ZEPHILOSOPHY Telegram 1109
የፈላስፋ ህይወት በምን ይገለፃል?

የአማርኛው መዝገበ ቃላት “ፈለሰፈ” እንዲሁም “ፍልሰፋ” የሚሉትን ቃላት ልዩ ልዩ ብልሃትንና ጥበብን ከአእምሮ እያመነጨ አስገኘ፣ ያልነበረውን የጥበብ ሥራ ፈጥሮ አገኘ፣ ያልተገለጠውን (ያልታወቀውን) እንዲታወቅ አደረገ፣ ጥበብን(እውቀትን) ወደደ በማለት ትርጉም ሰጧቸዋል፡፡

የሚከተሉት ባህሪዎች ደግሞ ፈላስፋዎች የሚኖሩትን ህይወት ሊያመለክቱ የሚችሉ ዋና ዋና መገለጫዎች ናቸው።

1.ፈላስፋዎች የእውቀት ሱሰኞች ናቸው፤ አዲስን ነገር ለማወቅ የተራቡ ናቸው:: ነጋም መሸም ያው ነው - እውቀትን መፈለግ የጊዜ ገደብ የለውም፡፡ ለፈላስፋ ጊዜ፣ ቦታ፣ ሁኔታ እውቀት ማስገኘት አለባቸው፡፡ ለፈላስፋ እውቀት በልተው የማይጠግቡት የሚጣፍጥ ምግብ ነው፣ ጠጥተው የማይረኩት ጣፋጭ ወይን ጠጅ ነው፡፡ ሰዎች፣ ተፈጥሮ. ሌላም ሌላም... እግዚአብሔርም ይሁን ለፈላስፋ ሁሉም እውቀት ናቸው፡፡ ተፈጥሮ የያዘችው የሚያስደምም ህብርና ሥርዓት ምስጢር ማወቅ ጉጉታቸው መጠን የለውም፡፡ የሰውን ግላዊ፣ ማኅበራዊና ተፈጥሯዊ ማንነቱን፣ ተስፋውንና ጭንቀቱን ለማወቅ ሥሥት ያደረባቸው ናቸው፡፡ ፈላስፋ ለማንም አይገዛም ቢባል የተጋነነ አይሆንም፣ ግለ - ታሪካቸው ይመስክራልና፡፡ ነገር ግን ለማንም የማይረታው ልቦናቸው ለአንድ ነገር ተሸናፊና ባሪያ ነው - ለእውቀት!

2.ፈላስፋዎች ሌላው የሚታወቁበት ነገር ለሰው ልጅ እጅግ አሳቢዎች መሆናቸው ነው:: ከማንም በላይ ህብረተሰብ የሚሠቃይባቸው ችግሮች ይሰማቸዋል፡፡ ህብረተሰብን ለከፋ ህመም የዳረጉ ቁስሎች እነርሱንም ይጠዘጥዛቸዋል፡፡ ህብረተሰብ ገመናውን በይስሙላ ከበሮችና ወዳሴዎች መሸፈኑ ያንገበግባቸዋል፡፡ ለፈላስፋ የሰው ልጅ በእውነተኛ ማንነቱ መኖር እስካልቻለ ድረስ ህሊናቸው ረፍት አያገኝም፡፡ ሰው ተስፋ ያጣበት ነገር ፈላስፋን አንገቱን ያስደፋዋል፤ ከትካዜውም አይመለስም፡፡ ፈላስፋ ሰው ከሀዘኑ፣ ከጭንቀቱ፣ ከችግሩ የሚያወጣ እውቀት እስካላገኘ ድረስ የሚበላውን፣ የሚለብሰውን፣ የሚኖርበትን፣ ወዘተ እስኪረሳ ድረስ በሀሳብ ይናወዛል፡፡

የሰው ልጅ ተስፋ ማጣት ጩኸት በቀንም በሌሊትም በጆሮው ያቃጭልበታል፣ «ምን ልሁን? ተስፋ ቆረጥሁ፣ ታደገኝ እያለ የሚጠራው ይመስለዋል፤ ነፍሱ በህዝቡ ሰቆቃ መሃል ሁና ትዋትታለች፡፡ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ሥርዓቶች በሰው ልጅ ላይ የሚያደርሱት በደል መታገስ የሚችልበት ጉልበት የለውም - ነፍሱ ከተበደሉት ጋር ናት - ሲያለቅሱ ታለቅሳለች፣ ሲታራዙ፣ ሲራቡ፣ ሲሰደዱ አብራቸው ትሰደዳለች፡፡

3.ፈላስፋነት አማጺነት ነው፡፡ፈላስፋ መጥፎ ሥርዓት ላይ አማጺ ነው፡፡ ተፈትኖና ተመርምሮ ባልተረጋገጠ አስተሳሰብና እምነት ጋር አብሮና ተመሣስሎ ላለመኖር እንቢተኛ ነው፡፡ በአጓጉል ማኀበራዊ ሥርዓቶች ተጨፍልቆ ላለመኖርና ራሱን ነፃ ለማውጣት ይጥራል፣ በራሱ ህሊና ለመምራትና የራሱን ማንነት ይዞ ለመገኘት ህሊናው በማይቀበላቸው እምነቶችና አስተሳሰቦች ላይ ያምፃል፡፡ ህሊናውንና ማንነቱን አሳልፎ ሳይሰጥ በተረዳውና በአመነው ነገር ላይ ብቻ ህይወቱን ለመምራት የስብዕና ጥንካሬ ያለው ፈላስፋ ነው፡፡

4.ፈላስፋ ራሱን የሚቀድስ ሰው ነው፡፡ ግለሰቦችና ማኅበራዊ ሥርዓቶች ከሚያደርሱት በደል ራሱን በእውቀት እያበቃ ተካፋይ ላለመሆን የእውነት መንገድን እየፈለገ የሚኖርና ከህብረተሰብ  ‌እድፍ ራሱን የሚያነፃ ፈላስፋ ነው፡፡ ስሜታዊነትን፣ አድሏዊነትንና ወገንተኛነትን ከህይወቱ በማስወገድ ስብዕናውን የሚቀድስና በእውቀት የቅድስና ህይወት መኖር የሚችል ፈላስፋ ነው፡፡ፈላስፋ ምድራዊ ለሆነው ማንነት (ለሥጋዊ ደስታ፤ ለክብር፣ ለዝናና ለሐብት) ብሎ ህሊናውን የማይሸጥ እና ላመነበት ነገር እስከ ሞት ፅዋ ድረስ የሚጋፈጥ ነው።

ረ/ፕሮፌሰር ዋለልኝ እምሩ
@zephilosophy



tgoop.com/Zephilosophy/1109
Create:
Last Update:

የፈላስፋ ህይወት በምን ይገለፃል?

የአማርኛው መዝገበ ቃላት “ፈለሰፈ” እንዲሁም “ፍልሰፋ” የሚሉትን ቃላት ልዩ ልዩ ብልሃትንና ጥበብን ከአእምሮ እያመነጨ አስገኘ፣ ያልነበረውን የጥበብ ሥራ ፈጥሮ አገኘ፣ ያልተገለጠውን (ያልታወቀውን) እንዲታወቅ አደረገ፣ ጥበብን(እውቀትን) ወደደ በማለት ትርጉም ሰጧቸዋል፡፡

የሚከተሉት ባህሪዎች ደግሞ ፈላስፋዎች የሚኖሩትን ህይወት ሊያመለክቱ የሚችሉ ዋና ዋና መገለጫዎች ናቸው።

1.ፈላስፋዎች የእውቀት ሱሰኞች ናቸው፤ አዲስን ነገር ለማወቅ የተራቡ ናቸው:: ነጋም መሸም ያው ነው - እውቀትን መፈለግ የጊዜ ገደብ የለውም፡፡ ለፈላስፋ ጊዜ፣ ቦታ፣ ሁኔታ እውቀት ማስገኘት አለባቸው፡፡ ለፈላስፋ እውቀት በልተው የማይጠግቡት የሚጣፍጥ ምግብ ነው፣ ጠጥተው የማይረኩት ጣፋጭ ወይን ጠጅ ነው፡፡ ሰዎች፣ ተፈጥሮ. ሌላም ሌላም... እግዚአብሔርም ይሁን ለፈላስፋ ሁሉም እውቀት ናቸው፡፡ ተፈጥሮ የያዘችው የሚያስደምም ህብርና ሥርዓት ምስጢር ማወቅ ጉጉታቸው መጠን የለውም፡፡ የሰውን ግላዊ፣ ማኅበራዊና ተፈጥሯዊ ማንነቱን፣ ተስፋውንና ጭንቀቱን ለማወቅ ሥሥት ያደረባቸው ናቸው፡፡ ፈላስፋ ለማንም አይገዛም ቢባል የተጋነነ አይሆንም፣ ግለ - ታሪካቸው ይመስክራልና፡፡ ነገር ግን ለማንም የማይረታው ልቦናቸው ለአንድ ነገር ተሸናፊና ባሪያ ነው - ለእውቀት!

2.ፈላስፋዎች ሌላው የሚታወቁበት ነገር ለሰው ልጅ እጅግ አሳቢዎች መሆናቸው ነው:: ከማንም በላይ ህብረተሰብ የሚሠቃይባቸው ችግሮች ይሰማቸዋል፡፡ ህብረተሰብን ለከፋ ህመም የዳረጉ ቁስሎች እነርሱንም ይጠዘጥዛቸዋል፡፡ ህብረተሰብ ገመናውን በይስሙላ ከበሮችና ወዳሴዎች መሸፈኑ ያንገበግባቸዋል፡፡ ለፈላስፋ የሰው ልጅ በእውነተኛ ማንነቱ መኖር እስካልቻለ ድረስ ህሊናቸው ረፍት አያገኝም፡፡ ሰው ተስፋ ያጣበት ነገር ፈላስፋን አንገቱን ያስደፋዋል፤ ከትካዜውም አይመለስም፡፡ ፈላስፋ ሰው ከሀዘኑ፣ ከጭንቀቱ፣ ከችግሩ የሚያወጣ እውቀት እስካላገኘ ድረስ የሚበላውን፣ የሚለብሰውን፣ የሚኖርበትን፣ ወዘተ እስኪረሳ ድረስ በሀሳብ ይናወዛል፡፡

የሰው ልጅ ተስፋ ማጣት ጩኸት በቀንም በሌሊትም በጆሮው ያቃጭልበታል፣ «ምን ልሁን? ተስፋ ቆረጥሁ፣ ታደገኝ እያለ የሚጠራው ይመስለዋል፤ ነፍሱ በህዝቡ ሰቆቃ መሃል ሁና ትዋትታለች፡፡ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ሥርዓቶች በሰው ልጅ ላይ የሚያደርሱት በደል መታገስ የሚችልበት ጉልበት የለውም - ነፍሱ ከተበደሉት ጋር ናት - ሲያለቅሱ ታለቅሳለች፣ ሲታራዙ፣ ሲራቡ፣ ሲሰደዱ አብራቸው ትሰደዳለች፡፡

3.ፈላስፋነት አማጺነት ነው፡፡ፈላስፋ መጥፎ ሥርዓት ላይ አማጺ ነው፡፡ ተፈትኖና ተመርምሮ ባልተረጋገጠ አስተሳሰብና እምነት ጋር አብሮና ተመሣስሎ ላለመኖር እንቢተኛ ነው፡፡ በአጓጉል ማኀበራዊ ሥርዓቶች ተጨፍልቆ ላለመኖርና ራሱን ነፃ ለማውጣት ይጥራል፣ በራሱ ህሊና ለመምራትና የራሱን ማንነት ይዞ ለመገኘት ህሊናው በማይቀበላቸው እምነቶችና አስተሳሰቦች ላይ ያምፃል፡፡ ህሊናውንና ማንነቱን አሳልፎ ሳይሰጥ በተረዳውና በአመነው ነገር ላይ ብቻ ህይወቱን ለመምራት የስብዕና ጥንካሬ ያለው ፈላስፋ ነው፡፡

4.ፈላስፋ ራሱን የሚቀድስ ሰው ነው፡፡ ግለሰቦችና ማኅበራዊ ሥርዓቶች ከሚያደርሱት በደል ራሱን በእውቀት እያበቃ ተካፋይ ላለመሆን የእውነት መንገድን እየፈለገ የሚኖርና ከህብረተሰብ  ‌እድፍ ራሱን የሚያነፃ ፈላስፋ ነው፡፡ ስሜታዊነትን፣ አድሏዊነትንና ወገንተኛነትን ከህይወቱ በማስወገድ ስብዕናውን የሚቀድስና በእውቀት የቅድስና ህይወት መኖር የሚችል ፈላስፋ ነው፡፡ፈላስፋ ምድራዊ ለሆነው ማንነት (ለሥጋዊ ደስታ፤ ለክብር፣ ለዝናና ለሐብት) ብሎ ህሊናውን የማይሸጥ እና ላመነበት ነገር እስከ ሞት ፅዋ ድረስ የሚጋፈጥ ነው።

ረ/ፕሮፌሰር ዋለልኝ እምሩ
@zephilosophy

BY ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy


Share with your friend now:
tgoop.com/Zephilosophy/1109

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

To delete a channel with over 1,000 subscribers, you need to contact user support How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) There have been several contributions to the group with members posting voice notes of screaming, yelling, groaning, and wailing in different rhythms and pitches. Calling out the “degenerate” community or the crypto obsessives that engage in high-risk trading, Co-founder of NFT renting protocol Rentable World emiliano.eth shared this group on his Twitter. He wrote: “hey degen, are you stressed? Just let it out all out. Voice only tg channel for screaming”. Co-founder of NFT renting protocol Rentable World emiliano.eth shared the group Tuesday morning on Twitter, calling out the "degenerate" community, or crypto obsessives that engage in high-risk trading. The Standard Channel
from us


Telegram ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
FROM American