tgoop.com/learn_with_John/873
Create:
Last Update:
Last Update:
ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ ኹለቱ ሐዋርያት ከአጠራራቸው ጀምሮ የተለያየ ሁኔታ ቢታይባቸውም፤ ለእግዚአብሔር አገልግሎት ግን በተሰጣቸው የሥራ ድርሻ በታማኝነት ያገለገሉ ናቸው፡፡ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸው ጨለማውን ዓለም በማድመቃቸው ‹ብርሃናተ ዓለም› ተብለው ይጠራሉ፡፡ የቅዱሳኑ አገልግሎት፣ ገድላቸው እና ተአምራቸው በመጽሐፈ ስንክሳር፣ በዜና ሐዋርያት እና በገድለ ሐዋርያት በሰፊው ተጽፎ ይገኛል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ኹለት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ዐሥራ አራት መልእክታትን ጽፈዋል። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በ፷፯ ዓ.ም በኔሮን ቄሣር እጅ ቁልቁል ተሰቅሎ ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በ፷፯ ዓ.ም. በኔሮን ቄሣር እጅ አንገቱን ተቆርጦ ሰማዕትነትን ተቀብሏል፡፡
የቅዱሳኑ ሐዋርያት ረድኤትና በረከታቸው ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ምንጭ፡-
✍️ መጽሐፍ ቅዱስ
✍️ ገድለ ሐዋርያት
✍️ መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ሐምሌ ፭
✍️ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ (1995)፡፡ ዜና ሐዋርያት
✍️ ቤተ ክርስቲያንህን ዕወቅ
✍️ Pope Shenouda. Saint Peter and Paul
BY እልመስጦአግያ+++
Share with your friend now:
tgoop.com/learn_with_John/873