Telegram Web
በዓለ ቅዱስ ሚካኤል

እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ!

ሚካኤል ማለት ‹‹መኑ ከመ አምላክ (እግዚአብሔር)፤ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው›› ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እርሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ፣ ርኀሩኅ፣ ኃያልና ረቂቅ ማንም እንደሌለ የሚያመለክት ነው፡፡

ቅዱስ ሚካኤል ሌሎች መጠሪያዎች አሉት፤ እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ እነርሱም ‹‹መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ፣…›› ናቸው፡፡ መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በእርሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸና ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡

መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡ መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታልና በእርሱ አማካኝነት ይሠራል ለማለት ነው፡፡

ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ሁሉ ልዕልና ላይ ትሕትናን ደርቦ የያዘ፣ በጸሎቱ ተማጽኖና በተራዳኢነት አምኖ ለሚለምነው ሁሉ ፈጥኖ በመድረስ ከሠራዊተ አጋንንት ተንኰል የሚያድን መልአክ እንደሆነ በቅዱስ መጽሐፍ ተጠቅሶ እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ ሙሴንና እስራኤልን በሲና በረሃ (ዘፀ.፳፫÷፳-፳፪)፤ (ዘፀ.፲፬÷፲፭-፳) ኢያሱን በኢያሪኮ (ኢያ.፭÷፲፫-፲፭)፤ ከአሞራውያንም እጅ ሕዝቅያስን እንደረዳቸው ተጽፏል፡፡ (ኢሳ.፴፯÷፴፮) በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ፲ ቁጥር ፲፫ ላይ ‹‹የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሃያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ›› በማለት የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት ተገልጿል፡፡ በዚሁ የመጽሐፍ ክፍል ምዕራፍ ፲፪ ቁጥር ፩ ላይ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል›› በማለት ታላቅነቱን፣ ለሰው ልጆች ሁሉ በአማላጅነቱና በተራዳኢነት የሚቆም እንደሆነ በማያሻማ ቃል ተገልጿል፡፡

በአጠቃላይ በኦሪት የእግዚአብሔር መልአክ እየተባለ የሚጠራው አብዛኛውን ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያስተምራሉ፤ በድርሳነ ሚካኤልም ተጽፎ ይገኛል፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ያልረዳው ቅዱስ የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በዘመነ ሰመዕታትም ሰማዕታትን በተጋድሎ ያጸናቸው ይህ ሩኅሩኅ መላክ እንደሆነ በእነ ቅዱስ ፋሲለደስ እንዲሁም በእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገድላት ላይ በሰፊው ተገልጿል፡፡
የቤተ ክርስቲያን አባቶች በየወሩ በ፲፪ ቀን መታሰቢያውን እንድናደርግ አዘውናል፡፡ ይህንንም ያልቻለ በዓመት አራት ዓበይት በዓላትን ከቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ጀምሮ እንደተቻለ ማዝከር ይገባል፡፡ እነዚህም ኅዳር ፲፪ ቀን ቀጥሎ ሰኔ ፲፪ ቀን ከዚያም ነሐሴ ፲፪ ቀንና ታኅሣሥ ፲፪ ቀን ናቸው፡፡

ሰኔ ፲፪፡- በቅዳሴያችን ‹‹ተውህቦ ምሕረት ለሚካኤል፤ ለሚካኤል ምሕረት (ይቅርታ ርኀራኄ) ተሰጠው እንላለን፤ ነቢዩ ሄኖክም ምሕረት ለሚካኤል መሰጠቱን ገልጿል፤ ትሕትናውን ታዛዥነቱን አስረድቷል፡፡ (ሄኖ.፮÷፭፣፲÷፲፪)

የሰማያውያን ሠራዊት አለቃ፣ ለሰው ሁሉ የሚራራና ስለ ሰው ልጆች ሳያቋርጥ ወደ ፈጣሪው የሚለምን፣ ርኀሩኀና ትሑት የሆነው ኃያሉ ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን ከሞት ያዳነበት፣ የሞቱን ደብዳቤ ወደ ሕይወት የቀየረበት የመታሰቢያው ዕለት ነው፡፡

@ortodoxtewahedo
ከሦስት ወራት በፊት ጥር 2/2016 ዓ.ም. ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ጀምሮ “አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ” የሚሉ ልጥፎች በበርካታ የኢትዮጵያውያን የፌስቡክ አካውንቶች እና ገጾች መሠራጨት ጀመሩ።
በፎቶ እና ጽሁፍ ከተቀናበረ ምስል ጋር የተሠራጩት እነዚህ ልጥፎች ፌስቡክ ላይ የወጡት፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ አቡነ ጴጥሮስ ከአዲስ አበባ ወደ አሜሪካ መጓዛቸውን ተከትሎ ነበር።
የኒው ዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር የወጡት፤ “ይፋዊ የሆነውን መደበኛ የአሠራር ሥርዓት ተከትለው” እንደሆነ ቢቢሲ ከቤተ ክርስቲያኗ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
በዕለቱ የተሠራጩት ሦስት ዋነኛ ጽሁፎች “ሰበር መረጃ፤ አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ”፣ “አሜሪካዊው አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮብልለዋል!” እና “ከአሜሪካዊ አቡነ ጴጥሮስ ኩብለላ ጀርባ ያሉ እውነታዎች!” የሚል መግቢያ ያላቸው ናቸው።
ጽሁፎቹ አቡነ ጴጥሮስን፤ “በቤተ ክህነት ውስጥ ህቡዕ የፖለቲካ አደረጃጀት በመምራት” እና “የቤተክህነት ሃብት የሆነ በርካታ ገንዘብ እና ንብረት ይዞ በመጥፋት” ይከስሳሉ።
ከሦስቱ ጽሁፎች ውስጥ በብዛት የተሠራጨው “ሰበር መረጃ፤ አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ” የሚለው ሲሆን፣ ይህ ጽሁፍ በጥር 2 እና 3/2016 ዓ.ም. ብቻ ቢያንስ 1,004 ጊዜ በተለያዩ የፌስቡክ አካውንት እና ገጾች እንደተለጠፈ ቢቢሲ አረጋግጧል። ከግራፊክስ ምስሎች ጋር የተለጠፈው ይህ ጽሁፍ፤ ጥር ሁለት ቀን ብቻ ይህ ቢያንስ 898 ጊዜ ፌስቡክ ላይ ተጋርቷል።
https://bbc.in/3Q4Mfjh

https://www.facebook.com/100068240109154/posts/736159432002054/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v
ኒቆዲሞስ ፯ ሣምንት ዐብይ ጾም

ኒቆዲሞስ የትህትና፣ የትጋትና የጽናት አብነት ነው።

ኒቆዲሞስ ማለት:- በግሪክ ቋንቋ “አሸናፊ/ነት” ማለት ነው፡፡

ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ ብቻ ሳይሆን የፈሪሳውያን አለቃ፣ የኦሪት መምህር ብቻ ሳይሆን የኦሪት ምሁርም ነበር፡፡

በእርሱ ደረጃ የነበሩ ታላላቅ የአይሁድ ምሁራን መንፈሳዊ ስልጣናቸውና ሹመታቸው የእግዚአብሔር ስጦታ መሆኑን ረስተው በህዝቡ ላይ የሚመፃደቁ ነበሩ፡፡

በዘመናቸው እውቀትን የሚገልጥ እውነተኛ አምላክ የካህናት አለቃ ኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛ ለመሆን ወደዚህ ዓለም ሲመጣ አልወደዱም ነበር። እርሱ ግን የትህትና ባለቤት በመሆኑ ሁሉን ችሎ ያስተምር ነበር።

ዮሐ ፫÷፩-፲፪ ፣ ማቴ ፭÷፳
ማቴ ፲፮÷ ፮ ኢየሱስም፦ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን ርሾ ተጠንቀቁና ተጠበቁ አላቸው።

እግዚአብሔር አምላክ ትዕግስቱን ሰጥቶ ክፉውን በመጠየፍ ደግ ደጉን ብቻ በመስራት የመንግሥቱ ወራሾች፣ የስሙ ቀዳሾች ያድርገን፣ ወዶና ፈቅዶ ለዚህ ዕለት እንደ አደረሰን ሁሉ እንድ በደላችን ሳይመለከት ቀሪውን ጊዜ ያስፈጽመን አሜን!

" ኢትዮጵያ ሠላምሽ ይብዛ"

@ortodoxtewahedo
". . .አማን መነኑ ሰማዕታት ጣዕማ ለዛ ዓለም
ወከዐው ደሞሙ በእንተ እግዚአብሔር
ወተዐገሡ ሞተ መሪረ በእንተመንግሥተ ሰማያት
ተሣሃለነ በከመ ዕበየ ሣህልከ:: ሰአሊ ለነ ቅድስት "

@ortodoxtewahedo
."ሆዳችሁ ጠግቦ ከምታቀርቡት አንድ መቶ ጸሎትና ተራራ ከሚያርድ ድምጻችሁ ይልቅ በጾም ውስጥ ሆናችሁ የምታቀርቡት አንድ ጸሎት ተሰሚነት አለው።"

#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ

@ortodoxtewahedo
+ . . . አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም:: እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች:: ስለዚህ እልሃለሁ : እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአቷ ተሰርዮላታል:: ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል:: እርስዋንም:- 'ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል' አላት:: ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው:- 'ኃጢአትን እንኩዋ የሚያስተሰርይ ይህ ማነው' ይሉ ጀመር:: ሴቲቱንም:- 'እምነትሽ አድኖሻል: በሰላም ሒጂ' አላት:: +"

+ (ሉቃ. 7:46)

< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >.

@ortodoxtewahedo
+ሁለቱ መምህራን+

በመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ

አንደኛው መምህር የዓለም መድኀኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው
ሁለተኛው መምህር ከአንደኛው መምህር ለመማር የመጣው ኒቆዲሞስ ነው

ኒቆዲሞስ ብሉይ ኪዳንን ለአይሁድ የሚስተምር
አይሁድን በሶስት ነገር የሚመራ ነበር
በእውቀት
በገንዘብ
በሥልጣን
በእውቀት መምህራቸው ነበር
በገንዘብ ከአይሁድ የተሻለ ሀብት ነበረው
በሥልጣን አለቃቸው ሁኖ ተሹሞ ነበር

ኒቆዲሞስ የአይሁድ መምህር ሁኖ በሚያስተምርት ወቅት የመምህራን መምህር የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን ሊያስተም በምድር ላይ ተገለጠ
ያን ጊዜ ኒቆዲሞስ ሊማር ወደ ጌታችን በሌሊት ሄደ

ኒቆዲሞስ በሌሊት መማር የፈለገው ስለ አምስት ነገሮች ነው
1 አይሁድን ፈርቶ
በቀን ልማር ስሄድ አይሁድ ቢያዩኝ ከሥልጣኔ ይሽሩኛል ሀብቴን ይቀሙኛል ብሎ ፈርቶ ነው
በኢየሱስ ያመነ ከምኩራብ ይሰደድ የሚል ሕግ አይሁድ አውጥተው ነበርና

2 ውዳሴ ከንቱ ፈልጎ
መምህር ነኝ ይላል ለምን ሊማር ይሄዳል ብለው እንዳይነቅፉት ተደብቆ በሌሊት ሂዷል

3 በኦሪት ህግ ውስጥ እንዳለ ለመግለጽ
ኦሪት ሌሊት ወንጌል መዓልት ትባላለች
በኦሪት ሁሉም ሰው ቢሞት ወደ ጨለማዋ ሲኦል ይወርድ ስለ ነበር ኦሪት ጨለማ ትባላለች
ወንጌል የነፍስ ብርሃን ናትና መዓልት ትባላለች

4 ምስጢሩን በደንብ ለመረዳት
የቀን ልቡና ባካና ነው ዓይን በቀን ወጭ ወራጁን ሀላፊ አግዳሚውን ሲአይ
ጆሮ የተለያዩ ድንምጾችን ሲሰማ ልብ ይባክናል
በሌሊት ግን ሁሉ ጸጥ ያለ የሚሰማ ድምጽ የሌለበት የሚንቀሳቀስ የማይታይበት ስለሆነ የሌሊት ልቡና ሀሳቡ የተሰበስበ ነው ስለዚህ ጌታችን የሚነግረውን ምሥጢር ሁሉ ለመረዳት ከቀኑ ይልቅ ሌሊቱን መርጦ ሂዷል

5 የዕረፍት ጊዜውን መርጦ
ቀን አይሁድን ሲያስተምር ሲመክር የተጣላ ሲያስታርቅ የተበደለ ሲያስክስ የተቀማ ሲያስመልስ ወንበር ዘርግቶ ሲፈርድ ይውል ነበር
ሌሊት ግን ሁሉም ወደ የቤቱ ሲሄድ ኒቆዲሞስ ደክሞኛል ልርፍ ሳይል ከስራ እንደዋለ እንቅልፉን ትቶ ለመማር ወደ ጌታችን ሂዷል

ጌታችንም ምሥጢረ ሥላሴን ለአብርሃም በሶስት ሰዎች አምሳል ወደ ቤቱ ሂዶ እንደገለጠ
ምሥጢረ ሥጋዌን ለቶማስ በዝግ ቤት ገብቶ ጎኔን ዳሰኝ ብሎ እንደገለጠ
ምሥጢረ ቁርባንን ለሐዋርያት በዕለተ ሐሙስ በኀብስትና በወይን ነገ የሚቆረሰው ሥጋዬ የሚፈሰው ደሜ ይህ ነው ብሎ እንደገለጠ
ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታንን ለማርታና ለማርያ ወንድማቸው ዓልአዛርን ከመቃብር አስነስቶ ለኢያኤሮስ ልጁን ከሞት አስነስቶ እንዳስተማራቸው

ለኒቆዲሞስም ምሥጢረ ጥምቀትን ገልጦ አስተምሮታል
ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም ብሎ ስለ ጥምቀት ሲያስተምረው
መወለድን እንጂ መወለጃውን ከምን እንደሚወለድ አልገለፀለትም ነበርና ኒቆዲሞስ ትምህርቱ ሲከብደው ሰው ካረጀ በኋላ ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅጸን ገብቶ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ብሎ ጠየቀ
ጌታችንም ከውሃና ከመንፈስ ካለተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም
ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋል ስላልኩህ አታድንቅ ነፋስ ወደ ወደደው ይነፍሳል ድምጹን ትሰማለህ ነግር ግን ከየት እንደመጣ ወደየትም እንደሚሄድ አይታወቅም ብሎ ረቂቁን ልደት ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ እንደሆነ በረቂቁ ነፋስ መስሎ አስተማረው

ዳግም ልደት ረቂቅ ነውና በረቀቀው ነፋስ መስሎታል
ረቂቃን ፍጥረታት ሶስት ናቸው
መላእክት
ነፍሳት
ነፋሳት እነዚህ ሶስቱ ረቂቃን ፍጥረታት ናቸው
ከነዚህ አንዱ ነፋስን ጠቅሶ አስተምሮታል በእርግጥ የነፋስ ድምጽ አለው ወይ?
የሚል ካለ የነፋስ ድምጹ ባህር ሲገስጽ ማእበል ሞገድ ሲያስነሳ ዛፍ ሲያንቀሳቅስ ድምጹ ይሰማል
ኒቆዲሞስ ግን መልሶ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ?አለዉ

ጌታችንም አንተ የእስራኤል መምህራቸው ነህ ይሄን እንዴት አታውቅም ብሎ ገሰጸው
መምህር ብሎ መምህርነቱን ነገረው
አታውቅም ብሎ አላዋቂነቱ ገለጸበት
የምናውቀውን እንመሰግራለን ያየነውን እንናገራለን ነገር ግን ምስክርነታችን አትቀበሉንም
በምድር ያለውን ብነግራቸው ካላመናችው በሰማይ ያለውን ብነግራችው እንዴት ታምናላችው? ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም እርሱ የሰው ልጅ በሰማይ ይኖራል አለው ከዚህ በሇላ ኒቆዲሞስ አምኗል ሰማያዊ አምላክ መሆኑንም ተረድቷል

ኒቆዲሞስም ተደብቆ በሌሊት ሰው ሳያየው ምስጢረ ጥምቀትን ተምሮ ብቻ አልቀረም በአደባባይ በመጨረሻዋ ሰዓት ሃይማኖቱን ገልጿል
ያስተምራቸው ይመራቸው የነበሩት አይሁድ የኒቆዲሞስ መምህር የሆነውን ክርስቶስን በቅናት ሰቅለው ሲገድሉት የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉ ሸሽተው የሚቀብረው ባጣ ጊዜ ኒቆዲሞስ በአደባብ ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር የክርስቶስ ተከታይ መሆኑን አሳይቷል
ያኔ በመከራ ሰዓት ሁሉ ሲሸሽ ኒቆዲሞስና ዮሴፍ ተገኝተዋል

መልኩን ለማየት ይከተሉት የነበሩት ሁሉ ሰውነቱ በደም ሲታለል ደምግባቱ ሲጠፋ ከፊቱ ባልተገኙበት ጊዜ

ኀብስት አበርክተው የሚያበሉ እጆቹ ሲቸነከረው ብንራብ አበርክቶ ያበላናል ብለው የሚከተሉት ሁሉ በጠፉበት ጊዜ

ብንሞት ያነሳናል ብንታመም ይፈውሰናል ብለው ሲከተሉት የነበሩት ሁሉ እሱ ታሞ ሲሞት በሸሹበት ጊዜ

የሚያደርገውን ታምራት ለማየት በመደነቅ የሚከተሉት ሁሉ ከፊቱ ባልተገኙበት ጊዜ

ከዋለበት እየዋሉ ካደረበት እያደሩ ወንጌልን ሲማሩ የነበሩት ሁሉ ከእመቤታችንና ከዮሐንስ በቀር ፈርተው ሸሽተው ከመስቀል አውርዶ የሚቀብረው በጠፋበት ጊዜ

ስላሳ ስምንት ዓመት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁረኛ ተይዞ በቃል ፈውሶ አልጋህን ተሸክመህ ሂድ ያለውማ ይባስ ብሎ ባአደባባይ አንተ ነህ ያዳንከኝ ብሎ በጥፊ በመታው ጊዜ

ሁሉ ፈርቶ የሚቀብረው አጥቶ ከሞተ በሇላ መስቀል ላይ ሁለት ሰዓት እንደተሰቀለ ሲቆይ

ከተወለደበት ጀምሮ ዕውር የነበረው ዓይኑን ያበራለት የት ገብቶ ይሆን?

ሰባት አጋንንት ያወጣላት መግደላዊት ማርያም ከመስቀል አውርዳ ለምን አልቀበረችውም? ከዚያ ሁሉ ስቃይ የፈወሷት ከአጋንንት እስራት ነጻ ያወጣት የሚቀብረው ሲያጣ

12 ዓመት ሙሉ ደም ይፈሳት የነበረቸው ሴት ሰው ሲንቃት ሲጸየፋት ከሰው እኩል ያደረጋት መስቀል ላይ ሲውል የት ሂዳ ይሆን?

በደንጋይ ተቀጥቅጣ ትሙት ብለው ተከሳ ሲያመጧት በሰላም ሂጂ ብሎ ያሰናበታት ከሞት ያዳናት መስቀል ላይ ተሰቅሎ የሚቀብረው ሲያጣ ሆዷ እንዴት ቻለ?

ከሞት ያስነሰው ዓልአዛር የት ገባ ?
ሞት ፈርቶ ይሆን ከመስቀል አውርዶ ያልቀበረው?

የሚገርመው እሱ ተሰቅሎ በመሞቱ የተነሱ ከአምስት መቶ በላይ ሙታን ነበሩ እነሱ እንኳን ከሞት በመነሳታቸው ተደሰቱ እንጂ ከመስቀል አውርደው አልቀበሩት

ያን ጊዜ ነበረ ሰው ባጣበት ጊዜ የሚቀብረው ባጣ ጊዜ
በድብቅ በሌሊት ይማር የነበርው ኒቆዲሞስ ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋራ የመጣው
እሱን ሰቅለው የገደሉ ይገሉናል ሳይሉ ከመስቀል አውርደው አቅፈው እያለቀሱ ስመው በበፍታ ሲገንዙት( ወአንበስበሰ አዕይንቲሁ እግዚእ ኢየሱስ )ጊታችን አምላካችን በባህርየ መለኮቱ ዓይኖቹን ግልጽልጽ አድርጎ እንደሩቅ ብእሲ ዝም ብላችው አትገንዙኝ
ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኀያል ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት እያላችው ገንዙኝ ብሎ ኪዳኑን አስተምሯቸው ኪዳን እያደረሱ ገንዘው አክብረው ማንም ባልተቀበረበት በአዲስ መቃብር መለኮት ያልተለየው ነፍስ የተለየው ቅዱስ ሥጋውን ሽቱ ቀብተው ሲቀብሩት (ኦ ዮሴፍ ወኒቆዲሞስ በከመ አክበርክሙኒ ወሰአምክሙኒ አነሂ አከብረክሙ በሰማያት ወአነብረክሙ ዲበ ዕንቆ ሰንፔር ሰማያዊ)ዮሴፍ ኒቆዲሞስ ሆይ እንዳከበራችውኝ እንደሳማችሁኝ እኔም በሰማያት አከብራችዋለው በሰማያዊ እንቆ ሰንፔር ላይ አስቀምጣችዋለው ብሎ ተስፋቸውን ንግሯቸዋል

የቅዱስ ዮሴፍና የቅዱስ ኒቆዲሞስ በረከት በሁላችን ላይ ይደርብን

መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ

@ortodoxtewahedo
"ንጹሕ ምንጭ ኢትዮጵያ" የተሰኘው ዐውደ ርእይ በቅዱስ ፓትርያርኩ ጉብኝትና ቡራኬ ተጠናቀቀ !

በሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት አዘጋጅነት የተሰናደው "ንጹሕ ምንጭ ኢትዮጵያ" የተሰኘው ልዩ ታሪካዊ ዐውደ ርእይ ከሚያዝያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 9 ቀናት ለዕይታ ቀርቦ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ ጉብኝትና ቡራኬ በትናንትናው ዕለት ሚያዝያ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተጠናቋል።

ዐውደ ርእዩ የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊና ትውልዳዊ ሀብቶችን በትንናትናዊ ውበታቸው በአሁናዊ ቅኝት የቀረበበት ፣ ትውልዱን የሚመጥን ሥራዎች የታዩበት ነው ተብሏል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ከቅዱስነታቸው ጋር ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዓን አባቶች ፣ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ኦርቶዶክሳውያን ተገኝተዋል።

@መረጃው የተዋሕዶ ሚዲያ ነው

@ortodoxtewahedo
Forwarded from ✟☨ ማኅቶት ፕሮሞሽን ☨✟
ምን አይነት መዝሙሮችን ይፈልጋሉ?👇👇👇
2024/04/23 05:53:17
Back to Top
HTML Embed Code:


Fatal error: Uncaught Error: Call to undefined function pop() in /var/www/tgoop/chat.php:243 Stack trace: #0 /var/www/tgoop/route.php(43): include_once() #1 {main} thrown in /var/www/tgoop/chat.php on line 243