tgoop.com/yenetube/54712
Last Update:
ኢራን አሜሪካን ኢላማ ካደረገች መዘዙ እንደሚከፋ የአሜሪካ ባለስልጣን አስጠነቀቀቁ
አሜሪካ ይህንን ያለችው ኢራን፤ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ዩኬ እስራኤልን የሚረዱ ከሆነ አጸፋውን እንደምትመልስ ማስጠንቀቋን ተከትሎ ነው።
እስራኤል በኢራን ላይ የፈጸመችውን ጥቃት በተመለከተ ከጥቃቱ በፊት አሜሪካ “ምክር ተጠይቃ” በምላሹ “ራሷን ለመከላከል መሰረታዊ ነው” የሚል ምላሽ እንደተሰጣት የአሜሪካ ባለስልጣን ተናግረዋል ።
“አሜሪካ ስለ ጥቃቱ ቀድሞ ቢነገራትም በነዚህ ጥቃቶች ላይ ወታደራዊ ተሳትፎ አልነበራትም” ሲሉ የአገሪቱ የአለም አቀፍ ድርጅት ጉዳዮች ቢሮ ከፍተኛ ባለስልጣን ማኮይ ፒት ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ተናግረዋል።
"ዋነኛው ቅድሚያ የምንሰጠው በቀጣናው ውስጥ ያሉ የአሜሪካ ዜጎች፣ ሰራተኞች እና ኃይሎችን ጥበቃ ነው።" ብለዋል።
ኢራን በቀጣናው ያሉ የአሜሪካ ዜጎች፣ የጦር ሰፈሮችን ወይም መሰረተ ልማቶችን ዒላማ ካደረገች “የሚከተላት መዘዝ አስከፊ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
የአሜሪካ አቋም ኢራን ስምምነት ማድረግ አለባት የሚል እንደሆኑ ገልጸው አገራቸው “ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ” ትሻለች ብለዋል።
“የኢራን አመራሮች በዚህ ወቅት መደራደራቸው ብልህነት ነው” ብለዋል።
ኢራን በእስራኤል ላይ እየወሰደች ያለችን አጸፋዊ እርምጃ ለማስቆም አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ዩናይትድ ኪንግደም እስራኤልን የሚረዱ ከሆነ ምላሹን እንደምትሰጥ ማስጠንቀቋን የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ ዘግቧል።
ሶስቱ አገራት ለእስራኤል ድጋፋቸውን ከሰጡ ኢራን በቀጣናው የሚገኙ የጦር ሰፈሮቻቸውን እና መርከቦችን ኢላማ እንደምታደርግ ዘገባዎች ወጥተዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
BY YeneTube

Share with your friend now:
tgoop.com/yenetube/54712