ORTODOXTEWAHEDO Telegram 21713
+ሁለቱ መምህራን+

በመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ

አንደኛው መምህር የዓለም መድኀኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው
ሁለተኛው መምህር ከአንደኛው መምህር ለመማር የመጣው ኒቆዲሞስ ነው

ኒቆዲሞስ ብሉይ ኪዳንን ለአይሁድ የሚስተምር
አይሁድን በሶስት ነገር የሚመራ ነበር
በእውቀት
በገንዘብ
በሥልጣን
በእውቀት መምህራቸው ነበር
በገንዘብ ከአይሁድ የተሻለ ሀብት ነበረው
በሥልጣን አለቃቸው ሁኖ ተሹሞ ነበር

ኒቆዲሞስ የአይሁድ መምህር ሁኖ በሚያስተምርት ወቅት የመምህራን መምህር የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን ሊያስተም በምድር ላይ ተገለጠ
ያን ጊዜ ኒቆዲሞስ ሊማር ወደ ጌታችን በሌሊት ሄደ

ኒቆዲሞስ በሌሊት መማር የፈለገው ስለ አምስት ነገሮች ነው
1 አይሁድን ፈርቶ
በቀን ልማር ስሄድ አይሁድ ቢያዩኝ ከሥልጣኔ ይሽሩኛል ሀብቴን ይቀሙኛል ብሎ ፈርቶ ነው
በኢየሱስ ያመነ ከምኩራብ ይሰደድ የሚል ሕግ አይሁድ አውጥተው ነበርና

2 ውዳሴ ከንቱ ፈልጎ
መምህር ነኝ ይላል ለምን ሊማር ይሄዳል ብለው እንዳይነቅፉት ተደብቆ በሌሊት ሂዷል

3 በኦሪት ህግ ውስጥ እንዳለ ለመግለጽ
ኦሪት ሌሊት ወንጌል መዓልት ትባላለች
በኦሪት ሁሉም ሰው ቢሞት ወደ ጨለማዋ ሲኦል ይወርድ ስለ ነበር ኦሪት ጨለማ ትባላለች
ወንጌል የነፍስ ብርሃን ናትና መዓልት ትባላለች

4 ምስጢሩን በደንብ ለመረዳት
የቀን ልቡና ባካና ነው ዓይን በቀን ወጭ ወራጁን ሀላፊ አግዳሚውን ሲአይ
ጆሮ የተለያዩ ድንምጾችን ሲሰማ ልብ ይባክናል
በሌሊት ግን ሁሉ ጸጥ ያለ የሚሰማ ድምጽ የሌለበት የሚንቀሳቀስ የማይታይበት ስለሆነ የሌሊት ልቡና ሀሳቡ የተሰበስበ ነው ስለዚህ ጌታችን የሚነግረውን ምሥጢር ሁሉ ለመረዳት ከቀኑ ይልቅ ሌሊቱን መርጦ ሂዷል

5 የዕረፍት ጊዜውን መርጦ
ቀን አይሁድን ሲያስተምር ሲመክር የተጣላ ሲያስታርቅ የተበደለ ሲያስክስ የተቀማ ሲያስመልስ ወንበር ዘርግቶ ሲፈርድ ይውል ነበር
ሌሊት ግን ሁሉም ወደ የቤቱ ሲሄድ ኒቆዲሞስ ደክሞኛል ልርፍ ሳይል ከስራ እንደዋለ እንቅልፉን ትቶ ለመማር ወደ ጌታችን ሂዷል

ጌታችንም ምሥጢረ ሥላሴን ለአብርሃም በሶስት ሰዎች አምሳል ወደ ቤቱ ሂዶ እንደገለጠ
ምሥጢረ ሥጋዌን ለቶማስ በዝግ ቤት ገብቶ ጎኔን ዳሰኝ ብሎ እንደገለጠ
ምሥጢረ ቁርባንን ለሐዋርያት በዕለተ ሐሙስ በኀብስትና በወይን ነገ የሚቆረሰው ሥጋዬ የሚፈሰው ደሜ ይህ ነው ብሎ እንደገለጠ
ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታንን ለማርታና ለማርያ ወንድማቸው ዓልአዛርን ከመቃብር አስነስቶ ለኢያኤሮስ ልጁን ከሞት አስነስቶ እንዳስተማራቸው

ለኒቆዲሞስም ምሥጢረ ጥምቀትን ገልጦ አስተምሮታል
ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም ብሎ ስለ ጥምቀት ሲያስተምረው
መወለድን እንጂ መወለጃውን ከምን እንደሚወለድ አልገለፀለትም ነበርና ኒቆዲሞስ ትምህርቱ ሲከብደው ሰው ካረጀ በኋላ ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅጸን ገብቶ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ብሎ ጠየቀ
ጌታችንም ከውሃና ከመንፈስ ካለተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም
ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋል ስላልኩህ አታድንቅ ነፋስ ወደ ወደደው ይነፍሳል ድምጹን ትሰማለህ ነግር ግን ከየት እንደመጣ ወደየትም እንደሚሄድ አይታወቅም ብሎ ረቂቁን ልደት ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ እንደሆነ በረቂቁ ነፋስ መስሎ አስተማረው

ዳግም ልደት ረቂቅ ነውና በረቀቀው ነፋስ መስሎታል
ረቂቃን ፍጥረታት ሶስት ናቸው
መላእክት
ነፍሳት
ነፋሳት እነዚህ ሶስቱ ረቂቃን ፍጥረታት ናቸው
ከነዚህ አንዱ ነፋስን ጠቅሶ አስተምሮታል በእርግጥ የነፋስ ድምጽ አለው ወይ?
የሚል ካለ የነፋስ ድምጹ ባህር ሲገስጽ ማእበል ሞገድ ሲያስነሳ ዛፍ ሲያንቀሳቅስ ድምጹ ይሰማል
ኒቆዲሞስ ግን መልሶ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ?አለዉ

ጌታችንም አንተ የእስራኤል መምህራቸው ነህ ይሄን እንዴት አታውቅም ብሎ ገሰጸው
መምህር ብሎ መምህርነቱን ነገረው
አታውቅም ብሎ አላዋቂነቱ ገለጸበት
የምናውቀውን እንመሰግራለን ያየነውን እንናገራለን ነገር ግን ምስክርነታችን አትቀበሉንም
በምድር ያለውን ብነግራቸው ካላመናችው በሰማይ ያለውን ብነግራችው እንዴት ታምናላችው? ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም እርሱ የሰው ልጅ በሰማይ ይኖራል አለው ከዚህ በሇላ ኒቆዲሞስ አምኗል ሰማያዊ አምላክ መሆኑንም ተረድቷል

ኒቆዲሞስም ተደብቆ በሌሊት ሰው ሳያየው ምስጢረ ጥምቀትን ተምሮ ብቻ አልቀረም በአደባባይ በመጨረሻዋ ሰዓት ሃይማኖቱን ገልጿል
ያስተምራቸው ይመራቸው የነበሩት አይሁድ የኒቆዲሞስ መምህር የሆነውን ክርስቶስን በቅናት ሰቅለው ሲገድሉት የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉ ሸሽተው የሚቀብረው ባጣ ጊዜ ኒቆዲሞስ በአደባብ ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር የክርስቶስ ተከታይ መሆኑን አሳይቷል
ያኔ በመከራ ሰዓት ሁሉ ሲሸሽ ኒቆዲሞስና ዮሴፍ ተገኝተዋል

መልኩን ለማየት ይከተሉት የነበሩት ሁሉ ሰውነቱ በደም ሲታለል ደምግባቱ ሲጠፋ ከፊቱ ባልተገኙበት ጊዜ

ኀብስት አበርክተው የሚያበሉ እጆቹ ሲቸነከረው ብንራብ አበርክቶ ያበላናል ብለው የሚከተሉት ሁሉ በጠፉበት ጊዜ

ብንሞት ያነሳናል ብንታመም ይፈውሰናል ብለው ሲከተሉት የነበሩት ሁሉ እሱ ታሞ ሲሞት በሸሹበት ጊዜ

የሚያደርገውን ታምራት ለማየት በመደነቅ የሚከተሉት ሁሉ ከፊቱ ባልተገኙበት ጊዜ

ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ ወንጌልን ሲማሩ የነበሩት ሁሉ ከእመቤታችንና ከዮሐንስ በቀር ፈርተው ሸሽተው ከመስቀል አውርዶ የሚቀብረው በጠፋበት ጊዜ

ስላሳ ስምንት ዓመት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁረኛ ተይዞ በቃል ፈውሶ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ያለውማ ይባስ ብሎ ባአደባባይ አንተ ነህ ያዳንከኝ ብሎ በጥፊ በመታው ጊዜ

ሁሉ ፈርቶ የሚቀብረው አጥቶ ከሞተ በሇላ መስቀል ላይ ሁለት ሰዓት እንደተሰቀለ ሲቆይ

ከተወለደበት ጀምሮ ዕውር የነበረው ዓይኑን ያበራለት የት ገብቶ ይሆን?

ሰባት አጋንንት ያወጣላት መግደላዊት ማርያም ከመስቀል አውርዳ ለምን አልቀበረችውም? ከዚያ ሁሉ ስቃይ የፈወሷት ከአጋንንት እስራት ነጻ ያወጣት የሚቀብረው ሲያጣ

12 ዓመት ሙሉ ደም ይፈሳት የነበረቸው ሴት ሰው ሲንቃት ሲጸየፋት ከሰው እኩል ያደረጋት መስቀል ላይ ሲውል የት ሂዳ ይሆን?

በደንጋይ ተቀጥቅጣ ትሙት ብለው ተከሳ ሲያመጧት በሰላም ሂጂ ብሎ ያሰናበታት ከሞት ያዳናት መስቀል ላይ ተሰቅሎ የሚቀብረው ሲያጣ ሆዷ እንዴት ቻለ?

ከሞት ያስነሰው ዓልአዛር የት ገባ ?
ሞት ፈርቶ ይሆን ከመስቀል አውርዶ ያልቀበረው?

የሚገርመው እሱ ተሰቅሎ በመሞቱ የተነሱ ከአምስት መቶ በላይ ሙታን ነበሩ እነሱ እንኳን ከሞት በመነሳታቸው ተደሰቱ እንጂ ከመስቀል አውርደው አልቀበሩት

ያን ጊዜ ነበረ ሰው ባጣበት ጊዜ የሚቀብረው ባጣ ጊዜ
በድብቅ በሌሊት ይማር የነበርው ኒቆዲሞስ ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋራ የመጣው
እሱን ሰቅለው የገደሉ ይገሉናል ሳይሉ ከመስቀል አውርደው አቅፈው እያለቀሱ ስመው በበፍታ ሲገንዙት( ወአንበስበሰ አዕይንቲሁ እግዚእ ኢየሱስ )ጊታችን አምላካችን በባህርየ መለኮቱ ዓይኖቹን ግልጽልጽ አድርጎ እንደሩቅ ብእሲ ዝም ብላችው አትገንዙኝ



tgoop.com/ortodoxtewahedo/21713
Create:
Last Update:

+ሁለቱ መምህራን+

በመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ

አንደኛው መምህር የዓለም መድኀኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው
ሁለተኛው መምህር ከአንደኛው መምህር ለመማር የመጣው ኒቆዲሞስ ነው

ኒቆዲሞስ ብሉይ ኪዳንን ለአይሁድ የሚስተምር
አይሁድን በሶስት ነገር የሚመራ ነበር
በእውቀት
በገንዘብ
በሥልጣን
በእውቀት መምህራቸው ነበር
በገንዘብ ከአይሁድ የተሻለ ሀብት ነበረው
በሥልጣን አለቃቸው ሁኖ ተሹሞ ነበር

ኒቆዲሞስ የአይሁድ መምህር ሁኖ በሚያስተምርት ወቅት የመምህራን መምህር የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን ሊያስተም በምድር ላይ ተገለጠ
ያን ጊዜ ኒቆዲሞስ ሊማር ወደ ጌታችን በሌሊት ሄደ

ኒቆዲሞስ በሌሊት መማር የፈለገው ስለ አምስት ነገሮች ነው
1 አይሁድን ፈርቶ
በቀን ልማር ስሄድ አይሁድ ቢያዩኝ ከሥልጣኔ ይሽሩኛል ሀብቴን ይቀሙኛል ብሎ ፈርቶ ነው
በኢየሱስ ያመነ ከምኩራብ ይሰደድ የሚል ሕግ አይሁድ አውጥተው ነበርና

2 ውዳሴ ከንቱ ፈልጎ
መምህር ነኝ ይላል ለምን ሊማር ይሄዳል ብለው እንዳይነቅፉት ተደብቆ በሌሊት ሂዷል

3 በኦሪት ህግ ውስጥ እንዳለ ለመግለጽ
ኦሪት ሌሊት ወንጌል መዓልት ትባላለች
በኦሪት ሁሉም ሰው ቢሞት ወደ ጨለማዋ ሲኦል ይወርድ ስለ ነበር ኦሪት ጨለማ ትባላለች
ወንጌል የነፍስ ብርሃን ናትና መዓልት ትባላለች

4 ምስጢሩን በደንብ ለመረዳት
የቀን ልቡና ባካና ነው ዓይን በቀን ወጭ ወራጁን ሀላፊ አግዳሚውን ሲአይ
ጆሮ የተለያዩ ድንምጾችን ሲሰማ ልብ ይባክናል
በሌሊት ግን ሁሉ ጸጥ ያለ የሚሰማ ድምጽ የሌለበት የሚንቀሳቀስ የማይታይበት ስለሆነ የሌሊት ልቡና ሀሳቡ የተሰበስበ ነው ስለዚህ ጌታችን የሚነግረውን ምሥጢር ሁሉ ለመረዳት ከቀኑ ይልቅ ሌሊቱን መርጦ ሂዷል

5 የዕረፍት ጊዜውን መርጦ
ቀን አይሁድን ሲያስተምር ሲመክር የተጣላ ሲያስታርቅ የተበደለ ሲያስክስ የተቀማ ሲያስመልስ ወንበር ዘርግቶ ሲፈርድ ይውል ነበር
ሌሊት ግን ሁሉም ወደ የቤቱ ሲሄድ ኒቆዲሞስ ደክሞኛል ልርፍ ሳይል ከስራ እንደዋለ እንቅልፉን ትቶ ለመማር ወደ ጌታችን ሂዷል

ጌታችንም ምሥጢረ ሥላሴን ለአብርሃም በሶስት ሰዎች አምሳል ወደ ቤቱ ሂዶ እንደገለጠ
ምሥጢረ ሥጋዌን ለቶማስ በዝግ ቤት ገብቶ ጎኔን ዳሰኝ ብሎ እንደገለጠ
ምሥጢረ ቁርባንን ለሐዋርያት በዕለተ ሐሙስ በኀብስትና በወይን ነገ የሚቆረሰው ሥጋዬ የሚፈሰው ደሜ ይህ ነው ብሎ እንደገለጠ
ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታንን ለማርታና ለማርያ ወንድማቸው ዓልአዛርን ከመቃብር አስነስቶ ለኢያኤሮስ ልጁን ከሞት አስነስቶ እንዳስተማራቸው

ለኒቆዲሞስም ምሥጢረ ጥምቀትን ገልጦ አስተምሮታል
ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም ብሎ ስለ ጥምቀት ሲያስተምረው
መወለድን እንጂ መወለጃውን ከምን እንደሚወለድ አልገለፀለትም ነበርና ኒቆዲሞስ ትምህርቱ ሲከብደው ሰው ካረጀ በኋላ ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅጸን ገብቶ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ብሎ ጠየቀ
ጌታችንም ከውሃና ከመንፈስ ካለተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም
ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋል ስላልኩህ አታድንቅ ነፋስ ወደ ወደደው ይነፍሳል ድምጹን ትሰማለህ ነግር ግን ከየት እንደመጣ ወደየትም እንደሚሄድ አይታወቅም ብሎ ረቂቁን ልደት ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ እንደሆነ በረቂቁ ነፋስ መስሎ አስተማረው

ዳግም ልደት ረቂቅ ነውና በረቀቀው ነፋስ መስሎታል
ረቂቃን ፍጥረታት ሶስት ናቸው
መላእክት
ነፍሳት
ነፋሳት እነዚህ ሶስቱ ረቂቃን ፍጥረታት ናቸው
ከነዚህ አንዱ ነፋስን ጠቅሶ አስተምሮታል በእርግጥ የነፋስ ድምጽ አለው ወይ?
የሚል ካለ የነፋስ ድምጹ ባህር ሲገስጽ ማእበል ሞገድ ሲያስነሳ ዛፍ ሲያንቀሳቅስ ድምጹ ይሰማል
ኒቆዲሞስ ግን መልሶ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ?አለዉ

ጌታችንም አንተ የእስራኤል መምህራቸው ነህ ይሄን እንዴት አታውቅም ብሎ ገሰጸው
መምህር ብሎ መምህርነቱን ነገረው
አታውቅም ብሎ አላዋቂነቱ ገለጸበት
የምናውቀውን እንመሰግራለን ያየነውን እንናገራለን ነገር ግን ምስክርነታችን አትቀበሉንም
በምድር ያለውን ብነግራቸው ካላመናችው በሰማይ ያለውን ብነግራችው እንዴት ታምናላችው? ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም እርሱ የሰው ልጅ በሰማይ ይኖራል አለው ከዚህ በሇላ ኒቆዲሞስ አምኗል ሰማያዊ አምላክ መሆኑንም ተረድቷል

ኒቆዲሞስም ተደብቆ በሌሊት ሰው ሳያየው ምስጢረ ጥምቀትን ተምሮ ብቻ አልቀረም በአደባባይ በመጨረሻዋ ሰዓት ሃይማኖቱን ገልጿል
ያስተምራቸው ይመራቸው የነበሩት አይሁድ የኒቆዲሞስ መምህር የሆነውን ክርስቶስን በቅናት ሰቅለው ሲገድሉት የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉ ሸሽተው የሚቀብረው ባጣ ጊዜ ኒቆዲሞስ በአደባብ ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር የክርስቶስ ተከታይ መሆኑን አሳይቷል
ያኔ በመከራ ሰዓት ሁሉ ሲሸሽ ኒቆዲሞስና ዮሴፍ ተገኝተዋል

መልኩን ለማየት ይከተሉት የነበሩት ሁሉ ሰውነቱ በደም ሲታለል ደምግባቱ ሲጠፋ ከፊቱ ባልተገኙበት ጊዜ

ኀብስት አበርክተው የሚያበሉ እጆቹ ሲቸነከረው ብንራብ አበርክቶ ያበላናል ብለው የሚከተሉት ሁሉ በጠፉበት ጊዜ

ብንሞት ያነሳናል ብንታመም ይፈውሰናል ብለው ሲከተሉት የነበሩት ሁሉ እሱ ታሞ ሲሞት በሸሹበት ጊዜ

የሚያደርገውን ታምራት ለማየት በመደነቅ የሚከተሉት ሁሉ ከፊቱ ባልተገኙበት ጊዜ

ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ ወንጌልን ሲማሩ የነበሩት ሁሉ ከእመቤታችንና ከዮሐንስ በቀር ፈርተው ሸሽተው ከመስቀል አውርዶ የሚቀብረው በጠፋበት ጊዜ

ስላሳ ስምንት ዓመት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁረኛ ተይዞ በቃል ፈውሶ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ያለውማ ይባስ ብሎ ባአደባባይ አንተ ነህ ያዳንከኝ ብሎ በጥፊ በመታው ጊዜ

ሁሉ ፈርቶ የሚቀብረው አጥቶ ከሞተ በሇላ መስቀል ላይ ሁለት ሰዓት እንደተሰቀለ ሲቆይ

ከተወለደበት ጀምሮ ዕውር የነበረው ዓይኑን ያበራለት የት ገብቶ ይሆን?

ሰባት አጋንንት ያወጣላት መግደላዊት ማርያም ከመስቀል አውርዳ ለምን አልቀበረችውም? ከዚያ ሁሉ ስቃይ የፈወሷት ከአጋንንት እስራት ነጻ ያወጣት የሚቀብረው ሲያጣ

12 ዓመት ሙሉ ደም ይፈሳት የነበረቸው ሴት ሰው ሲንቃት ሲጸየፋት ከሰው እኩል ያደረጋት መስቀል ላይ ሲውል የት ሂዳ ይሆን?

በደንጋይ ተቀጥቅጣ ትሙት ብለው ተከሳ ሲያመጧት በሰላም ሂጂ ብሎ ያሰናበታት ከሞት ያዳናት መስቀል ላይ ተሰቅሎ የሚቀብረው ሲያጣ ሆዷ እንዴት ቻለ?

ከሞት ያስነሰው ዓልአዛር የት ገባ ?
ሞት ፈርቶ ይሆን ከመስቀል አውርዶ ያልቀበረው?

የሚገርመው እሱ ተሰቅሎ በመሞቱ የተነሱ ከአምስት መቶ በላይ ሙታን ነበሩ እነሱ እንኳን ከሞት በመነሳታቸው ተደሰቱ እንጂ ከመስቀል አውርደው አልቀበሩት

ያን ጊዜ ነበረ ሰው ባጣበት ጊዜ የሚቀብረው ባጣ ጊዜ
በድብቅ በሌሊት ይማር የነበርው ኒቆዲሞስ ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋራ የመጣው
እሱን ሰቅለው የገደሉ ይገሉናል ሳይሉ ከመስቀል አውርደው አቅፈው እያለቀሱ ስመው በበፍታ ሲገንዙት( ወአንበስበሰ አዕይንቲሁ እግዚእ ኢየሱስ )ጊታችን አምላካችን በባህርየ መለኮቱ ዓይኖቹን ግልጽልጽ አድርጎ እንደሩቅ ብእሲ ዝም ብላችው አትገንዙኝ

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ


Share with your friend now:
tgoop.com/ortodoxtewahedo/21713

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Avoid compound hashtags that consist of several words. If you have a hashtag like #marketingnewsinusa, split it into smaller hashtags: “#marketing, #news, #usa. While some crypto traders move toward screaming as a coping mechanism, many mental health experts have argued that “scream therapy” is pseudoscience. Scientific research or no, it obviously feels good. Channel login must contain 5-32 characters The group also hosted discussions on committing arson, Judge Hui said, including setting roadblocks on fire, hurling petrol bombs at police stations and teaching people to make such weapons. The conversation linked to arson went on for two to three months, Hui said. 4How to customize a Telegram channel?
from us


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ
FROM American