tgoop.com/Menfesawigetmoch/124
Create:
Last Update:
Last Update:
+ሰኔ ሚካኤል+
አምና የዛሬ አመት ፥ያልጠከረ ልጅ ፥ታቅፌ በእጆቼ፤
ከቤትህ ባቀና ፥አንተን ልሳለምህ ፥ከደጅህ መጥቼ።
እግሮቼ ሳያውቁ ቢሰነካከሉ ጉድጓድ ቢቀናቸው፤
እንዳይሰበሩ መራመጃ ምንጣፍ፥ ሚካኤል ሆንካቸው።
የተከፈተውን የገባሁበትን ጉድጓድ ዘጋህና፤
ከቤቴ መለስከኝ ንግስህን አንግሼ፥ ገባሁኝ በደህና፤
ባህራን አደገ፥ ዳግም ጠነከረ፤
ሚካኤል ከጉድጓድ፥ ጠብቆን ነበረ፤
ያንተ የኔ ጌታ ይጠብቅ ነበረ፥ ያፀድቅ ነበረ፤
ያንተ አምላክ፥ እግዚአብሄር ያሳድግ ነበረ።
በበጎ እንዳስብህ፥ ዛሬን በትዝታ፤
መላኩ ሚካኤል ፥አለብኝ ውለታ።
አንተ ዘጋህልኝ፥ ጫፌ ሳይነካ፤
ምስጋናዬን ውሰድ፥ መባዬንም እንካ።
የማትረሳ መላክ፥ ጠባቂ ነህና፤
አረሳህም እኔ፥ አልረሳህምና፤
የተከፈተውን፥ ጉድጓድ ዘጋህና፤
አመቱ ሲደርስ አሰብኩህ በደህና።
አልረሳም አንተን፥ በሰኔ በሰኔ፤
ሚካኤል ወዳጄ፥ ምርኩዜ ነህ ለኔ።
++++
"በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ"
©ታዜና
™ #መንፈሳዊ_ግጥሞች
www.tgoop.com/Menfesawigetmoch
BY መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

Share with your friend now:
tgoop.com/Menfesawigetmoch/124