LEARN_WITH_JOHN Telegram 863
https://youtu.be/4s9LW4mhUqQ?si=EzwAsMh6cRJFCZHK
(መምህር ኢዮብ ይመኑ)
-እጠብቅሀለሁ-
እጠብቅሀለሁ በመጠቂያዬ፤
ትመጣለህና ሳትረሳ ጌታዬ።
ቀናት ቢያሰለቹ፥ ቢቆጠር ዘመናት፤
አምንሀለሁ ነፍሴን፥ እንደማትተዋት።
በምንም በየትም። በሁሉም ሁኔታ፤ 
እጠብቅሀለሁ፥ በእድሜ ጀምበር ማታ።

አማርሬህ፥ አኩርፌህም፥ አምቼህም፥ እኔ አውቃለሁ፤
ትግስትህን ሳልታገስ፥ ብዙ ነገር ብዬሀለሁ፤
ለዘመኔ እሾህ ሆኜ፥ ከቤትህም ጠፍቻለሁ፤
አትድረስብኝ አልደርስም፥ ብዬ በስምህ ምዬ አውቃለሁ።
ማታ እግሮቼን አጥበህ፥ በትህትና ለመከርከኝ፤
አላውቀውም፥ ማነው እሱ፥ ብዬ ባፌ መሰከርኩኝ።
ስታበራ ብቻ ሳይሆን፥ ጌቴሴማኒ ፀዳል ስትሆን፤
ቀያፋም ቤት መጥቻለሁ፥ ስትገረፍ ጅራፍ ልሆን።

ለካ እኔ ፈጠንኩ እንጂ፥ አንተ እኮ አልዘገየህም፤
በሰዓትህ ትመጣለህ፥ ቆየህ ምነው? አልልህም። 
እንደ ዕንባቆም እጮሀለሁ፥ አምላኬ ሆይ እልሀለሁ፤
ስትሰጠኝ ብቻ ሳይሆን፥ ብትከለክለኝም እጠብቅሀለሁ።
ፀጋህን ከኔ ውሰድልኝ፥ እኔ አንተን ከማጣህ፤
እንደዘኪዎስ ከዛፍ ልውጣ፥ ቤቴ ግባ አይቼህ።
በዝምታ ልቤን ክፈት፥ ግባ ማነው? ሳልልህ፤
አንተ ብቻ ናልኝ እንጂ፥ ከቤቴ ጋር ላምልክህ።


ደሞ እንዲህም ብዬሀለሁ፥ መቼ ጠይቄው መች መለሰ፤
ምነው ልቦናን ነሳኝ፥ እኔን ከሰው አሳነሰ።
ለምንድነው ያዋረደኝ፥ ዝም የሚለው እንዲህ ስሆን፤
ለካ አንተ የምትመጣው፥ እንደ አልዓዛር አፈር ስሆን፤
ለካ ህመም አይደለም፥ ሞትም አይደል የሚያቆምህ፤
በአራት ቀኔ ሳትፀየፍ፥ መቃብሬን ትከፍታለህ።
ለካ መሽቶም ትመጣለህ፥ እድሜ ዘመን አይገታህም፤
የጠበቀህ እርፍ ይላል፥ ላንተ ምንም አይሳንህም።
:
እንደ ዮሴፍ ብጠላ፥ በወንድሞቼ ብከዳ፤
በሰላሳ ዲናር ብሸጥ፥ ብንከራተት ምድረበዳ።
የአባቴ አይንም ቢፈስ፥ ቢናፍቀው የልጅ መልኬን፤ 
የሀሰት ፍርድ ቢፈርዱብኝ፥ ብወረወር እድሜ ልኬን።
ፍርድ አጣመው ቢያንገላቱ፥ ፍርዱም ቢሆን እድሜ ይፍታ፤
ማንም ዳግም አያስረኝም፥ አንተ መተህ ስትፈታ።
አንተ ምን ይሳንሀል፥ በወህኒው በኩል በር አለህ።
በጲጢፋራ መንበር፥ ልታነግሰኝ ትመጣለህ

ታማኝ ነህ  ለጠበቀህ፥ ማህጸንን ትፈታለህ፤
ሲስቁብኝ ልትባርከኝ፥ በመቅደስህ ትመጣለህ።
መካን ብባል የተጣለች፥ ስሜም እንኳ በቅሎ ቢሆን፤
መቶ ፍሬ ይገኝብኝ፥ አብዛኝና ለዘር ልሁን።
የሀናን ለቅሶ የሰማህ፥ የኤልሳቤትን እንባ ያበስክ፤
ልጅ የጠየቀችህን፥ በልጆች የምትባርክ፤
ዛሬ አለሁ ያንተ ሀና፥ ዛሬም አለሁ ያንተ ኤልሳቤት፤
እንደ ዮሀንስ ባርከህ ስጠኝ፥ ባንተ ጊዜ በለኝ አቤት።
:
መሮኛል ስልህ ወደላይ፥ የበታቼን ሳላየው፤ 
አንተ ባልቆረትከው ቀን፥ የራሴን ሞት የተመኘው።
ምነው መታገስ ከበደኝ፥ ነገን ዛሬ ደመደምኩት፤
ምነው ተስፋ ቆረጥኩ፥ ዛሬን አሁን ቀበርኩት።
እንደ ሙሴ በእድሜ ማታ፥ ከከንዓን ሩቅ ብሆን፤
የልፋቴን ሳልቀበል፥ ዕጣ ፈንታ ሞትን ቢሆን፤
በታቦርም ትመጣለህ፥ ቃልኪዳንህ አይታጠፍም
ካንተ ይሰጠዋል እንጂ፥ ሰው በራሱ አያተርፍም
:
ከእሳት በፊት ትደርሳለህ፤
ወይስ ነዶ ትመጣለህ፤
ስወገር ትደርሳለህ፤
ወይስ ፍርዱን ትሽራለህ፤
ስትታመም ትመጣለህ፤
ወይስ ስሞት ታስነሳለህ።
አልወተውትህም እታገስሀለሁ፤
በሁሉም ሁኔታ እጠብቅሀለሁ።
++++
የተናቀን የተረሳን፥ አንተ ስታስታውሰው፤
የጠሉኝ ቢሰበሰቡ፥ ቢሉኝ እንዳንተ እናንግሰው።
ቋጠሮዬን ስትፈታ፥ ከቀበሮ ደስታ ጠብቀኝ፤
ጽድቅህን እኔ እሻለሁ፥ መንግስትን አትንፈገኝ።
+++
( መምህር ኢዮብ ይመኑ)
ግጥም ደራሲ©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   www.tgoop.com/Menfesawigetmoch 



tgoop.com/learn_with_John/863
Create:
Last Update:

https://youtu.be/4s9LW4mhUqQ?si=EzwAsMh6cRJFCZHK
(መምህር ኢዮብ ይመኑ)
-እጠብቅሀለሁ-
እጠብቅሀለሁ በመጠቂያዬ፤
ትመጣለህና ሳትረሳ ጌታዬ።
ቀናት ቢያሰለቹ፥ ቢቆጠር ዘመናት፤
አምንሀለሁ ነፍሴን፥ እንደማትተዋት።
በምንም በየትም። በሁሉም ሁኔታ፤ 
እጠብቅሀለሁ፥ በእድሜ ጀምበር ማታ።

አማርሬህ፥ አኩርፌህም፥ አምቼህም፥ እኔ አውቃለሁ፤
ትግስትህን ሳልታገስ፥ ብዙ ነገር ብዬሀለሁ፤
ለዘመኔ እሾህ ሆኜ፥ ከቤትህም ጠፍቻለሁ፤
አትድረስብኝ አልደርስም፥ ብዬ በስምህ ምዬ አውቃለሁ።
ማታ እግሮቼን አጥበህ፥ በትህትና ለመከርከኝ፤
አላውቀውም፥ ማነው እሱ፥ ብዬ ባፌ መሰከርኩኝ።
ስታበራ ብቻ ሳይሆን፥ ጌቴሴማኒ ፀዳል ስትሆን፤
ቀያፋም ቤት መጥቻለሁ፥ ስትገረፍ ጅራፍ ልሆን።

ለካ እኔ ፈጠንኩ እንጂ፥ አንተ እኮ አልዘገየህም፤
በሰዓትህ ትመጣለህ፥ ቆየህ ምነው? አልልህም። 
እንደ ዕንባቆም እጮሀለሁ፥ አምላኬ ሆይ እልሀለሁ፤
ስትሰጠኝ ብቻ ሳይሆን፥ ብትከለክለኝም እጠብቅሀለሁ።
ፀጋህን ከኔ ውሰድልኝ፥ እኔ አንተን ከማጣህ፤
እንደዘኪዎስ ከዛፍ ልውጣ፥ ቤቴ ግባ አይቼህ።
በዝምታ ልቤን ክፈት፥ ግባ ማነው? ሳልልህ፤
አንተ ብቻ ናልኝ እንጂ፥ ከቤቴ ጋር ላምልክህ።


ደሞ እንዲህም ብዬሀለሁ፥ መቼ ጠይቄው መች መለሰ፤
ምነው ልቦናን ነሳኝ፥ እኔን ከሰው አሳነሰ።
ለምንድነው ያዋረደኝ፥ ዝም የሚለው እንዲህ ስሆን፤
ለካ አንተ የምትመጣው፥ እንደ አልዓዛር አፈር ስሆን፤
ለካ ህመም አይደለም፥ ሞትም አይደል የሚያቆምህ፤
በአራት ቀኔ ሳትፀየፍ፥ መቃብሬን ትከፍታለህ።
ለካ መሽቶም ትመጣለህ፥ እድሜ ዘመን አይገታህም፤
የጠበቀህ እርፍ ይላል፥ ላንተ ምንም አይሳንህም።
:
እንደ ዮሴፍ ብጠላ፥ በወንድሞቼ ብከዳ፤
በሰላሳ ዲናር ብሸጥ፥ ብንከራተት ምድረበዳ።
የአባቴ አይንም ቢፈስ፥ ቢናፍቀው የልጅ መልኬን፤ 
የሀሰት ፍርድ ቢፈርዱብኝ፥ ብወረወር እድሜ ልኬን።
ፍርድ አጣመው ቢያንገላቱ፥ ፍርዱም ቢሆን እድሜ ይፍታ፤
ማንም ዳግም አያስረኝም፥ አንተ መተህ ስትፈታ።
አንተ ምን ይሳንሀል፥ በወህኒው በኩል በር አለህ።
በጲጢፋራ መንበር፥ ልታነግሰኝ ትመጣለህ

ታማኝ ነህ  ለጠበቀህ፥ ማህጸንን ትፈታለህ፤
ሲስቁብኝ ልትባርከኝ፥ በመቅደስህ ትመጣለህ።
መካን ብባል የተጣለች፥ ስሜም እንኳ በቅሎ ቢሆን፤
መቶ ፍሬ ይገኝብኝ፥ አብዛኝና ለዘር ልሁን።
የሀናን ለቅሶ የሰማህ፥ የኤልሳቤትን እንባ ያበስክ፤
ልጅ የጠየቀችህን፥ በልጆች የምትባርክ፤
ዛሬ አለሁ ያንተ ሀና፥ ዛሬም አለሁ ያንተ ኤልሳቤት፤
እንደ ዮሀንስ ባርከህ ስጠኝ፥ ባንተ ጊዜ በለኝ አቤት።
:
መሮኛል ስልህ ወደላይ፥ የበታቼን ሳላየው፤ 
አንተ ባልቆረትከው ቀን፥ የራሴን ሞት የተመኘው።
ምነው መታገስ ከበደኝ፥ ነገን ዛሬ ደመደምኩት፤
ምነው ተስፋ ቆረጥኩ፥ ዛሬን አሁን ቀበርኩት።
እንደ ሙሴ በእድሜ ማታ፥ ከከንዓን ሩቅ ብሆን፤
የልፋቴን ሳልቀበል፥ ዕጣ ፈንታ ሞትን ቢሆን፤
በታቦርም ትመጣለህ፥ ቃልኪዳንህ አይታጠፍም
ካንተ ይሰጠዋል እንጂ፥ ሰው በራሱ አያተርፍም
:
ከእሳት በፊት ትደርሳለህ፤
ወይስ ነዶ ትመጣለህ፤
ስወገር ትደርሳለህ፤
ወይስ ፍርዱን ትሽራለህ፤
ስትታመም ትመጣለህ፤
ወይስ ስሞት ታስነሳለህ።
አልወተውትህም እታገስሀለሁ፤
በሁሉም ሁኔታ እጠብቅሀለሁ።
++++
የተናቀን የተረሳን፥ አንተ ስታስታውሰው፤
የጠሉኝ ቢሰበሰቡ፥ ቢሉኝ እንዳንተ እናንግሰው።
ቋጠሮዬን ስትፈታ፥ ከቀበሮ ደስታ ጠብቀኝ፤
ጽድቅህን እኔ እሻለሁ፥ መንግስትን አትንፈገኝ።
+++
( መምህር ኢዮብ ይመኑ)
ግጥም ደራሲ©ታዜና
   #መንፈሳዊ_ግጥሞች
   www.tgoop.com/Menfesawigetmoch 

BY እልመስጦአግያ+++




Share with your friend now:
tgoop.com/learn_with_John/863

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Healing through screaming therapy A Hong Kong protester with a petrol bomb. File photo: Dylan Hollingsworth/HKFP. Write your hashtags in the language of your target audience. It’s yet another bloodbath on Satoshi Street. As of press time, Bitcoin (BTC) and the broader cryptocurrency market have corrected another 10 percent amid a massive sell-off. Ethereum (EHT) is down a staggering 15 percent moving close to $1,000, down more than 42 percent on the weekly chart. Deputy District Judge Peter Hui sentenced computer technician Ng Man-ho on Thursday, a month after the 27-year-old, who ran a Telegram group called SUCK Channel, was found guilty of seven charges of conspiring to incite others to commit illegal acts during the 2019 extradition bill protests and subsequent months.
from us


Telegram እልመስጦአግያ+++
FROM American