tgoop.com/Zephilosophy/1106
Last Update:
እስልምና እና ተፈጣሪያዊነት
Eslamic creationism thought
የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች እንደሚሉት የሚታየው እና የማይታየውን ኹሉ የፈጠረው አላህ ነው፡፡ በሰማይ ሆነ በምድር ያሉ ፍጡራን በሙሉ መኖር የሚመሰከሩት ዋነኛው ነገርም ህልውናውን ነው፡፡ ፀሐይ ሆነች ጨረቃ እንዲሁም ከዋከብትን የተፈጠሩትም ሆነ የሚታዘዙት ለአላህ ነው፡፡ ፈጣሪ በዓለም ላይ ያሉ ፍጡራንን ተዛማች ጥንድ አድርጎ የፈጠረው ማለትም ሰማይ እና ምድር፣ ሞት እና ሕይወት፣ ደስታ እና ሀዘን፣ የሚንቀሳቀስ እና የማይንቀሳቀስ አድርጎ ያበጀው የምንም እና የማንም ፈጣሪ እሱ እንደሆነ እንድንገነዘብ ዘንድ ነውም ይሉናል የሃይማኖቱ የሥነ መለኮት መምህራን፡፡ የሰማይን ከፍታ፣ የሌሊትን አጨላለም፣ የቀኑን መልክ፣ የምድር መዘርጋት በሙሉ የተደረገው በአላህ ይሁን ቃል ነው፡፡
እንደ እስልምና ሀይማኖት አስተሳሰብ አለም የተፈጠረችው በስድስት ቀን አፈጣጠር ትረካ ቢሆንም ብዙዎቹ የሀይማኖቱ መምህራን እንደሚሉት "ቀን" የሚለው ትርጉም የሰው የጊዜ አቆጣጠርን ("24 ሰዓት") አይገልፅም ይልቅ በአላህ የጊዜ አቆጣጠር ይወሰናል ይህም ማለት አንዱ ቀን ሚሊዮን አመታት ሊሆን ይችላል የሚል አስተምህሮ አለው።
የሰውን አፈጣጠር ከቅዱስ ቅራዓን አንፃር ምን መልክ እንዳለው ሳጠና ከገረመኝ ነገሮች አንዱ የሰዎች መልክ(የቆዳ ቀለም መለያየት) ምክንያት ምን እንደሆነ ያገኝውት ምላሽ ነው፡፡
"መልካችን የተለያየው፣ የቆዳ ቀለማችን አንድ
ያልሆነው አደም የተፈጠረበት አፈር አንድ ዓይነት ባለመሆኑ ነው።"ይላሉ
“አላህ አደምን ከወሰዳቸው የምድር አፈር አይነቶች ኹሉ ፈጠረው፡፡ የአደም ልጆችም በዚህ የምድር አፈር አይነት (መልክ) የተለያዩ ሆነው መጡ፡፡ ከነሱም ውስጥ ቀይ፣ ነጭ፣ ጥቁር፣ በዚህ መሀል የሆነም በመሆን መጡ...” (አቡ ዳዉድ 4695፣ ቲርሚዚይ 2955)
@zephilosophy
BY ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
Share with your friend now:
tgoop.com/Zephilosophy/1106