tgoop.com/behlateabew/7363
Last Update:
ክርስቶስ ተነሥቷል(Christ Risen) በሚለው ቃል ውስጥ ያለው መንፈሳዊ ኀይል።
በአባ ዮሐንስ ገባሬ መንክራት (St. Jonh Maximivotch) የተደረገው ተአምር።
አባ ዮሐንስ ገባሬ መንክራት በአንድ ወቅት የብርሃን ሳምንት ተብሎ በሚታወቅበት ሳምንት አንድ የታመመ ኦርቶዶክዊ ምዕመንን ለመጠየቅ ጉዞውን ወደ አንድ የአይሁዳውያን ሆስፒታል ያደርጋሉ።
አባ ዮሐንስ በሆስፒታሉ በአንደኛው ዋርድ ፊትለፊት ሲያልፍ ድንገት ቆመና በመጋረጃ በተሸፈነው ክፍል ውስጥ አንዲት አይሁዳዊት አሮጊት ሕይወቷ አልፏል በመባሉ ሸፋፍነዋት አልጋ ላይ እንዳስተኟት ይረዳል።
አባ ዮሐንስ ገባሬ መንክራት ድንገት ከተጋረደው ክፍል ፊትለፊት ቆመና ቅዱስ መስቀሉ አውጥቶ ድምጹ ከፍ አድርጎ ጮኸና "ክርስቶስ ተነሥቷል" እያለ በመስቀል ምልክት እያማተበ ተናገረ፣ ድንገት ይኸንን በሚያደርግበት ወቅት ሞተች የተባለችዋ እናት አእምሮዋ ተመለሰላትና ቃል አውጥታ ውሃ ስጡኝ ብላ ጠየቀች።
አባ ዮሐንስም አንዷን ነርስ ጠራት እንዲህ አላት ታማሚዋ ውሃ እየፈለገች ነው ብሎ ሲነግራት ይኸንን የሰሙ የሆስፒታሉ ሠራተኞችም አስቀድማ አርፋለች ተብላ የነበረችው ታማሚዋ ባሳየችው አስገራሚ ለውጥ በጣም ተደነቁ ከዚያ በኋላ ታማሚዋም በተደረገላት አስደናቂ ተአምር ተሽሏት አገግማ ከሆስፒታሉ ወጥታ ወደ ቤቷ ሔደች።
አባ ዮሐንስም በክርስቶስ የትንሣኤው ኃይል በማያምኑት መካከል አስደናቂውን ተአምር አደረጉ።
አቤቱ ሆይ የትንሣኤህ ኃይል ይገለጥ ሰይጣን ከነ ሠራዊቱ ይሸነፍ፣ ሞትም ከነ መውጊያው ይወገድ፣ ሲኦልም ከነ ድል መንሣቷ ትሻር፣ ኃጢአት እና አለማመን ከእኛ ይራ፣ ሕይወታችን የተቀደሰች ትሁን ዙሪያችን በትንሣኤው ኃይል በትንሣኤው ብርሃን የታጠረ ይሁን።
ክርስቶስ ተነሥቷል
በእውነት እርሱ ተነሥቷል።
BY ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
Share with your friend now:
tgoop.com/behlateabew/7363