BEHLATEABEW Telegram 7362
ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
Photo
[•• አምስቱ ትንሣኤዎች••]
      
‹‹...በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው ሁለተኛው ሞት በእርሱ ላይ ሥልጣን የለውም፡፡›› ራእ ፳ ፥ ፮

ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት «ትንሣኤን» በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲያመሠጥሩት በአምስት ዓይነት ትርጉም ያስቀምጡታል፡፡

ይኸውም ትንሣኤ ኅሊና፣ ትንሣኤ ልቡና፣ ትንሣኤ ሙታን፣ ትንሣኤ ክርስቶስና ትንሣኤ ዘጉባኤ በሚል በአምስት መንገድ ይከፈላል።

፩ኛ. ትንሣኤ ኅሊና ነው
ይህ ትንሣኤ ኅሊና ተዘክሮተ እግዚአብሔር (እግዚአብሔርን ማሰብ) ማለት ነው። ሙሴ በኦሪቱ ‹‹እመኒ እንዘ ተሐውር ወእመኒ እንዘ ትትነሣእ ኢትርሣእ ተዘክሮተ እግዚአብሔር፡፡ ስትሄድም ስትነሣም እግዚአብሔርን ማሰብ አትርሣ›› ብሎ ሊቀ ነቢያት ሙሴ እንደተናገረው።

፪ኛ. ትንሣኤ ልቡና ነው፤
ትንሣኤ ልቡና ደግሞ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማትና በንስሐ እየታደሱ በሕይወት መኖር ማለት ነው:: ይኸውም ሰው ሁለት ጊዜ ይሞታል፤ ሁለት ጊዜ ይነሣል፤

የሰው ልጅ የመጀመሪያው ሞቱ ኀጢአት መሥራቱ ከእግዚአብሔር መለየቱ ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሥጋ ፍትወት በምድራዊ ቅንጦት የሚቀማጠሉትን ሲናገር ‹‹ቅምጥሊቱ ግን በሕይወቷ ሳለ የሞተች ናት›› ፩ኛ ጢሞ ፭ ÷፲ ፯ ሲል በኀጢአት መኖር ትልቁ ሞት እንደኾነ ነግሮናል፣

ሁለተኛው በሥጋ መሞቱ ነው:: ስለዚህ ሰው ሁለት ጊዜ እንደሚሞት ሁለት ጊዜ ይነሣል፤

የሰው ልጅ የመጀመሪያ ትንሣኤው እንዴትና ምን እንደሆነ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ እንዲህ ሲል ነግሮናል፤ ‹‹ይህ የፊተኛው ትንሣኤ ነው፤ በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው
ሁለተኛው ሞት በእርሱ ላይ ሥልጣን የለውም፡፡›› ራእ ፳ ፥ ፮  በማለት ንስሐ ገብቶ ከእግዚአብሔር ታርቆ ትንሣኤ ልቡናን ገንዘብ ያደረገ ሰው ሞተ ሥጋንና ሞተ ነፍስ ድል ነሥቶ እንደሚኖር ነግሮናል፡፡ 

ለትንሣኤ ልቡና ትልቅ ምክር የሚሆነን በሉቃስ ወንጌል የተመዘገበው ታሪክ ነው፤  ‹‹ይህ ልጄ ሞቶ ነበረና ደግሞም ሕያው ሆኗል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቷል›› በማለት በኀጢአት መኖር እንደ መሞት ከኀጢአት መመለስ እንደ ትንሣኤ መቆጠሩን አስረድቶናል። ሉቃ ፲፭ ፥ ፳፬ ማንኛውም ሰው ከቤተ ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ሕይወት ከወጣ እንደ ሞተ ነው የሚቆጠረው፡፡

፫ኛ. ትንሣኤ ሙታን ነው
ይህ ደግሞ ለጊዜው የሙታን በሥጋ (በተአምራት) መነሣት ሲሆን፤ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይከተለዋል:: ይኸውም በብሉይ ኪዳን ነቢዩ ኤልያስ አንድ ሙት፣ ነቢዩ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነሥተዋል፤ በሐዲስ ኪዳን ጌታችን የዐራት ቀን ሬሳ አልአዛርን፣ የዕለት ሬሳ ወልደ መበለትን፣ ወለተ ኢያኤሮስን ከሞት አስነሥቷል፤ ይህ ‹‹ትንሣኤ ሙታን›› ይባላል፡፡

፬ኛ. ትንሣኤ ክርስቶስ ነው
ትንሣኤ ክርስቶስ እንደሚታወቀው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዛ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣቱን የሚገልጥ ነው:: ይህ ትንሣኤ የትንሣኤው ሁሉ በኵር ተብሎ ይጠራል᎓᎓ ትንሣኤው ከፍጡራን ትንሣኤ የተለየና ብቸኛ ነው:: 

፭ኛ. ትንሣኤ ዘጉባኤ ነው
ትንሣኤ ዘጉባኤ ከዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ዅሉ እንደየሥራው ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው የዘለዓለም ትንሣኤ ነው።

በሕብረት፣ በነገድ፣ በጉባኤ ለዓለም ሕዝብ ሁሉ የሚደረግ ትንሣኤ በመሆኑ ትንሣኤ ዘጉባኤ ተብሏል። ጌታ በወንጌሉ ስለትነሣኤ ዘጉባኤ ሲናገር «በመቃብር ያሉት ሁሉ ድምፁን
የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል፤ መልካምም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉና በዚህ አታድንቁ።» ዮሐ ፭ ፥ ፳፱ ሲል በትንሣኤ ዘጉባኤ ከሚደረጉ ተአምራት አንጻር ዛሬ የሚደረጉ ተአምራት ምንም እንዳልሆኑ አስተምሯል። ትንሣኤ ክርስቶስ ለትንሣኤ ሙታን ምስክር ለትንሣኤ ዘጉባኤ በኵር  ነው
   ©መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል



tgoop.com/behlateabew/7362
Create:
Last Update:

[•• አምስቱ ትንሣኤዎች••]
      
‹‹...በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው ሁለተኛው ሞት በእርሱ ላይ ሥልጣን የለውም፡፡›› ራእ ፳ ፥ ፮

ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት «ትንሣኤን» በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲያመሠጥሩት በአምስት ዓይነት ትርጉም ያስቀምጡታል፡፡

ይኸውም ትንሣኤ ኅሊና፣ ትንሣኤ ልቡና፣ ትንሣኤ ሙታን፣ ትንሣኤ ክርስቶስና ትንሣኤ ዘጉባኤ በሚል በአምስት መንገድ ይከፈላል።

፩ኛ. ትንሣኤ ኅሊና ነው
ይህ ትንሣኤ ኅሊና ተዘክሮተ እግዚአብሔር (እግዚአብሔርን ማሰብ) ማለት ነው። ሙሴ በኦሪቱ ‹‹እመኒ እንዘ ተሐውር ወእመኒ እንዘ ትትነሣእ ኢትርሣእ ተዘክሮተ እግዚአብሔር፡፡ ስትሄድም ስትነሣም እግዚአብሔርን ማሰብ አትርሣ›› ብሎ ሊቀ ነቢያት ሙሴ እንደተናገረው።

፪ኛ. ትንሣኤ ልቡና ነው፤
ትንሣኤ ልቡና ደግሞ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማትና በንስሐ እየታደሱ በሕይወት መኖር ማለት ነው:: ይኸውም ሰው ሁለት ጊዜ ይሞታል፤ ሁለት ጊዜ ይነሣል፤

የሰው ልጅ የመጀመሪያው ሞቱ ኀጢአት መሥራቱ ከእግዚአብሔር መለየቱ ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሥጋ ፍትወት በምድራዊ ቅንጦት የሚቀማጠሉትን ሲናገር ‹‹ቅምጥሊቱ ግን በሕይወቷ ሳለ የሞተች ናት›› ፩ኛ ጢሞ ፭ ÷፲ ፯ ሲል በኀጢአት መኖር ትልቁ ሞት እንደኾነ ነግሮናል፣

ሁለተኛው በሥጋ መሞቱ ነው:: ስለዚህ ሰው ሁለት ጊዜ እንደሚሞት ሁለት ጊዜ ይነሣል፤

የሰው ልጅ የመጀመሪያ ትንሣኤው እንዴትና ምን እንደሆነ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ እንዲህ ሲል ነግሮናል፤ ‹‹ይህ የፊተኛው ትንሣኤ ነው፤ በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው
ሁለተኛው ሞት በእርሱ ላይ ሥልጣን የለውም፡፡›› ራእ ፳ ፥ ፮  በማለት ንስሐ ገብቶ ከእግዚአብሔር ታርቆ ትንሣኤ ልቡናን ገንዘብ ያደረገ ሰው ሞተ ሥጋንና ሞተ ነፍስ ድል ነሥቶ እንደሚኖር ነግሮናል፡፡ 

ለትንሣኤ ልቡና ትልቅ ምክር የሚሆነን በሉቃስ ወንጌል የተመዘገበው ታሪክ ነው፤  ‹‹ይህ ልጄ ሞቶ ነበረና ደግሞም ሕያው ሆኗል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቷል›› በማለት በኀጢአት መኖር እንደ መሞት ከኀጢአት መመለስ እንደ ትንሣኤ መቆጠሩን አስረድቶናል። ሉቃ ፲፭ ፥ ፳፬ ማንኛውም ሰው ከቤተ ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ሕይወት ከወጣ እንደ ሞተ ነው የሚቆጠረው፡፡

፫ኛ. ትንሣኤ ሙታን ነው
ይህ ደግሞ ለጊዜው የሙታን በሥጋ (በተአምራት) መነሣት ሲሆን፤ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይከተለዋል:: ይኸውም በብሉይ ኪዳን ነቢዩ ኤልያስ አንድ ሙት፣ ነቢዩ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነሥተዋል፤ በሐዲስ ኪዳን ጌታችን የዐራት ቀን ሬሳ አልአዛርን፣ የዕለት ሬሳ ወልደ መበለትን፣ ወለተ ኢያኤሮስን ከሞት አስነሥቷል፤ ይህ ‹‹ትንሣኤ ሙታን›› ይባላል፡፡

፬ኛ. ትንሣኤ ክርስቶስ ነው
ትንሣኤ ክርስቶስ እንደሚታወቀው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዛ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣቱን የሚገልጥ ነው:: ይህ ትንሣኤ የትንሣኤው ሁሉ በኵር ተብሎ ይጠራል᎓᎓ ትንሣኤው ከፍጡራን ትንሣኤ የተለየና ብቸኛ ነው:: 

፭ኛ. ትንሣኤ ዘጉባኤ ነው
ትንሣኤ ዘጉባኤ ከዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ዅሉ እንደየሥራው ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው የዘለዓለም ትንሣኤ ነው።

በሕብረት፣ በነገድ፣ በጉባኤ ለዓለም ሕዝብ ሁሉ የሚደረግ ትንሣኤ በመሆኑ ትንሣኤ ዘጉባኤ ተብሏል። ጌታ በወንጌሉ ስለትነሣኤ ዘጉባኤ ሲናገር «በመቃብር ያሉት ሁሉ ድምፁን
የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል፤ መልካምም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይወጣሉና በዚህ አታድንቁ።» ዮሐ ፭ ፥ ፳፱ ሲል በትንሣኤ ዘጉባኤ ከሚደረጉ ተአምራት አንጻር ዛሬ የሚደረጉ ተአምራት ምንም እንዳልሆኑ አስተምሯል። ትንሣኤ ክርስቶስ ለትንሣኤ ሙታን ምስክር ለትንሣኤ ዘጉባኤ በኵር  ነው
   ©መ/ር ሚኪያስ ዳንኤል

BY ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ




Share with your friend now:
tgoop.com/behlateabew/7362

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Each account can create up to 10 public channels 5Telegram Channel avatar size/dimensions The visual aspect of channels is very critical. In fact, design is the first thing that a potential subscriber pays attention to, even though unconsciously. Polls The best encrypted messaging apps
from us


Telegram ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
FROM American