YENETUBE Telegram 54690
እስራኤል አዲስ ጥቃት መፈፀሟ ተነገረ !

የእስራኤል አየር ሃይል አመሻሹ ላይ በኢራን መአከላዊ ክፍል በመዝለቅ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ ።

የእስራኤል የስለላ ድርጅት እንደገለፀዉ ከሆነ አመሻሹ ላይ የፈፀመዉ ጥቃት የኢራንን የጸጥታ ተቋም ልብ ውስጥ ዘልቆ በመግባት ከኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ጋር ግንኙነት ያላቸውን ቦታዎች ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱን የአየር መከላከያ እና የባለስቲክ ሚሳኤል ማዕከላትን ኢላማዎች መምታቱን ገልጿል ።

የእስራኤል ፕሬዘዳንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ "ለኢራን ህዝብ ምንም ነገር እንደሌለን በቀጥታ እየነገርኳቸው ነው። እየተሰቃዩ መሆናቸውን እናውቃለን። የሚኖሩበትን ሁኔታ አይተናል… ትግላችን ከኢራን ህዝብ ጋር አይደለም ። ጥቃቱ የተካሄደው (ቦታው) ሰዎች በጎዳና ላይ በማይገኙበት ጊዜ ነው ፣ እናም በሲቪሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የተቻለንን ሁሉ አድርገናል" ብለዋል ።

ጥቃቱን በተመለከተ ከቴህራን በኩል በተገኘ መረጃ በተራራ ውስጥ በጥልቀት የተገነባው ፎርዶ የኑክሌያር ማብሊያ ጣቢያ ጨምሮ በርካታ ሰዉ የሚኖርባቸዉ አካባቢዎች በቦንብ መደብደቡን በጥቃቱ 78 ሰዎች መሞታቸውን እና ከሟቾቹ መካከል ህጻናትን ጨምሮ ሲቪሎች እንደሚገኙበት የኢራን መንግስት ቲቪ ገልጿል ።



tgoop.com/yenetube/54690
Create:
Last Update:

እስራኤል አዲስ ጥቃት መፈፀሟ ተነገረ !

የእስራኤል አየር ሃይል አመሻሹ ላይ በኢራን መአከላዊ ክፍል በመዝለቅ ጥቃት መፈፀሙን አስታወቀ ።

የእስራኤል የስለላ ድርጅት እንደገለፀዉ ከሆነ አመሻሹ ላይ የፈፀመዉ ጥቃት የኢራንን የጸጥታ ተቋም ልብ ውስጥ ዘልቆ በመግባት ከኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ጋር ግንኙነት ያላቸውን ቦታዎች ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱን የአየር መከላከያ እና የባለስቲክ ሚሳኤል ማዕከላትን ኢላማዎች መምታቱን ገልጿል ።

የእስራኤል ፕሬዘዳንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ "ለኢራን ህዝብ ምንም ነገር እንደሌለን በቀጥታ እየነገርኳቸው ነው። እየተሰቃዩ መሆናቸውን እናውቃለን። የሚኖሩበትን ሁኔታ አይተናል… ትግላችን ከኢራን ህዝብ ጋር አይደለም ። ጥቃቱ የተካሄደው (ቦታው) ሰዎች በጎዳና ላይ በማይገኙበት ጊዜ ነው ፣ እናም በሲቪሎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የተቻለንን ሁሉ አድርገናል" ብለዋል ።

ጥቃቱን በተመለከተ ከቴህራን በኩል በተገኘ መረጃ በተራራ ውስጥ በጥልቀት የተገነባው ፎርዶ የኑክሌያር ማብሊያ ጣቢያ ጨምሮ በርካታ ሰዉ የሚኖርባቸዉ አካባቢዎች በቦንብ መደብደቡን በጥቃቱ 78 ሰዎች መሞታቸውን እና ከሟቾቹ መካከል ህጻናትን ጨምሮ ሲቪሎች እንደሚገኙበት የኢራን መንግስት ቲቪ ገልጿል ።

BY YeneTube






Share with your friend now:
tgoop.com/yenetube/54690

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Choose quality over quantity. Remember that one high-quality post is better than five short publications of questionable value. How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) The main design elements of your Telegram channel include a name, bio (brief description), and avatar. Your bio should be: As of Thursday, the SUCK Channel had 34,146 subscribers, with only one message dated August 28, 2020. It was an announcement stating that police had removed all posts on the channel because its content “contravenes the laws of Hong Kong.” 4How to customize a Telegram channel?
from us


Telegram YeneTube
FROM American