YENETUBE Telegram 54684
ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ በስድስተኛው ቀን ከእስር ተፈታ!

የ'ኢትዮጵያ ኢንሳይደር' የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ወልደየስ ከእስር መፈታቱን ጠበቃው አቶ ቤተማርያም አለማየሁ ለቢቢሲ ተናገሩ።ተስፋለም ከእስር የተፈታው ዛሬ አርብ፣ ሰኔ 6/2017 ዓ.ም እስጢፋኖስ አካባቢ ከሚገኘው የፖሊስ መምሪያ መሆኑን ቤተማሪያም ገልጸዋል።

ባለፈው ማክሰኞ ሰኔ 3/ 2017 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ የቄርቆስ ምድብ ችሎት በ15 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና ከእስር እንዲፈታ ወስኖ ነበር። ሆኖም ፖሊስ ለአዲስ አበባ ይግባኝ ሰሚ ችሎት አቤቱታ በማቅረቡ ሳይፈታ ቀርቷል።ይግባኝ ሰሚ ችሎት ሰኔ 4/ 2017 ዓ.ም. ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ የፖሊስን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማጽናት ጋዜጠኛው የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅለት በድጋሚ በይኗል።

ነገር ግን ፖሊስ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔን በመቃወም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰበር ሰሚ ችሎት በድጋሜ አቤቱታ አቅርቧል።ሰበር ሰሚ ችሎቱ ትላንት ሐሙስ የፖሊስ ይግባኝ አቤቱታ "አያስቀርብም" በሚል መወሰኑን የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ባለቤት ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ባወጣው መግለጫ ላይ አስታውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa



tgoop.com/yenetube/54684
Create:
Last Update:

ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ በስድስተኛው ቀን ከእስር ተፈታ!

የ'ኢትዮጵያ ኢንሳይደር' የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ወልደየስ ከእስር መፈታቱን ጠበቃው አቶ ቤተማርያም አለማየሁ ለቢቢሲ ተናገሩ።ተስፋለም ከእስር የተፈታው ዛሬ አርብ፣ ሰኔ 6/2017 ዓ.ም እስጢፋኖስ አካባቢ ከሚገኘው የፖሊስ መምሪያ መሆኑን ቤተማሪያም ገልጸዋል።

ባለፈው ማክሰኞ ሰኔ 3/ 2017 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ የቄርቆስ ምድብ ችሎት በ15 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና ከእስር እንዲፈታ ወስኖ ነበር። ሆኖም ፖሊስ ለአዲስ አበባ ይግባኝ ሰሚ ችሎት አቤቱታ በማቅረቡ ሳይፈታ ቀርቷል።ይግባኝ ሰሚ ችሎት ሰኔ 4/ 2017 ዓ.ም. ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ የፖሊስን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማጽናት ጋዜጠኛው የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅለት በድጋሚ በይኗል።

ነገር ግን ፖሊስ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔን በመቃወም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰበር ሰሚ ችሎት በድጋሜ አቤቱታ አቅርቧል።ሰበር ሰሚ ችሎቱ ትላንት ሐሙስ የፖሊስ ይግባኝ አቤቱታ "አያስቀርብም" በሚል መወሰኑን የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ባለቤት ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ባወጣው መግለጫ ላይ አስታውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa

BY YeneTube




Share with your friend now:
tgoop.com/yenetube/54684

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

SUCK Channel Telegram Polls A vandalised bank during the 2019 protest. File photo: May James/HKFP. Hui said the time period and nature of some offences “overlapped” and thus their prison terms could be served concurrently. The judge ordered Ng to be jailed for a total of six years and six months. Unlimited number of subscribers per channel
from us


Telegram YeneTube
FROM American