Notice: file_put_contents(): Write of 18539 bytes failed with errno=28 No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 50

Warning: file_put_contents(): Only 4096 of 22635 bytes written, possibly out of free disk space in /var/www/tgoop/post.php on line 50
ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy@Zephilosophy P.1069
ZEPHILOSOPHY Telegram 1069
ብርሃናዊና ፅልመታዊ
ደራሲ-ስብሃት ገ/እግዚአብሔር

መኖር-ማንበብ - መፃፍ። እዚህ ላይ ገፀባህሪ የሚባለው ፍጡር ይመጣና ራሱን ያስተዋውቃል። ፔሲሚስት Pessimist ነው። በአማርኛ  ምን እንደሚባል ቃሉን እስክንፈልግ ድረስ ተቃራኒው ኦፕቲሚስት Optimist ማንሳት የማይቀር ነው። እንዲህ ይላል። ግማሽ ብርጭቆ ወይን ጠጅ ቢያሳዩዋቸው ኦኘቲሚስት ለመሙላት ግማሽ ጐደለው ሲል አቶ ፔስሚስት ግን ገና ግማሽ ብርጭቆ ይቀራል ይላል።

የዲክ ግሬጐሪ አባት ደግሞ አስቀድሞ ማን እየቀዳ እንደሆነ ማወቅ ያሻል ይላሉ።

ነብሳችን በፔሲሚስትና በኦፕቲሚስትነት መሀከል እንደ ሸማኔ መወርወሪያ ብርሃናዊነትና ዕልመታዊነት ይፈራረቁብናል። እቺ ምድራዊት ህይወታችን ስንኖራት የሲኦልና የገነት ስብጥርጥር ትመስላለች። ራብ ክፉኛ ሲሞረሙረን ጊዜዋ አንገብጋቢት ሲኦል ብትሆንም፤ አግኝተን ስንበላ አግኝተን ስንበላ ደግሞ ምግቡ መጣፈጡ የገነት ያህል ነው። ውሀ ጥም ለረዥም ጊዜ ሲያቃጥለን ጊዜው የሲኦል በመሆኑ ቢከፋንም፤ ውሀ አግኝተን ስንጠጣበት ገነት ሲበዛ መጣፈጥዋን እናውቃለን። ከአቅም ውጭ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ሽንታችን ቢወጥረንና ከዚያም እየባሰበት ሄዶ ፊኛችን ሊፈነዳ እየቃጣ ቆይቶ ቆይቶ በለስ ቢታረቀንና ሽንታችንን ብንሸና ያቺ እፎይታ
የገነት ሌላ ገፅታ ናት።

እንደ መፈላሰፍ ቢያሰኛቸው ፔሲሚስቱ ንጉስ
ሰሎሞንን ይጠቅሳሉ። “ከቆሙት የሞቱት ይሻላሉ፤ ከሞቱት ደግሞ ጭራሹኑ ያልተፈጠሩት ይሻላሉ። ከንቱ ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉ ከንቱ ነው።” ኖረን ኖረን ማብቂያችን ሞት እስከሆነ ድረስ እንዴትስ ብንኖር ምን ልዩነት ያመጣል?

“ፈሳሾች ሁሉ ወደ ባህር ይሄዳሉ፣ ባህሩ ግን አይሞላም። ፈሳሾች ወደሚሄዱበት ስፍራ እንደገና ወደዚያ ይመለሳሉ።ነገር ሁሉ ያደክማል፣ ሰው ይናገረው ዘንድ አይችልም፣ አይን ከማየት አይጠግብም፣ ጆሮም ከመስማት አይሞላም። ለፊተኞቹ ነገሮች መታሰቢያ የላቸውም፣ ለኋለኞቹም ነገሮች ከእነርሱ በኋላ በሚነሱት ሰዎች ዘንድ መታሰቢያ አይገኝላቸውም። ከፀሀይ በታች የተሰራውን ስራ ሁሉ አየሁ፣ እነሆ ሁሉ ከንቱ ነው። ነፋስንም እንደመከተል ነው። ጠማማ ይቀና ዘንድ አይችልም፤ ጐደሎም ይሞላ ዘንድ አይችልም።
...
ጥበብና እብደትን ሞኝነትንም አውቅ ዘንድ ልቤን ሰጠሁ፤ ይህም ደግሞ ነፋስን እንደመከተል እንደሆነ አስተዋልሁ። በጥበብ መብዛት ትካዜ ይበዛልና እውቀትንም የሚጨምር ሀዘንን ይጨምራልና...

... ልጄ የሰራቻትን ስራዬን ሁሉ የደከምሁበትንም ድካሜን ተመለከትሁ፣ እነሆ ሁሉ ከንቱ፣ ነፋስንም እንደ መከተል ነበረ፣ ከፀሀይ በታችም ትርፍ አልነበረም...!!"

ብርሀናማው ኦፕትሚስት የበኩሉን ይቀጥላል። እየለመድነው መሄዳችን መውለድ ምንኛ የሚያስደንቅ ተአምር መሆኑ እየተረሳን ይሄዳል እንጂ ከወንዱና ከሴቷ መተቃቀፍ ህፃኑ መመንጨቱ ማደጉ በጣም የሚገርም ነው። በየእንስሳቱ በየእፅዋቱ ተአምራት መባዛቱ። የህይወትን ችቦ ከትውልድ ወደ ትውልድ እያስተላለፉ ማለፍ።

የአፍላነት እድሜያችን ወደነበረው ወደ ህፃንነታችን እንመለስና እናቴን ከየት መጣሁ ስላት ወልጄህ ነው ትለኛለች። አንቺስ ከየት መጣሽ? እናቴ ወለደችኝ። እሷስ ከየት መጣች?እናቷ ወለደቻት። ማለቂያ የለውም? ሄዋንን እግዚአብሄር ፈጠራት። እሱስ ከየት መጣ? እሱማ ፈጣሪ ነው። እሺ እሱንስ ማን ፈጠረው? እሱማ አልተፈጠረም ፈጣሪ ነው። እሺ ከየት መጣ ኧይ!? ተወኝ እንግዲህ አታድርቀኝ!
በአዛውንትነት እድሜያችንም ከጥያቄ ወደ ጥያቄ እየነጠርን እንሄድ እንሄድና በመጨረሻ ፍጥጥ! መልስ የለም።

በአዳም ሀረግ ብንሄድ ወይም በኢቮሉሽን (በዝግመታዊ ለውጥ) ብንጓዘው የመጨረሻው ጥያቄያችን “ይሄ ሁሉ መዋለድ መፈጣጠር እንዴት ተጀመረ? የጀማሪውስ ጀማሪ ማን ወይም ምንድነው? ምንም ይሁን። ብቻ ሂደቱ ተጀምሯል። በራሳችን ላይ እያየነው ነው። ከአለመኖር ወደ መኖር መጥተናል። ቀጥሎ እንግዲህ በጊዜ ውስጥ ነብሳችን የኖረባትን ስጋችንን እና ያኖረችን ምድራችንን ተሰናብታ ለዘለአለም ወደምንኖርበት ሰማይ ቤት ታርጋለች። ሂደቷን ለመቀጠል። እቺ የመጨረሻዋ ምኞት ናት የሚሉ ቢኖሩ የመፈጠር ወይም የመወለድን ተአምር በገዛ ራሳቸው ሂደት ያዩት መሆኑን የማይገነዘቡ ወይም የረሱ ናቸው። እንጂ ካለመኖር ወደ መኖር (ከአልቦ ወደ ቦ) የነጠረ ተአምር በመሞት ሌላ ተአምር ከመኖር ወደ ዘለአለማዊ ህይወት ሊነጥር ለምን አይችልም? ተስፋ አለ። እምነትም አለ። የዛፍ ፍሬ ያንን የማናውቀው መነሻና መድረሻችንን የሚያውቅ ሀይል በማመንዋ ትረግፋለች። በእምነት ስትጠብቅ ሰንብታ ዝናብ ይመጣላታል። በእምነት ቅጠልዋ ብቅ ትላለች ከፀሀይ ጋር የፈጠራ ስራዋን ትቀጥላለች...

እነዚህ ብርሃናዊና ዕልመታዊ ተቃራኒ ገፀባህሪያት ከውስጣችን ተወስደው በማህበራዊና በአለማዊ ገፅታ ሲታዩ ወደ ሩቅ ምስራቅ ወደ ህንድ ወደ ቻይና አስተሳሰብ ይወስዱናል። ቀንና ሌት፣ ላይና ታች፣ ወንድና ሴት፣ በጋና ክረምት፣ ራብና ጥጋብ፣ እጥረትና ርዝመት፣ርቀትና ቅርበት፣ ደስታና ሀዘን፣ ብርድና ሙቀት...ሁለት ሁለት መሬትና ሰማይ
እነዚህ ሁሉት ሁለቶች መሐልኮ የሚመሳሰል ሶስተኛ አለ። ሶስተኛውን ማወቅ ግን የፈጣሪውን ምስጢር ገልጦ ማየት ስለሚሆን ለኛ ለፍጡራን ክልክል ነው።

ምናልባት እነሱ ሁለት፣ ሁለት እየሆኑ ያሉት እኔ ሶስተኛቸው ወይ እነሱ የፈጠሩኝ ወይ እኔ የፈጠርኳቸው ወይ በየተራ ያኛውም ይኸኛውም። ክልክል ነው!!

@zephilosophy
👍64🔥42



tgoop.com/Zephilosophy/1069
Create:
Last Update:

ብርሃናዊና ፅልመታዊ
ደራሲ-ስብሃት ገ/እግዚአብሔር

መኖር-ማንበብ - መፃፍ። እዚህ ላይ ገፀባህሪ የሚባለው ፍጡር ይመጣና ራሱን ያስተዋውቃል። ፔሲሚስት Pessimist ነው። በአማርኛ  ምን እንደሚባል ቃሉን እስክንፈልግ ድረስ ተቃራኒው ኦፕቲሚስት Optimist ማንሳት የማይቀር ነው። እንዲህ ይላል። ግማሽ ብርጭቆ ወይን ጠጅ ቢያሳዩዋቸው ኦኘቲሚስት ለመሙላት ግማሽ ጐደለው ሲል አቶ ፔስሚስት ግን ገና ግማሽ ብርጭቆ ይቀራል ይላል።

የዲክ ግሬጐሪ አባት ደግሞ አስቀድሞ ማን እየቀዳ እንደሆነ ማወቅ ያሻል ይላሉ።

ነብሳችን በፔሲሚስትና በኦፕቲሚስትነት መሀከል እንደ ሸማኔ መወርወሪያ ብርሃናዊነትና ዕልመታዊነት ይፈራረቁብናል። እቺ ምድራዊት ህይወታችን ስንኖራት የሲኦልና የገነት ስብጥርጥር ትመስላለች። ራብ ክፉኛ ሲሞረሙረን ጊዜዋ አንገብጋቢት ሲኦል ብትሆንም፤ አግኝተን ስንበላ አግኝተን ስንበላ ደግሞ ምግቡ መጣፈጡ የገነት ያህል ነው። ውሀ ጥም ለረዥም ጊዜ ሲያቃጥለን ጊዜው የሲኦል በመሆኑ ቢከፋንም፤ ውሀ አግኝተን ስንጠጣበት ገነት ሲበዛ መጣፈጥዋን እናውቃለን። ከአቅም ውጭ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ሽንታችን ቢወጥረንና ከዚያም እየባሰበት ሄዶ ፊኛችን ሊፈነዳ እየቃጣ ቆይቶ ቆይቶ በለስ ቢታረቀንና ሽንታችንን ብንሸና ያቺ እፎይታ
የገነት ሌላ ገፅታ ናት።

እንደ መፈላሰፍ ቢያሰኛቸው ፔሲሚስቱ ንጉስ
ሰሎሞንን ይጠቅሳሉ። “ከቆሙት የሞቱት ይሻላሉ፤ ከሞቱት ደግሞ ጭራሹኑ ያልተፈጠሩት ይሻላሉ። ከንቱ ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉ ከንቱ ነው።” ኖረን ኖረን ማብቂያችን ሞት እስከሆነ ድረስ እንዴትስ ብንኖር ምን ልዩነት ያመጣል?

“ፈሳሾች ሁሉ ወደ ባህር ይሄዳሉ፣ ባህሩ ግን አይሞላም። ፈሳሾች ወደሚሄዱበት ስፍራ እንደገና ወደዚያ ይመለሳሉ።ነገር ሁሉ ያደክማል፣ ሰው ይናገረው ዘንድ አይችልም፣ አይን ከማየት አይጠግብም፣ ጆሮም ከመስማት አይሞላም። ለፊተኞቹ ነገሮች መታሰቢያ የላቸውም፣ ለኋለኞቹም ነገሮች ከእነርሱ በኋላ በሚነሱት ሰዎች ዘንድ መታሰቢያ አይገኝላቸውም። ከፀሀይ በታች የተሰራውን ስራ ሁሉ አየሁ፣ እነሆ ሁሉ ከንቱ ነው። ነፋስንም እንደመከተል ነው። ጠማማ ይቀና ዘንድ አይችልም፤ ጐደሎም ይሞላ ዘንድ አይችልም።
...
ጥበብና እብደትን ሞኝነትንም አውቅ ዘንድ ልቤን ሰጠሁ፤ ይህም ደግሞ ነፋስን እንደመከተል እንደሆነ አስተዋልሁ። በጥበብ መብዛት ትካዜ ይበዛልና እውቀትንም የሚጨምር ሀዘንን ይጨምራልና...

... ልጄ የሰራቻትን ስራዬን ሁሉ የደከምሁበትንም ድካሜን ተመለከትሁ፣ እነሆ ሁሉ ከንቱ፣ ነፋስንም እንደ መከተል ነበረ፣ ከፀሀይ በታችም ትርፍ አልነበረም...!!"

ብርሀናማው ኦፕትሚስት የበኩሉን ይቀጥላል። እየለመድነው መሄዳችን መውለድ ምንኛ የሚያስደንቅ ተአምር መሆኑ እየተረሳን ይሄዳል እንጂ ከወንዱና ከሴቷ መተቃቀፍ ህፃኑ መመንጨቱ ማደጉ በጣም የሚገርም ነው። በየእንስሳቱ በየእፅዋቱ ተአምራት መባዛቱ። የህይወትን ችቦ ከትውልድ ወደ ትውልድ እያስተላለፉ ማለፍ።

የአፍላነት እድሜያችን ወደነበረው ወደ ህፃንነታችን እንመለስና እናቴን ከየት መጣሁ ስላት ወልጄህ ነው ትለኛለች። አንቺስ ከየት መጣሽ? እናቴ ወለደችኝ። እሷስ ከየት መጣች?እናቷ ወለደቻት። ማለቂያ የለውም? ሄዋንን እግዚአብሄር ፈጠራት። እሱስ ከየት መጣ? እሱማ ፈጣሪ ነው። እሺ እሱንስ ማን ፈጠረው? እሱማ አልተፈጠረም ፈጣሪ ነው። እሺ ከየት መጣ ኧይ!? ተወኝ እንግዲህ አታድርቀኝ!
በአዛውንትነት እድሜያችንም ከጥያቄ ወደ ጥያቄ እየነጠርን እንሄድ እንሄድና በመጨረሻ ፍጥጥ! መልስ የለም።

በአዳም ሀረግ ብንሄድ ወይም በኢቮሉሽን (በዝግመታዊ ለውጥ) ብንጓዘው የመጨረሻው ጥያቄያችን “ይሄ ሁሉ መዋለድ መፈጣጠር እንዴት ተጀመረ? የጀማሪውስ ጀማሪ ማን ወይም ምንድነው? ምንም ይሁን። ብቻ ሂደቱ ተጀምሯል። በራሳችን ላይ እያየነው ነው። ከአለመኖር ወደ መኖር መጥተናል። ቀጥሎ እንግዲህ በጊዜ ውስጥ ነብሳችን የኖረባትን ስጋችንን እና ያኖረችን ምድራችንን ተሰናብታ ለዘለአለም ወደምንኖርበት ሰማይ ቤት ታርጋለች። ሂደቷን ለመቀጠል። እቺ የመጨረሻዋ ምኞት ናት የሚሉ ቢኖሩ የመፈጠር ወይም የመወለድን ተአምር በገዛ ራሳቸው ሂደት ያዩት መሆኑን የማይገነዘቡ ወይም የረሱ ናቸው። እንጂ ካለመኖር ወደ መኖር (ከአልቦ ወደ ቦ) የነጠረ ተአምር በመሞት ሌላ ተአምር ከመኖር ወደ ዘለአለማዊ ህይወት ሊነጥር ለምን አይችልም? ተስፋ አለ። እምነትም አለ። የዛፍ ፍሬ ያንን የማናውቀው መነሻና መድረሻችንን የሚያውቅ ሀይል በማመንዋ ትረግፋለች። በእምነት ስትጠብቅ ሰንብታ ዝናብ ይመጣላታል። በእምነት ቅጠልዋ ብቅ ትላለች ከፀሀይ ጋር የፈጠራ ስራዋን ትቀጥላለች...

እነዚህ ብርሃናዊና ዕልመታዊ ተቃራኒ ገፀባህሪያት ከውስጣችን ተወስደው በማህበራዊና በአለማዊ ገፅታ ሲታዩ ወደ ሩቅ ምስራቅ ወደ ህንድ ወደ ቻይና አስተሳሰብ ይወስዱናል። ቀንና ሌት፣ ላይና ታች፣ ወንድና ሴት፣ በጋና ክረምት፣ ራብና ጥጋብ፣ እጥረትና ርዝመት፣ርቀትና ቅርበት፣ ደስታና ሀዘን፣ ብርድና ሙቀት...ሁለት ሁለት መሬትና ሰማይ
እነዚህ ሁሉት ሁለቶች መሐልኮ የሚመሳሰል ሶስተኛ አለ። ሶስተኛውን ማወቅ ግን የፈጣሪውን ምስጢር ገልጦ ማየት ስለሚሆን ለኛ ለፍጡራን ክልክል ነው።

ምናልባት እነሱ ሁለት፣ ሁለት እየሆኑ ያሉት እኔ ሶስተኛቸው ወይ እነሱ የፈጠሩኝ ወይ እኔ የፈጠርኳቸው ወይ በየተራ ያኛውም ይኸኛውም። ክልክል ነው!!

@zephilosophy

BY ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy


Share with your friend now:
tgoop.com/Zephilosophy/1069

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Ng Man-ho, a 27-year-old computer technician, was convicted last month of seven counts of incitement charges after he made use of the 100,000-member Chinese-language channel that he runs and manages to post "seditious messages," which had been shut down since August 2020. In 2018, Telegram’s audience reached 200 million people, with 500,000 new users joining the messenger every day. It was launched for iOS on 14 August 2013 and Android on 20 October 2013. A Telegram channel is used for various purposes, from sharing helpful content to implementing a business strategy. In addition, you can use your channel to build and improve your company image, boost your sales, make profits, enhance customer loyalty, and more. Telegram users themselves will be able to flag and report potentially false content. bank east asia october 20 kowloon
from us


Telegram ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
FROM American