tgoop.com/yenetube/54718
Last Update:
በአዲስአበባ እና በስድስት ክልሎች የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ መከሰቱን ሪፖርት ገለፀ!
ኢንተርናሽናል ሜዲካል ኮርፕስ (IMC) በአዲስ አበባ እና በስድስት ክልሎች የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ(ኤምፖክስ) መከሰቱን አስታወቀ። ኢንተርናሽናል ሜዲካል ኮርፕስ ባሳለፍነው ሳምንት ሰኔ 6 ወን ባወጣው ሪፖርት፤ እስከ ሰኔ 3 ቀን በ አዲስ አበባ ከተማ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ሲዳማ፣ ሀረሪ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች 18 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው መረጋገጡን ገልጾ፤ የአንድ ሰው ይህወት ማለፉን አስታውቋል። ይህም የሞት መጠኑን ወደ 5.6 በመቶ ከፍ ያደርገዋል ብሏል።
በሽታው መጀመሪያ የተገኘው በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ የ27 ቀን ሕፃን ልጅ ላይ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር እና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ግንቦት 17 ቀን በጋራ አስታውቀዋል።ባሳለፍነው ሳምንትም በአማራ ክልል በመተማ እና ባሕርዳር ከተሞች በዝንጀሮ ፈንጣጣ (ኤምፖክስ) በሽታ የተያዙ ሁለት ሰዎች መገኘታቸውን የክልሉ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገልጿል።
በሽታው በመተማ አንድ ሰው እንዲሁም በባሕርዳር አንድ ሰው አጠቃላይ በሁለት ሰዎች ላይ የተገኘ ቢሆንም በሽተኞች በወቅቱ ተገቢውን ሕክምና አግኝተው በማገገም ላይ መሆናቸውን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
BY YeneTube
Share with your friend now:
tgoop.com/yenetube/54718