሷ ፤
እንደነ ኤልሳቤጥ ፤ ወይም እንደ ሐና
ልጅ እንኳን ለማግኘት ፤ አታውቅም ተማፅና ።
ምክንያቱም እሷ ፤
መሆኑ አልገባት ፤ እንድትሆን እልፍኙ
ገና በልጅነት ፤ ያረጋት መናኙ ።
ምክንያቱም እሷ ፤
በልቧ ጸንሳው ፤ መኖርን ነው እንጂ
መባል አታስብም ፤ አምላክን ውለጂ ።
ምክንያቱም እሷ ፤
ምረጠኝ ሳትለው ፤ ወዶ የመረጣት
አንዳችም ሳትሻ ፤ ሁሉ የተሰጣት
የእርሱ ድንቅ ሥራ ፤ ልዩ ምሥክር ናት ።
✍ አቤል ታደለ
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
@Melikt_weg_gitim
JoinandShare🙏
📌 ድንግልና ለምን "ዓይን" እንደተባለ የሚያውቅ ማን ነው ❓
❖ ድንግልና የአንድን ሰው ማንነት እስከ መወሰን ወይም ገልጦ እስከ ማሳየት የሚደርስ መሠረታዊ ምሥጢር እንድትይዝ ሆና በመፈጠሯ አይደለምን ? ዓይን ታያለች እርሷም ትታያለች፡፡
❖ አንቺ ሴት ከጋብቻሽ በፊት ድንግልናሽን ያጠፋሽው ከሆነ ስታገቢ ባልሽን በምን ታዪዋለሽ ? ድንግልና "ዓይን" ተብላለችና፤ ባልም ድንግልናውን ጠብቆ ካልኖረ ረቂቅ መነጽር ድንግልና የለውምና ሚስቱን በምኑ ይመለከታታል? ዛሬ ዛሬ ብዙ ባልና ሚስቶች በጥቃቅን አለመግባባቶች ለአንድ ቀን እንኳን ተያይተው የማያውቁ ያህል የሚሆኑትና የሚኳረፉት ምናልባት ድንግልናን መጠበቅ ስለቀረ ሕገ እግዚአብሔርም እየፈረሰ ስለመጣ ይሆን ? በማለት መጠየቅ አስተዋይነት ነው፡፡
❖ ድንግልና ሁሉን አርቆ የሚያሳይ ከፍተኛ ቦታ ነው፤ የኑሮ ደረጃቸውን በድንግልና ሆነው መርምረውና ተመልክተው ያገቡ ሰዎች አይጸጸቱም ማለትም አንድ ሰው ደረጃው ማግባትም ይሁን መመንኮስ በሚገባ ለይቶ ማወቅ የሚችለው ንጽሕናውን ጠብቆ ለመኖር ከቻለ ብቻ ነው፡፡
❖ መጽሐፍ ቅዱስ "የሰውነት መብራት ዓይን ናት፡፡ እንግዲህ ዓይንህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ብሩህ ይሆናል፤ ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል ይላል፡፡
📖 ማቴ 22፥23
❖ እንደዚሁም ሁሉ በዓይን የተመሰለች ድንግልናም በሕገ ወጥነት በዝሙት ሥራ ከጠፋች አንደ ሰው ሰውነቱ ሁሉ እንደጨለመበት ሊያምን ይገባዋል፤ ምክንያቱም ድንግልና ሃይማኖትና ምግባር መሠረታቸውን ለቀው እንዳይናጉ የሚያደርግ ጽኑ መሠረት ነውና፤ ማለትም አመለካከት ፣ አነጋገርና አሠራር ሚዛናቸውን እንዳልሳቱ ከድንግልና አጠባበቅ አንጻር መናገር ይቻላል፤ ስለዚህ ድንግልና "ዓይን" ቢባል ያንሰዋል እንጂ አይበዛበትም፡፡
❖ ብዙ ጊዜ ድንግልና ለሴቶች የሚነገረው በጉልህ ምልክት የሚታወቀው በእነርሱ ስለሆነ ነው፤ ነገር ግን ድንግልና ለወንዶችም የጸና ተጠቃሽ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ
✍️ "ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው ፣ ድንግሎች ናቸው" በማለት ከትቦ ይዟል፡፡
📖 ራዕ 14፥4
🔔 ንስሀ ግን የወደቁትን ታነሳለች ቀማኛውን መጽዋች፣ ዘማዊውንም ድንግል ታደርጋለች
📌 አዘጋጅ
® ዲ/ን ቡሩክ ይርጋ
📌ምንጭ
✍️በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ
📚ሕይወተ ወራዙት
✍ "አንተ ሰው ቃለ እግዚአብሔርን ተማር፤ ባትለወጥም ዝም ብለህ ተማር! ኹልጊዜ ተማር። ላትስተካከል ትችላለህ፤ ላትለወጥ ትችላለህ፤ ግን ተማር፤ ቢያንስ ቢያንስ ጥሩ ሰው እንኳን ባትኾን ራስህን ለመውቀስ የምትችልበት ዓቅም ታገኛለህ፤ ካልተማርክ ግን ራስህን እንኳን መውቀስ የምትችልበት ዓቅም አታገኝም፤ ስለዚህ ተማር ስትማር ቢያንስ ኃጢአት እንኳን ስትሠራ ራስህን እየወቀስክ ትሠራለና፤ ይህች የንስሐ በር ትኾንልሃለች፤ አንድ ቀን ወደ ንስሐም ትመራሃለች"
📘ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን
❖ ድንግልና የአንድን ሰው ማንነት እስከ መወሰን ወይም ገልጦ እስከ ማሳየት የሚደርስ መሠረታዊ ምሥጢር እንድትይዝ ሆና በመፈጠሯ አይደለምን ? ዓይን ታያለች እርሷም ትታያለች፡፡
❖ አንቺ ሴት ከጋብቻሽ በፊት ድንግልናሽን ያጠፋሽው ከሆነ ስታገቢ ባልሽን በምን ታዪዋለሽ ? ድንግልና "ዓይን" ተብላለችና፤ ባልም ድንግልናውን ጠብቆ ካልኖረ ረቂቅ መነጽር ድንግልና የለውምና ሚስቱን በምኑ ይመለከታታል? ዛሬ ዛሬ ብዙ ባልና ሚስቶች በጥቃቅን አለመግባባቶች ለአንድ ቀን እንኳን ተያይተው የማያውቁ ያህል የሚሆኑትና የሚኳረፉት ምናልባት ድንግልናን መጠበቅ ስለቀረ ሕገ እግዚአብሔርም እየፈረሰ ስለመጣ ይሆን ? በማለት መጠየቅ አስተዋይነት ነው፡፡
❖ ድንግልና ሁሉን አርቆ የሚያሳይ ከፍተኛ ቦታ ነው፤ የኑሮ ደረጃቸውን በድንግልና ሆነው መርምረውና ተመልክተው ያገቡ ሰዎች አይጸጸቱም ማለትም አንድ ሰው ደረጃው ማግባትም ይሁን መመንኮስ በሚገባ ለይቶ ማወቅ የሚችለው ንጽሕናውን ጠብቆ ለመኖር ከቻለ ብቻ ነው፡፡
❖ መጽሐፍ ቅዱስ "የሰውነት መብራት ዓይን ናት፡፡ እንግዲህ ዓይንህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ብሩህ ይሆናል፤ ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል ይላል፡፡
📖 ማቴ 22፥23
❖ እንደዚሁም ሁሉ በዓይን የተመሰለች ድንግልናም በሕገ ወጥነት በዝሙት ሥራ ከጠፋች አንደ ሰው ሰውነቱ ሁሉ እንደጨለመበት ሊያምን ይገባዋል፤ ምክንያቱም ድንግልና ሃይማኖትና ምግባር መሠረታቸውን ለቀው እንዳይናጉ የሚያደርግ ጽኑ መሠረት ነውና፤ ማለትም አመለካከት ፣ አነጋገርና አሠራር ሚዛናቸውን እንዳልሳቱ ከድንግልና አጠባበቅ አንጻር መናገር ይቻላል፤ ስለዚህ ድንግልና "ዓይን" ቢባል ያንሰዋል እንጂ አይበዛበትም፡፡
❖ ብዙ ጊዜ ድንግልና ለሴቶች የሚነገረው በጉልህ ምልክት የሚታወቀው በእነርሱ ስለሆነ ነው፤ ነገር ግን ድንግልና ለወንዶችም የጸና ተጠቃሽ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ
✍️ "ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው ፣ ድንግሎች ናቸው" በማለት ከትቦ ይዟል፡፡
📖 ራዕ 14፥4
🔔 ንስሀ ግን የወደቁትን ታነሳለች ቀማኛውን መጽዋች፣ ዘማዊውንም ድንግል ታደርጋለች
📌 አዘጋጅ
® ዲ/ን ቡሩክ ይርጋ
📌ምንጭ
✍️በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ
📚ሕይወተ ወራዙት
✍ "አንተ ሰው ቃለ እግዚአብሔርን ተማር፤ ባትለወጥም ዝም ብለህ ተማር! ኹልጊዜ ተማር። ላትስተካከል ትችላለህ፤ ላትለወጥ ትችላለህ፤ ግን ተማር፤ ቢያንስ ቢያንስ ጥሩ ሰው እንኳን ባትኾን ራስህን ለመውቀስ የምትችልበት ዓቅም ታገኛለህ፤ ካልተማርክ ግን ራስህን እንኳን መውቀስ የምትችልበት ዓቅም አታገኝም፤ ስለዚህ ተማር ስትማር ቢያንስ ኃጢአት እንኳን ስትሠራ ራስህን እየወቀስክ ትሠራለና፤ ይህች የንስሐ በር ትኾንልሃለች፤ አንድ ቀን ወደ ንስሐም ትመራሃለች"
📘ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን
በመነን የሃገር ባህል ልብስ
ሽፎኖች
አፍሪካ ጨርቅ
ከፋይ
የፈለጉትን ዲዛይን መርጠው ማዘዝ ይችላሉ
ለማዘዝ በዚህ ስልክ ይደውሉ:-
0923251317 ምትክ ዲዛይን
ሽፎኖች
አፍሪካ ጨርቅ
ከፋይ
የፈለጉትን ዲዛይን መርጠው ማዘዝ ይችላሉ
ለማዘዝ በዚህ ስልክ ይደውሉ:-
0923251317 ምትክ ዲዛይን