YENETUBE Telegram 54716
አሜሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ36 አገራት ዜጎች ላይ የጉዞ ዕገዳ ልትጥል ነው!

የትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያን ግበፅ እና ናይጄሪያን ጨምሮ የ36 አገራት ዜጎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ለማገድ ሃሳብ እንዳለው ሮይተርስ እና ዋሽንግተን ፖስት የተመለከቱት የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ውስጣዊ ሰነድ አመለከተ።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ የተፈረመው ለዲፕሎማቶች የተዘጋጀው ሰነድ ላይ በቀጣይ ዜጎቻቸው ላይ ዕገዳ ሊጣልባቸው የታሰቡት 36 አገራት ዝርዝር የሰፈረ ሲሆን፣ አገራቱ ከዕገዳው ለመውጣት ማከናወን የሚጠበቁባቸው ማስተካከያዎችም ተካተውበታል።

ሰነዱ ዜጎቻቸው ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ሙሉ ወይም ከፊል ዕገዳ የሚጣልባቸው አገራት በመለየት ያሉባቸውን ችግሮች በማስቀመጥ፤ ይህ ዕገዳ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት አገራቱ የሚጠበቅባቸውን መመዘኛዎች እና ማስተካከያዎችን እንዲያደርጉ የሁለት ወራት ጊዜ እንደሚሰጣቸው ተጠቅሷል።

ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ ለሚመለከታቸው ዲፕሎማቶች የተሠራጨው ሰነድ "[የውጭ ጉዳይ] መሥሪያ ቤቱ የተቀመጡ መመዘኛዎች እና ግዴታዎችን በ60 ቀናት የማያሟሉ ከሆነ ሙሉ ወይም ከፊል የጉዞ ዕገዳ የሚጣልባቸውን አሳሳቢ የሆኑ 36 አገራትን ለይቷል" ማለቱን ሮይተርስ አመልክቷል።

ባለፈው ግንቦት ኤርትራ፣ ሱዳን እና ሶማሊያን ጨምሮ ሰባት የአፍሪካ አገራት ባሉባቸው 12 አገራት ላይ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአገራቸውን እና የሕዝባቸውን ደኅንነት ለመጠበቅ በሚል ትዕዛዝ ፈርመው ተግባራዊ መሆኑ ይታወሳል።

(ቢቢሲ)
@YeneTube @FikerAssefa



tgoop.com/yenetube/54716
Create:
Last Update:

አሜሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ36 አገራት ዜጎች ላይ የጉዞ ዕገዳ ልትጥል ነው!

የትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያን ግበፅ እና ናይጄሪያን ጨምሮ የ36 አገራት ዜጎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ለማገድ ሃሳብ እንዳለው ሮይተርስ እና ዋሽንግተን ፖስት የተመለከቱት የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ውስጣዊ ሰነድ አመለከተ።

በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ የተፈረመው ለዲፕሎማቶች የተዘጋጀው ሰነድ ላይ በቀጣይ ዜጎቻቸው ላይ ዕገዳ ሊጣልባቸው የታሰቡት 36 አገራት ዝርዝር የሰፈረ ሲሆን፣ አገራቱ ከዕገዳው ለመውጣት ማከናወን የሚጠበቁባቸው ማስተካከያዎችም ተካተውበታል።

ሰነዱ ዜጎቻቸው ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ሙሉ ወይም ከፊል ዕገዳ የሚጣልባቸው አገራት በመለየት ያሉባቸውን ችግሮች በማስቀመጥ፤ ይህ ዕገዳ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት አገራቱ የሚጠበቅባቸውን መመዘኛዎች እና ማስተካከያዎችን እንዲያደርጉ የሁለት ወራት ጊዜ እንደሚሰጣቸው ተጠቅሷል።

ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ ለሚመለከታቸው ዲፕሎማቶች የተሠራጨው ሰነድ "[የውጭ ጉዳይ] መሥሪያ ቤቱ የተቀመጡ መመዘኛዎች እና ግዴታዎችን በ60 ቀናት የማያሟሉ ከሆነ ሙሉ ወይም ከፊል የጉዞ ዕገዳ የሚጣልባቸውን አሳሳቢ የሆኑ 36 አገራትን ለይቷል" ማለቱን ሮይተርስ አመልክቷል።

ባለፈው ግንቦት ኤርትራ፣ ሱዳን እና ሶማሊያን ጨምሮ ሰባት የአፍሪካ አገራት ባሉባቸው 12 አገራት ላይ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአገራቸውን እና የሕዝባቸውን ደኅንነት ለመጠበቅ በሚል ትዕዛዝ ፈርመው ተግባራዊ መሆኑ ይታወሳል።

(ቢቢሲ)
@YeneTube @FikerAssefa

BY YeneTube




Share with your friend now:
tgoop.com/yenetube/54716

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Ng was convicted in April for conspiracy to incite a riot, public nuisance, arson, criminal damage, manufacturing of explosives, administering poison and wounding with intent to do grievous bodily harm between October 2019 and June 2020. The administrator of a telegram group, "Suck Channel," was sentenced to six years and six months in prison for seven counts of incitement yesterday. "Doxxing content is forbidden on Telegram and our moderators routinely remove such content from around the world," said a spokesman for the messaging app, Remi Vaughn. So far, more than a dozen different members have contributed to the group, posting voice notes of themselves screaming, yelling, groaning, and wailing in various pitches and rhythms. How to build a private or public channel on Telegram?
from us


Telegram YeneTube
FROM American