Telegram Web
+ሰኔ ሚካኤል+
አምና የዛሬ አመት ፥ያልጠከረ ልጅ ፥ታቅፌ በእጆቼ፤
ከቤትህ ባቀና አንተን፥ ልሳለምህ ከደጅህ መጥቼ።
እግሮቼ ሳያውቁ ቢሰነካከሉ፥ ጉድጓድ ቢቀናቸው፤
እንዳይሰበሩ መራመጃ ምንጣፍ፥ ሚካኤል ሆንካቸው።
የተከፈተውን የገባሁበትን፥ ጉድጓድ ዘጋህና፤
ከቤቴ መለስከኝ ንግስህን፥ አንግሼ ገባሁኝ በደህና፤
ባህራን አደገ፥ ዳግም ጠነከረ፤
ሚካኤል ከጉድጓድ፥ ጠብቆን ነበረ፤
ያንተ የኔ ጌታ ይጠብቅ ነበረ፥ ያፀድቅ ነበረ፤
ያንተ አምላክ፥ እግዚአብሄር ያሳድግ ነበረ።
በበጎ እንዳስብህ፥ ዛሬን በትዝታ፤
መላኩ ሚካኤል ፥አለብኝ ውለታ።
አንተ ዘጋህልኝ፥ ጫፌ ሳይነካ፤
ምስጋናዬን ውሰድ፥ መባዬንም እንካ።
የማትረሳ መላክ፥ ጠባቂ ነህና፤
አረሳህም እኔ፥ አልረሳህምና፤
የተከፈተውን፥ ጉድጓድ ዘጋህና፤
አመቱ ሲደርስ፥ አሰብኩህ በደህና።
አልረሳም አንተን፥ በሰኔ በሰኔ፤
ሚካኤል ወዳጄ፥ ምርኩዜ ነህ ለኔ።
++++
"በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ"
©ታዜና
      #መንፈሳዊ_ግጥሞች
      www.tgoop.com/Menfesawigetmoch
Forwarded from ♱ ባሕራን ♱
ኢትዮጵያን "ኤልዛቤል" በማለት የጠራው እና ከቤተክርስቲያን ጋር የዶግማ ልዩነት አለን በማለት የተናገረው መናፍቁ "አባ" ሠረቀብርሃን ወልደሳሙኤል ከቤተክርስቲያን ተወግዞ ተለየ !

ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ]

እመቤታችን ጥንተ አብሶ አለባት በሚለው ትምህርቱ የሚታወቀው መናፍቁ "አባ" ሠረቀብርሃን ወልደሳሙኤል ከቤተክርስቲያን አንድነት ተወግዞ መለየቱ ተገለጸ።

በቀድሞ ስሙ አባ ሠረቀብርሃን ወልደሳሙኤል የተባለው ግለሰብ በተለያዩ ጊዜያት በምንፍቅና ትምህርቱ የሚታወቀው ፤ በቅርቡ ደግሞ ከቀኖና ውጭ "መንበረ ሰላማ" በሚል በሚጠ'ራው መሠረት አልባ እና ከቤተክርስቲያን ቅዱስ ትውፊት ያፈነገጠ እንቅስቃሴ ጠንሳሽ እና አደራጅ በመሆን እተየተንቀሳቀሰ የሚገኝ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በግልጽ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር የዶግማ ልዩነት አለን በማለት መግለጹ ይታወሳል።

በዚህም መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ ግለሰቡን አውግዞ መለየቱን በዛሬው ዕለት አስታውቋል።

[ TMC ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
-እንመለስ-
'
ወዴት ናችሁ ቢለን፥
ጌታ ቢጠይቀን?
መልሳችን ምንድንው፥
ወዴት ነው ምንለው፤
የጸጋ ልብሳችን፥ ከላያችን ወልቋል፤
እውነት፥ ህይወት፥ መንገድ፥ ዛሬ ከኛ ርቋል።

እንመለስ ወደ እውነት ፥ሀሰት ቅጥፈትን እናርቀው፤
እንመለስ ወደ ህይወት ፥የሞትን ሀይል እናድቅቀው፤
እንመለስ ወደ መንገድ፥ጉዳናውን እንልቀቀው፤ 
እንመለስ ወደ እግዚአብሄ፥ ይመጣል እንጠብቀው።
++++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   www.tgoop.com/Menfesawigetmoch
https://youtu.be/4s9LW4mhUqQ?si=EzwAsMh6cRJFCZHK
(መምህር ኢዮብ ይመኑ)
-እጠብቅሀለሁ-
እጠብቅሀለሁ በመጠቂያዬ፤
ትመጣለህና ሳትረሳ ጌታዬ።
ቀናት ቢያሰለቹ፥ ቢቆጠር ዘመናት፤
አምንሀለሁ ነፍሴን፥ እንደማትተዋት።
በምንም በየትም። በሁሉም ሁኔታ፤ 
እጠብቅሀለሁ፥ በእድሜ ጀምበር ማታ።

አማርሬህ፥ አኩርፌህም፥ አምቼህም፥ እኔ አውቃለሁ፤
ትግስትህን ሳልታገስ፥ ብዙ ነገር ብዬሀለሁ፤
ለዘመኔ እሾህ ሆኜ፥ ከቤትህም ጠፍቻለሁ፤
አትድረስብኝ አልደርስም፥ ብዬ በስምህ ምዬ አውቃለሁ።
ማታ እግሮቼን አጥበህ፥ በትህትና ለመከርከኝ፤
አላውቀውም፥ ማነው እሱ፥ ብዬ ባፌ መሰከርኩኝ።
ስታበራ ብቻ ሳይሆን፥ ጌቴሴማኒ ፀዳል ስትሆን፤
ቀያፋም ቤት መጥቻለሁ፥ ስትገረፍ ጅራፍ ልሆን።

ለካ እኔ ፈጠንኩ እንጂ፥ አንተ እኮ አልዘገየህም፤
በሰዓትህ ትመጣለህ፥ ቆየህ ምነው? አልልህም። 
እንደ ዕንባቆም እጮሀለሁ፥ አምላኬ ሆይ እልሀለሁ፤
ስትሰጠኝ ብቻ ሳይሆን፥ ብትከለክለኝም እጠብቅሀለሁ።
ፀጋህን ከኔ ውሰድልኝ፥ እኔ አንተን ከማጣህ፤
እንደዘኪዎስ ከዛፍ ልውጣ፥ ቤቴ ግባ አይቼህ።
በዝምታ ልቤን ክፈት፥ ግባ ማነው? ሳልልህ፤
አንተ ብቻ ናልኝ እንጂ፥ ከቤቴ ጋር ላምልክህ።


ደሞ እንዲህም ብዬሀለሁ፥ መቼ ጠይቄው መች መለሰ፤
ምነው ልቦናን ነሳኝ፥ እኔን ከሰው አሳነሰ።
ለምንድነው ያዋረደኝ፥ ዝም የሚለው እንዲህ ስሆን፤
ለካ አንተ የምትመጣው፥ እንደ አልዓዛር አፈር ስሆን፤
ለካ ህመም አይደለም፥ ሞትም አይደል የሚያቆምህ፤
በአራት ቀኔ ሳትፀየፍ፥ መቃብሬን ትከፍታለህ።
ለካ መሽቶም ትመጣለህ፥ እድሜ ዘመን አይገታህም፤
የጠበቀህ እርፍ ይላል፥ ላንተ ምንም አይሳንህም።
:
እንደ ዮሴፍ ብጠላ፥ በወንድሞቼ ብከዳ፤
በሰላሳ ዲናር ብሸጥ፥ ብንከራተት ምድረበዳ።
የአባቴ አይንም ቢፈስ፥ ቢናፍቀው የልጅ መልኬን፤ 
የሀሰት ፍርድ ቢፈርዱብኝ፥ ብወረወር እድሜ ልኬን።
ፍርድ አጣመው ቢያንገላቱ፥ ፍርዱም ቢሆን እድሜ ይፍታ፤
ማንም ዳግም አያስረኝም፥ አንተ መተህ ስትፈታ።
አንተ ምን ይሳንሀል፥ በወህኒው በኩል በር አለህ።
በጲጢፋራ መንበር፥ ልታነግሰኝ ትመጣለህ

ታማኝ ነህ  ለጠበቀህ፥ ማህጸንን ትፈታለህ፤
ሲስቁብኝ ልትባርከኝ፥ በመቅደስህ ትመጣለህ።
መካን ብባል የተጣለች፥ ስሜም እንኳ በቅሎ ቢሆን፤
መቶ ፍሬ ይገኝብኝ፥ አብዛኝና ለዘር ልሁን።
የሀናን ለቅሶ የሰማህ፥ የኤልሳቤትን እንባ ያበስክ፤
ልጅ የጠየቀችህን፥ በልጆች የምትባርክ፤
ዛሬ አለሁ ያንተ ሀና፥ ዛሬም አለሁ ያንተ ኤልሳቤት፤
እንደ ዮሀንስ ባርከህ ስጠኝ፥ ባንተ ጊዜ በለኝ አቤት።
:
መሮኛል ስልህ ወደላይ፥ የበታቼን ሳላየው፤ 
አንተ ባልቆረትከው ቀን፥ የራሴን ሞት የተመኘው።
ምነው መታገስ ከበደኝ፥ ነገን ዛሬ ደመደምኩት፤
ምነው ተስፋ ቆረጥኩ፥ ዛሬን አሁን ቀበርኩት።
እንደ ሙሴ በእድሜ ማታ፥ ከከንዓን ሩቅ ብሆን፤
የልፋቴን ሳልቀበል፥ ዕጣ ፈንታ ሞትን ቢሆን፤
በታቦርም ትመጣለህ፥ ቃልኪዳንህ አይታጠፍም
ካንተ ይሰጠዋል እንጂ፥ ሰው በራሱ አያተርፍም
:
ከእሳት በፊት ትደርሳለህ፤
ወይስ ነዶ ትመጣለህ፤
ስወገር ትደርሳለህ፤
ወይስ ፍርዱን ትሽራለህ፤
ስትታመም ትመጣለህ፤
ወይስ ስሞት ታስነሳለህ።
አልወተውትህም እታገስሀለሁ፤
በሁሉም ሁኔታ እጠብቅሀለሁ።
++++
የተናቀን የተረሳን፥ አንተ ስታስታውሰው፤
የጠሉኝ ቢሰበሰቡ፥ ቢሉኝ እንዳንተ እናንግሰው።
ቋጠሮዬን ስትፈታ፥ ከቀበሮ ደስታ ጠብቀኝ፤
ጽድቅህን እኔ እሻለሁ፥ መንግስትን አትንፈገኝ።
+++
( መምህር ኢዮብ ይመኑ)
ግጥም ደራሲ©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   www.tgoop.com/Menfesawigetmoch 
‹‹በዓታ ለማርያም››
በተወለደች፣ በሶስት አመቷ፤
መቅደስ አመጧት፣ እናት አባቷ፡፡
ካህኑ ዘካርያስ፣ ቀኑን ያሳይሀል፤
ባርያውን በሰላም፣ ያሰናብትሁል፡፡

ማን ይመግባታል፣  ብለህ አትጨነቅ፤
ወላዲተ አምላክ፣ መሆኗን ሳታውቅ፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል፣ ክንፎቹን ዘርግቶ፤
ይመግባት ነበር፣ ከሰማያት መቶ፡፡

ሙሽራዬ ሆይ፤
ከሊባኖስ ነይ፡፡
ልጄ ስሚኝ ይላል፣ አባትሽ ዳዊት፤
የልዑል ማደርያው፣ ስትሆኚ ታይቶት፡፡

በዓታ ለማርያም፤
ስጪን ፍቅር ሰላም፤
<<ኢያቄም ወሀና፥ ወለዱ ሰማይ፤
ሰማያቸው ደግሞ፥ አወጣች ፀሀይ።>>


+++++++
©ታዜና
#መንፈሳዊ_ግጥሞች
www.tgoop.com/Menfesawigetmoch
በቅዱስ ስጋው በክቡር ደሙ
በመስቀሉ ሞት ድኗል አለሙ
ስጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ
ርስታችንን ሰጠን መልሶ
+++
©ታዜና 
       #መንፈሳዊ_ግጥሞች 
      www.tgoop.com/Menfesawigetmoch
የመረጋጋቴ፥ የማረፌ ምስጢር፤
የሹመቴ ግርማ፥ የወንበሬ ክብር
የህይወቴ አክሊል፥ ማርያም ትባለች።
ምግብ ይውሆነውን፥ ልጇን ሰታኛለች።
+++
©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   www.tgoop.com/Menfesawigetmoch
▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

እናንት የቤተክርስቲያን ዕንቁዎች የቤተክርስቲያን አምላክ ክብርን ፣ ጸጋንና ረጅም ዕድሜን ያድልልን። እናንተን ለሚመስሉ ሁሉ እንጂ ! ለንጽሕይትና ቅድስት ቤተክርስቲያን በፍጹም ነፍሳችሁ የታመናችሁ እውነተኛ ልጆቿ ሆናችኋልና !

የእኛ ዘመን ግን የከፋ ሆኗል። ዘይቱ ከማድጋው ተሟጦ ያለቀ ይመስላል። ምድሪቱ በመዝሙር ስም በሚዘፍኑ ዕልፎች ተሞልታለች። ባዶ ጩኸት ምድሪቱን ያውካል። ዝላዩና ጭፈራው ወሰኑን አጥቷል። ገንዘብንና ዝናን ሽመታው ከዓለሙ ይልቅ ከፍቷል። ኑፋቄው በአደባባይ በነጻነት ተገልጧል። ወይን ጠጁን ከነ አተላው የምንጠጣ ጎስቋሎች ሆነናል !

"እስከ መጨረሻው የሚጸና እርሱ ይድናል" [ ማቴ.፳፬፥፲፫ ]

እግዚአብሔር በምሕረቱ ያስበን !


▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬
++++#ታላቍ_መቃርዮስ_እንዲህ_አሉ#+++++

ጥላቻ የሚመጣው ቂምን ወይም ክፉን ከመሰወር ነው፣ ክፉን መሰወር ደግሞ ከኩራት፣ ኩራት ከግብዝነት፣ ግብዝነት ከእምነት ጉድለት፣ የእምነት ጉድለት ከልብ ድንዛዜ፣ የልብ ድንዛዜ ከቸልተኝነት፣ ቸልተኝኀት ከስንፍና፣ ስንፍና ከተስፋ መቁረጥ፣ ተስፋ መቁረጥ ከትዕግሥት ማጣት፣ ትዕግሥት ማጣት ከትዕቢት ይመጣል። ጸሎት በፍቅር ላይ ይመሠረታል፣ ፍቅር ደግሞ በደስታ፣ ደስታ ደግሞ በቅንነት፣ ቅንነት በትሕትና፣ ትሕትና በአገልግሎት፣ አገልግሎት በተስፋ፣ ተስፋ በእምነት፣ እምነት በመታዘዝ፣ መታዘዝ በግልጸኝነት ወይም ራስን ቀለል በማድረግ ላይ ይመሠረታል። Ven. Macarius the Great
ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ
እንኳ ለብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓል (ሐምሌ ፭) አደረሰን፤ አደረሳችሁ!!!
በመ/ር ጌታቸው በቀለ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሐምሌ ፭ ቀን “ጴጥሮስ ወጳውሎስ” በማለት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ እና ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልካሙን የክርስትና ገድል ተጋድለው ሰማዕትነት የተቀበሉበትን ቀን በታላቅና በተለየ ሁኔታ ታከብራለች። በዚሁ ዕለት የጾመ ሐዋርያት ፋሲካ የሚከበርበት ዕለትም ነው፡፡
የክርስትና ሃይማኖትን በማስፋፋት ከፍተኛውን ሚና የተጫወቱት እነዚህ ቅዱሳን ሐዋርያት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መልእክታትን ጽፈዋል። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ሁለት መልእክታትን ሲጽፍ፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ዐሥራ አራት መልእክታትን ጽፏል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ዓሣ ከማጥመድ ሥራ ለዚህ ታላቅ አገልግሎት ሲጠራ (ማቴ ፬፦፲፰)፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ቤተክርስቲያን እና የክርስቶስ ተከታዮችን ከማሳደድ ላይ ሳለ “ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? አንተ የምታሳድደኝ እኔ ኢየሱስ ነኝ፤ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል” (ሐዋ. ፱፡፬-፭) በሚል የተጠራ ነው። በዛሬው ዝግጅታችን የእነዚህን ቅዱሳን ታሪክ በአጭሩ እንደሚከተለው እንመለከታለን፡-
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ ጴጥሮስ በአባቱ የሮቤል፣ በእናቱ የስምዖን ነገድ ሲኾን፣ የተወለደውም በገሊላ አውራጃ በቤተ ሳይዳ ነው፡፡ ወላጆቹ ያወጡለት ስም “ስምዖን” ነበር፡፡ በቂሳርያ ከተማ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ማን ትሉኛላችሁ?» ብሎ በጠየቀ ጊዜ “አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረውን ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ጴጥሮስ” ብሎ ጠርቶታል፤ ትርጕሙም በግሪክ ቋንቋ ዐለት(መሠረት) ማለት ሲኾን፤ በአራማይክ ደግሞ “ኬፋ” ይባላል። የቅዱስ ጴጥሮስ ጥሪ ቅዱስ ጴጥሮስ የሚተዳደረው በዓሣ አጥማጅነት የነበረ ሲኾን፣ ሰዎችን በወንጌል መረብ እያጠመደ ወደ ክርስትና ሕይወት ይመልስ ዘንድ ጌታችን ለሐዋርያነት ጠርቶታል (ሉቃ. ፭፥፲፤ ማር.፩፥፲፮)፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በአራቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ በተቀመጡት የሐዋርያት ዝርዝር ቀዳሚውን ሥፍራ ይዞ ይገኛል። በበዓለ ሃምሳም ለደቀመዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስ በወረደላቸው ጊዜ ለተሰበሰቡት አይሁድ አፈ ጉባኤ ሆኖ ወንጌልን የሰበከ ሦስት ሺሕ ምእመናንን አሳምኖ የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን በኢየሩሳሌም የመሠረተ ነው (የሐዋ. ፩፥፲፮-፳፫፣ ፪፥፲፬-፴)፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ከሐዋርያት ሁሉ ቀደም ቀደም የማለት ባሕርይ ነበረው። ጌታ በጥብርያዶስ ባሕር ላይ ሌሊት በእግሩ ሲመጣ ቢመለከት “ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ” በማለት ካስፈቀደ በኋላ ወደ ጌታ ለመምጣት መንገድ ጀምሮ በመሐል ጥርጣሬ ገባውና መስጠም ስለ ጀመረ ጌታችን “ያመንክ እንጂ ያላመንክ አትሁን” ብሎ ገስፆ ከመስጠም አድኖታል (ማቴ ፲፬፥፳፪-፴፫)፡፡
በቅፍርናሆም ጌታችን ምሥጢረ ቁርባንን ሲያስተምር፣ አይሁድ ስላልገባቸው ወደ ኋላ አፈገፈጉ። ከደቀ መዛሙርቱም “ብዙዎቹ ወደ ኋላ ተመለሱ” በዚህን ጊዜ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁ?” ብሎ ሐዋርያትን ጠየቃቸው። በዚህ ሰዓት “ጌታ ሆይ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም የሕይወት ቃል አለህ። እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እንደሆንክ እናምናለን” በማለት ሐዋርያትን ወክሎ የመለሰ እርሱ ነው (ዮሐ ፮፥፷፮-፷፰)፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ይወድ ነበር። ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል (ማቴ ፲፮፥፳፫)፡፡ በኋላም “ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም” ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር። ጌታችን “ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ” እያለው እንኳን “ከአንተ ጋር መሞት እንኳን የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም” በማለት የተናገረ ሰው ነው (ማቴ ፳፮ ፥ ፴፬)፡፡ አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው ዐውቆአልና “ትወደኛለህን?” ተብሎ ሲጠየቅ “አንተ ታውቃለህ” ነበረ መልሱ። “ግልገሎቼን አሠማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጐቼን አሠማራ» በማለት አደራ የተቀበለ ነው (ዮሐ ፳፩፥፲፭-፲፯)፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ የሐዋርያት አለቃ ኾኖ ተሹሟል፡፡ ለአገልግሎት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮም በእስያ፣ በሮም፣ በሰማርያ፣ በልዳ፣ በኢዮጴ፣ በአንጾኪያ፣ በገላትያና በሌሎችም አገሮች እየተዘዋወረ ወንጌልን ሰብኳል፡፡ በስብከቱ ምክንያትም ልዩ ልዩ መከራን ተቀብሏል፡፡ በክርስቶስ ኀይል አጋዥነት ብዙ ድንቆችንና ተአምራትን አድርጓል፡፡ ከተሰጠው ጸጋ ብዛት የተነሣ በጥላው ሕሙማን ይፈወሱ ነበር (ሐዋ. ፭፥፲፭)፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ አንድ ዓመት ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ካስተማረ በኋላ የሮሜ ክርስቲያኖች እየበዙ ከመምጣታቸውም በላይ የክርስትናው ጉዞ እስከ ሮማ ባለሥልጣናት ደረሰ። በዚህን ጊዜ ኔሮን በቅንዓት ተነሣባቸው።
የቅዱስ ጴጥሮስ ሰማዕትነት
የቅዱስ ጴጥሮስ ምድራዊ የአገልግሎት ዘመኑ ሊፈጸም ሲቃረብም ኔሮን በ፷፬ ዓ.ም. እርሱ ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው ቤተ መንግሥቱ ተቀምጦ የሮማን ከተማ እሳት ለቀቀባት። የሮም ሕዝብ በደረሰው አደጋ እጅጉን ተቆጣ። ኔሮንም በክርስቲያኖች አመካኘ። የከተማው መጋየት ያበሳጨው የሮማ ሕዝብ፣ ክርስቲያን የሆነውን ሁሉ እያወጣ መግደሉን ተያያዘው። በቅዱስ ጴጥሮስና በሌሎችም ክርስቲያኖች ላይ የሞት ፍርድ ዐወጀ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም በሮም ሲያስተምር ቆይቶ የሮም መኳንንት እንዳይገድሉት ከሮም ሲወጣ ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ተገለጸለት፡፡ በዚህ ጊዜ “አቤቱ ጌታ ሆይ ወዴት ትሔዳለህ?” ሲል ቢጠይቀው ጌታችንም “ልሰቀል ወደሮም እሔዳለሁ” አለው፡፡ “ዳግመኛ ትሰቀላለህን?” ባለው ጊዜም “አንተ ስትፈራ ጊዜ ነው እንጂ” ሲል መለሰለት፡፡ ያንጊዜም “ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን ታጥቀህ ወደ ወደድኸው ትሔድነበር፡፡ ስትሸመግል ግን እጅህን ታነሣና ሌላ ሰው ያስታጥቅሃል፤ ወደ ማትወደውም ይወስድሃል” (ዮሐ. ፳፩፥፲፰) በማለት ጌታችን የነገረው ቃል አሟሟቱን የሚያመለክት መኾኑን አስታውሶ ወደ ሮም ተመልሶ ስብከቱን ቀጠለ፡፡

በሮማውያን ሕግ ቅጣት የተፈረደበት ወንጀለኛ የሮም አገር ተወላጅ ከኾነ የወንጀሉ ክብደትና ቅለት እየታየ ግርፋት ወይም ሞት ይፈረድበታል እንጂ በአንድ ወንጀል ሁለት ቅጣት አይቀጣም ነበር፡፡ ወንጀለኛው የውጪ አገር ዜጋ (ከሮም ውጪ) ከኾነ ግን ለምሳሌ ቅጣቱ ግርፋት ከኾነ ከተገረፈ በኋላ እስራት ይጨመርበታል፤ ቅጣቱ ሞት ከኾነም ከገረፉት በኋላ በመስቀል ወይም በሌላ መሣርያ ይገድሉት ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ዜግነቱ ሮማዊ አልነበረምና በግርፋትም፣ በእስራትም በሞትም እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡ ያን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ይዘው አሠሩት። ከጥቂት ቀናት በኋላም ሮማውያን የመስቀያውን እንጨት አቀረቡለት። እንደ ሥርዐታቸውም ቅዱስ ጴጥሮስን ከገረፉት በኋላ ሊሰቅሉት ሲሉ ወታደሮቹን “እንደ ክብር ንጉሥ እንደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስአቁማችሁ ሳይኾን፣ ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ” አላቸው፡፡ እነርሱም እንዳላቸው አድርገው ዘቅዝቀው ሰቅለውታል፡፡ ሐምሌ ፭ ቀን በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከዕብራዊያን፣ ከብንያም ነገድ ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው። ጠርሴስ በንግድዋ የታወቀች የኪልቂያ ዋና ከተማ ናት። ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነትን ይሰጡ ስለነበር፥ የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር። ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለአገልግሎት ከመጠራቱ በፊት “ሳውል” ይባል ነበር፡፡ ከኦሪቱ ምሁር ከገማልያል ሕገ ኦሪትንና መጻሕፍተ ነቢያትን ተምሯል፡፡ ለሕገ ኦሪት ቀናኢ ከመኾኑ የተነሣም የክርስቶስ ተከታዮችን ዅሉ ያሳድድ ነበር፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአይሁድ ሸንጎ አባልነት ለኹለት ዓመታት በሠራበት ወቅት ለኦሪታዊ እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመሆኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣሚ ይቃወም ነበር። እንዲያውም ሊቀ ዲያቆናት እስጢፋኖስን በማስተማሩ ምክንያት ተከሶ ለአይሁድ ሸንጎ ቀርቦ በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም ቅዱስ ጳውሎስ የገዳዮቹ ልብስ ጠባቂ ነበር (ሐዋ. ፯፥፶፰፤ ፳፪፥፳)፡፡ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ወደ ደማስቆ ሲሔድ ከመንገድ ላይ ለሐዋርያነት ተጠርቷል (ሐዋ. ፱፥፩-፴፩፤ ፳፪፥፩-፳፩)፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና “ውል ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ?” የሚለውን ድምፅ የሰማው። ሐዋርያው ጳውሎስም “ጌታ ሆይ ማን ነህ?” ብሎ ጠየቀ። “አንተ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ። የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል” ሲል መድኃኒታችን ተናገረው። ያን ጊዜም በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ “ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ?” ሲል ጠየቀ። ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው (የሐዋ. ፱፥፩)።
የሐዋርያው ዐይኖች ለማየት ሽላልቻሉ እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ። ለሦስት ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ። በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘው ሐናንያ ለተባለው አባት በራእይ ተገለጠለት። ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና ሄዶ እንዲያጠምቀው አዘዘው። ሐናንያ አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል። አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት የመጡ ናቸው። ያን ስደት ያስነሣው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው። በዚህ የቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ጳውሎስ ነበር። ይህን የሚያውቀው ሐናንያ በቅድሚያ ከእግዚአብሔር ጋር መከራከር ጀምሮ ነበር። በመጨረሻ ግን “ይህ በአሕዛብም በነገሥታትም በእሥራኤልም ልጆች ፊት ስሜን ይሸከም ዘንድ ለእኔ የተመረጠ ዕቃ ነውና ሂድ፤ ስለ ስሜ ስንት መከራ ሊቀበል እንዲያስፈልገው እኔ አመለክተዋለሁና” በማለት እግዚአብሔር ሐናንያን ላከው። ሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስን ካጠመቀውና ካስተማረው በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዐረብ ሀገር መሄዱን ራሱ ተናግሮአል(ገላ ፩፥፲፯)፡፡ ለሦስት ዓመታት በዐረብ በረሓ ከቆየ በኋላ ወደ ደማስቆ ከተማ ተመለሰ። በዚያም በነበሩ አይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ። ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰበክ በማየታቸው አይሁድ ተነሡበት።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ ከተማ ለዘጠኝ ዓመታት ቆይቷል። ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ። ከኢየሩሳሌም የተሰደዱት ክርስቲያኖች የአንጾኪያን ሕዝብ ተግተው በማስተማራቸው ዝናው እስከ ኢየሩሳሌም ደረሰ። በዚህም ምክንያት በኢየሩሳሌም የነበሩት አበው በርናባስን ወደ አንጾኪያ ላኩት። በርናባስ የግሪክ ቋንቋ ችሎታ ያለውን፣ ከማንኛውም ሰው ጋር መግባብ የሚችለውን፣ ደግሞም እግዚአብሔር ለአሕዛብ ሐዋርያ እንዲሆን የመረጠውን ቅዱስ ጳውሎስን ከጠርሴስ በማምጣት በአንጾኪያ ሥራቸውን ጀመሩ።
የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያዊ ጉዞ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመጀመሪያው ጉዞ ያደረገው ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ከተመለሰ በኋላ በልዑል እግዚአብሔር ጥሪ በአሕዛብ ሀገር ወንጌልን ለመስበክ ከበርናባስ ጋር ወጡ። ይህም ጉዞ የተከናወነው በ፵፮ ዓ.ም.አካባቢ ነው። የተሸፈኑትም ሀገሮች ሲሊንውቂያ፣ ቆጵሮስ፣ ስልማን፣ ጳፋ፣ ጰርጌን፣ ገላትያ፣ ጵስድያ፣ ኢቆንዮን፣ ሊቃኦንያ፣ ልስጥራ፣ ደርቤን፣ ጵንፍልያ፣ አታልያና አንጾኪያ ናቸው።
ሁለተኛው ጉዞ በ፶ ዓ.ም. ገደማ የተከናወነው ነው። በመጀመሪያው ጉዞ ማርቆስ አብሮ ተጉዞ ነበር። ነገር ግን ጵንፍልያ ከተማ ሲደርስ እናቱ ስለናፈቀችው መመለስ በመፈለጉ በርናባስ ወደ ኢየሩሳሌም ይዞት መጣ። ስለዚህም በሁለተኛው ጉዞ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሲላስን ይዞ ወደ ኪልቂያ ሶርያ ሲጓዝ በርናባስ ደግሞ ማርቆስን አስከትሎ ወደ ቆጵሮስ ሄደ። በዚህ ጉዞው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ግሪክ ደርሶአል። የተጓዘባቸውና ያስተማረባቸው ከተሞችም፦ ደርብያ፣ ልስጥራ፣ፍርግያ፣ ገላትያ፣ ሚስያ፣ጢሮአዳ፣ ሳሞትራቄ፣ ናፑሊ፣ ፊልጵስዩስ፣ ተሰሎንቄ፣ በርያ፣አቴና፣ ቆሮንቶስ፣ አንክራኦስ፣ አፌሶን፣ ቂሳርያ፣ ኢየሩሳሌምና አንጾኪያ ናቸው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የመንፈስ ልጁ ጢሞቴዎስን ያገኘው በዚሁ ጉዞው በልስጥራ ከተማ ነው።

ሦስተኛው ጉዞ የተከናወነው በ፶፬ ዓ.ም. ሲሆን የተሸፈኑትም ሀገሮች ገላትያ፣ ፍርግያ፣ ኤፌሶን፣ መቄዶንያ፣ ፊልጵስዩስ፣ ቆሮንቶስ፣ ጢሮአዳ፣ አሶን፣ ሚልጢኒን፣ አንጠቀከስዩ፣ ትሮጊሊዩም፣ መስጡ፣ ቆስ፣ ሩድ፣ ጳጥራ፣ ጢሮስ፣ ጵቶልማይስ፣ ቂሳርያ፣ ኢየሩሳሌም ናቸው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከልዩ ልዩ ሀገሮች ክርስቲያኖች የሰበሰበውን ዕርዳታ ለኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን በመያዝ ሦስተኛውን ጉዞ አጠናቅቆ ኢየሩሳሌም ገባ። ነገር ግን ኢየሩሳሌም የገባበት ጊዜ የፋሲካ በዓል ስለነበር ከልዩ ልዩ ሀገሮች የተሰበሰቡ አይሁድ በከተማዋ ነበሩ። እነዚህ በዝርወት የሚኖሩ አይሁድ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን በየሀገራቸው በትምህርቱ የተነሣ ሲቃወሙት የነበሩ ናቸው።
የቅዱስ ጳውሎስ ሰማዕትነት

ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮም በመላው ዓለም እየተዘዋወረ ወንጌልን በመስበክ ብዙዎችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሳምኗል፡፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት አዘጋጅቷል (፩ኛ ቆሮ. ፱፥፲፱-፳፫)፡፡ ወንጌልን በመስበኩ ምክንያትም ከአይሁድና ከአረማውያን ዘንድ ብዙ መከራና ስቃይ ደርሶበታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ከእግዚአብሔር በተሰጠው ጸጋ ብዙ ድንቆችንና ተአምራትን አድርጓል፡፡ በልብሱ ቅዳጅም ሕሙማን ይፈወሱ ነበር (ሐዋ. ፲፱፥፲፩)፡፡

አገልግሎቱን ሊፈጽም ሲልም የሮም ንጉሥ ኔሮን ቄሣር የክርስቲያኖች ቍጥር እየጨመረ የመጣው በቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት በመማረካቸው ምክንያት መኾኑን ተረድቶ፤ ይልቁንም የቤተ መንግሥቱ ሰዎች ሳይቀር በቅዱስ ጳውሎስ በመማረካቸው ተቈጥቶ ቅዱስ ጳውሎስን ወደ ፍርድ ሸንጎው አስቀረበው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ንጉሡንና ወታደሮችን ሳይፈራ የኢየሱስ ክርስቶስን የእግዚአብሔር ልጅነትና አምላካዊ ሥልጣን ይመሰክር ነበር፡፡
ንጉሡም በቍጣ ይሙት በቃ ፈረደበት፡፡ ወደሚገደልበት ስፍራ ሲወስዱትም በንግግሩና በአስተያየቱ ዅሉ ምንም ፍርኀት አይታይበትም ነበር፡፡ እንዳውም በጦርነት ድል አድርጎና ማርኮ እንደ ተመለሰ ወታደር ይደሰት ነበር እንጂ፡፡ ለሚገድሉትም ይቅርታን ይለምን ነበር፡፡

በመጨረሻ በ፷፬ ዓ.ም. ኔሮን በጥጋቡ የሮማ ከተማ ስትቃጠል ምን እንደምትመስል ማየት እፈልጋለሁ ብሎ አቃጠላት። የሮም ሕዝብ በከተማው መቃጠል በማዘኑና በማመፁ ነገሩን ሁሉ በክርስቲያኖች ላይ አሳበበ። በዚህም የተነሣ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ መሰደድ፣ መሠየፍ፣ መታረድ እጣ ፈንታው ሆነ። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በኒቆጵልዮን ከተማ ሲያስተምር በ፷፭ ዓ.ም. ተይዞ ወደ ወኅኒ ገባ። ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ፸፬ ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ አንገቱን ተሰይፎ በ፷፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፭ ቀን በሰማዕትነት ዐረፈ።

እንደ ማጠቃለያ
ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ ኹለቱ ሐዋርያት ከአጠራራቸው ጀምሮ የተለያየ ሁኔታ ቢታይባቸውም፤ ለእግዚአብሔር አገልግሎት ግን በተሰጣቸው የሥራ ድርሻ በታማኝነት ያገለገሉ ናቸው፡፡ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸው ጨለማውን ዓለም በማድመቃቸው ‹ብርሃናተ ዓለም› ተብለው ይጠራሉ፡፡ የቅዱሳኑ አገልግሎት፣ ገድላቸው እና ተአምራቸው በመጽሐፈ ስንክሳር፣ በዜና ሐዋርያት እና በገድለ ሐዋርያት በሰፊው ተጽፎ ይገኛል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ኹለት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ዐሥራ አራት መልእክታትን ጽፈዋል። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በ፷፯ ዓ.ም በኔሮን ቄሣር እጅ ቁልቁል ተሰቅሎ ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በ፷፯ ዓ.ም. በኔሮን ቄሣር እጅ አንገቱን ተቆርጦ ሰማዕትነትን ተቀብሏል፡፡

የቅዱሳኑ ሐዋርያት ረድኤትና በረከታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ምንጭ፡-

✍️ መጽሐፍ ቅዱስ
✍️ ገድለ ሐዋርያት
✍️ መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ሐምሌ ፭
✍️ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ (1995)፡፡ ዜና ሐዋርያት
✍️ ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ
✍️ Pope Shenouda. Saint Peter and Paul
#ልንናደድ_የሚገባን_ማን_ላይ_ነው?


ብዙ ኃጢአቶችንና ወንጀሎችን የሠራ አንድ ሰው ለሠራው ኃጢአትና ወንጀል ሳይቀጣ ሲቀር አይተን ብዙዎቻችን እንበሳጫለን፡፡ ያ ሰው እንዲጠየቅና እንዲቀጣ እንፈልጋለን፡፡ ይህ ሳይኾን ከቀረ ግን ቅር እንሰኛለን፤ እንናደዳለን፡፡

እንዲህ የምንኾነው ግን የገዛ ራሳችንን ግብር ስለማንመለከት ነው፡፡ መበሳጨትና መናደድ ቅርም መሰኘት የሚገባን በገዛ ራሳችን ላይ ነውና፡፡ እያንዳንዳችን ለራሳችን እንዲህ ብለን ልንጠይቅ ይገባናል፦ "በሌሎች ሰዎች ላይ ስንት በደል ፈጸምሁ? ለዚህ በደሌስ ስንቴ ሳልቀጣ ቀረሁ?"

በራሳችን ላይ ብዙ ምሳሌዎችን እንደምናገኝ ጥርጥር የለውም፡፡ ይህን ማወቃችን ደግሞ በሌሎች ሰዎች ላይ የተቆጣነው ቁጣና የተበሳጨነው ብስጭት እንደ ጢስ ተኖ እንደ ትቢያ በንኖ እንዲጠፋ ያደርጓል፡፡ ከዚህም በላይ ፊታችንን ወደ እግዚአብሔር እንድናዞር ስለ በደልነውም በደል ይቅርታንና ቸርነትን እንድንለምን ያደርገናል፡፡

እንዲያውም እኛ በበደልነው በደልና ሌሎች ሰዎች በሠሩት ኃጢአት ልዩነቱን እናስተውለው ይኾናል፡፡ ምናልባት የእኛ በደል የተሰወረና ለሌሎች ሰዎች የማይታይ ሕቡዕ ይኾናል፤ በአንጻሩ ደግሞ የሌሎች ሰዎች ኃጢአት በግልጽ የሚታይ ይኾናል፡፡

ታዲያ በዚህ ኹኔታ የእኛ በደል ንኡስ፥ የሌሎች ሰዎች ኃጢአት ግን ዐቢይ እንደ ኾነ ልናስብ ይገባናልን? በጭራሽ! ምክንያቱም በስውር የሚሠ'ራና ሌላ ሰው የማያየው በደል ብዙውን ጊዜ እጅግ አደገኛ ነው፡፡

ስርቆትንና ቀማኛነትን የመሳሰሉ በግልጽ የሚታዩ ኃጢአቶች ኃጢአት መኾናቸው በቀላሉ ይታወቃሉ፡፡ መታወቃቸው ብቻም ሳይኾን በቀላሉ ንስሐ ሊገባባቸውና ሊወገዱ የሚችሉ ናቸው፡፡ ውሸትን፣ ሐሜትንና በስውር ማታለልን የመሳሰሉ በስዉር የሚሠሩ በደሎች ግን በደል መኾናቸውን ለማወቅም ስለ እነዚህ ንስሐ ገብቶ ለማስወገድም እጅግ ክቡዳን ናቸው፡፡

(
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ - አምስቱ የንስሐ መንገዶች ገጽ 98-99)
                          †                          

   [   🕊  ማር መርቆሬዎስ   🕊   ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

🕊 † " ፒሉፓዴር " የአብ ወዳጅ † 🕊

እንኳን አደረሰን !

በዓለ ልደቱ ወቅዳሴ ቤቱ ለማር መርቆሬዎስ ፤ መፍቀሬ አብ።

ሰላም ለኅሊናከ ዘኢየአምር ቅያሜ ፤
....

ኦ ! በኅሊናህ ቂም በቀል የሌለብህ ! መዓዛህ እንደ ጣፋጭ ሽቱ የሆነ ! ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ [ ከሃዲዎች ] እንደ ደመና የበተኑህ ! የተጋድሎ ምስክርነትን የፈጸምህ ! ኦ! መርቆሬዎስ ዘሮሜ ! [ አርኬ ]

🕊

[ በከመ ልማድከ ፍጡነ ተራድአነ ] እንደልማድህ ፈጥነህ እርዳን !

🍒

†                       †                       †
💖                    🕊                    💖
እለታዊ መልዕክት📜
=>+"+ እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ: እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ: ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን:: +"+ (ዕብ. 6:10-13
#በስድብ_ፈንታ_አመስግኑ

ብዙ ጊዜ ስንሳደብ እና መጥፎ ቋንቋ ስንጠቀም “እኔ ይህን አለማድረግ አልችልም ልማዴ ነው" እንላለን፡፡ እናም ሲጎዱን አንድ ነገር መናገር ካለብንም፣ በስድብ ፈንታ ምስጋና መናገርን እራሳችንን እናስተምር።

ነገር ግን፣ ሰው እያሰቃየኝ ዝም ማለት አልችልም ትላለህ፡፡ ከመናገርምጨ ጨጠ  ዠዠ አልከለክልህም፡፡ ሆኖም ከመሳደብ ይልቅ ምስጋናን ተናገር፡፡ ከመበሳጨት ይልቅ ምስጋናህን ግለጽ፡፡

ለጌታህ መናዘዝ ትችላለህ፡፡ በጸሎትህ ውስጥ ጩኽ፤ እንዲሁ መከራህን ያቀልልሃል፣ ፈታኙም ሰይጣን በምስጋናህ ውስጥ ይሸሻል፣ የእግዚአብሔርም እርዳታ ወዳንተ ይቀርባል።

ከተሳደብክ፣ የእግዚአብሔርን ስጦታ ትከለክላለህ፤ እናም ፈታኙ በአንተ ላይ እንዲበረታ ታደርጋለህ፤ በዚያም እራስህን የበለጠ በህመም ውስጥ ታስገባለህ፡፡ ብታመስግን ግን የክፉ መንፈስን ጥቃት ትቃወማለህ፡፡

ነገር ግን ምላስ ብዙውን ጊዜ በልማድ ኃይል አንዳንድ መጥፎ ቃላትን ከመናገር ወደኋላ ማለት አይችልም:: ከዚያም በምትወድቅበት ጊዜ ኹሉ ቃሉ ከመናገርህ በፊት ጥርሶችህን ጠብቀው ይዘጉ፡፡ ምላስህ የደም ጠብታ ብታፈስስ ይሻላታል ፤ ከስድብም በኋላ የማያቋርጥ ቅጣት ከምትቀበል በጊዜው ሥቃይን ብትታገሥ ይሻልሃልና፡፡

(
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ - #የነፍስ_ምግብ #በፍሉይ_ዓለም_የተተረጎመ)
       ቃለ ሕይወትን ያሰማን

   🌹   የእግዚአብሔር ቸርነት 🌹
   🌹 የእመቤታችን ጸሎት      🌹
            ከሁላችን ጋራ ይሁን
የሰላም ሌሊት ያድርግልን እግዚአብሔር
የትንቢቱ መፈጸሚያ ከመሆን ይሰዉረን
ደህና እደሩ ተወዳጆች
    
                          †                          

   [   🕊  ቅ ዱ ስ    ዮ ሴ ፍ   🕊   ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

🕊  †  ፃድቁ_አረጋዊ_ዮሴፍ  †   🕊

እንኳን አደረሰን !

በዓለ ዕረፍቱ ለፃድቁ አረጋዊ ዮሴፍ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በፃድቁ ስም ለምናመሰግንበት በዚህች ዕለት መልካም ሽምግልና የነበረው የእመቤታችን የድንግል ማርያም ጠባቂ ድካሟን ለመሳተፍ ፣ ክብር ይግባውና ለጌታችንም አሳዳጊው ለመሆኑ የተገባው ፃድቁ አባታችን ቅዱስ ዮሴፍ አረፈ።

በአረፈበትም ጊዜ ጌታችን ወደ እርሱ መጥቶ እጆቹን በላዩ ላይ ጫነ ለሥጋውም መፍረስና መበስበስ እንዳያገኘው ኃይልን ሰጠው በአባቱ በያዕቆብም መቃብር አኖሩትየዘረ አዳምን አደራ ለመቀበል የተመረጠ ልዩ አባት ቅዱስ ዮሴፍ በረከቱ ይድረሰን።

መልአከ እግዚአብሔር እያነጋገረው እርሱ ግን በዝምታ የኖረ ታላቅ ቅዱስ ነው እመቤታችንን ለመጠበቅ ሦስት ተአምራት የተመለከተለት ብቸኛ አባት የድኅነታችን የምስጢር ሙዳይ ድንግል ማርያምን ለመቀበል የተመረጠ ክቡር ቅዱስ የሆነ በእርግና ዘመኑ ስለ ክርስቶስ መከራን የተቀበለ የሃይማኖት አርበኛ

ከእመቤታችን ቀጥሎ ጌታችንን ተንከባክቦ በማሳደጉ አባቱ ተብሎ እስከመጠራት የደረሰ ልዩ ነው። የእርሱን ያኽል ጌታውን በእጁ የዳሰሰ በትከሻው የተሸከመ አይገኝም።

🕊

የአረጋዊው የቅዱስ ዮሴፍ ምልጃና ጸሎቱ ከዘለዓለም እሳት ያድነን:: ጸጋ በረከቱ ይክፈለን::

🍒

†                       †                       †
💖                    🕊                    💖
2025/06/30 11:42:17
Back to Top
HTML Embed Code: