Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/Zephilosophy/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tgoop/post.php on line 50
ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy@Zephilosophy P.1054
ZEPHILOSOPHY Telegram 1054
የጠየቁ ተሻግረው አሻገሩን

ስንቱ ይሁን የፖሟ ፍሬ ስትወድቅ እየተመለከተ “ለምን? እና እንዴት? ሳይል ያለፈ! አንድ ሰው ግን ጠየቀ፤ አይዛክ ኒውተን፡፡ ኒውተን አእምሮቸውን በተገቢው ተጠቅመው ማለትም ማወቅን ሽተው፣ ያወቁትንም ለወግ አብቅተውና ለማዕረግ አድርሰው ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች ከተረፉት መካከል በምሳሌነት ሊነሳ የሚችል ግለሰብ ነው። ይህ ሳይንቲስት “በምን ምክንያት?፣ ከምን የተነሳ?' ብሎ፤ በመጠየቅ መንገድ ተጉዞ ምላሾችን ፈለገና ስለ መሬት ስበት እንዲገባን አደረገን። የፍጥነት እና የኃይል ምጥነት እንዲሁም የአድራጊ እና ተደራጊ እኩልነት ሕጎችን አጥንቶ ሚስጥራትን ገለጠልን። ይህን ማድረግ የቻለው አእምሮን በሚገባ ለመጠቀም ከሚያስችሉ መንገዶች መካከል የብልህ ምርጫ የሆነውን መጠየቅን በመምረጡ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡

ይህን መንገድ በመምረጥ ብልህነታቸውን ካስመስከሩ መሃከል በምሳሌነት ኒውተንን ብጠቅስም በተመሳሳይ በመጠየቅ መንገድ ተራምደው መዳረሻቸውን ተሻጋሪ እና አሻጋሪ ያደረጉ ሌሎችም አሉ። ኾኖም አሳዛኙ ነገር ለተፈጠረባቸው ጥያቄ መልስ ለማግኝት ዳክረው እውቀትን ያገኙ ሳይንቲስቶች፣ ተመራማሪዎች፣ ፈላስፎች በርካታ አሊያም በቂ የሚባል አለመሆናቸው ነው። ግና ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት እኚህ በቁጥር ውስን የሆኑ ብልሆች ለምን እንዴት የት ብለው በመጠየቃቸው እና ጥቂት የማይባል ምላሾችን ፈልገው በማግኝታቸው ዓለመ ሰማያትን፣ ምድራችንን እና ማንነታችንን እንድናውቅ ረድተውናል፤ እየረዱንም ይገኛሉ፡፡ ከተፈጥሮ ጋር ተስማምተን እንዴት ዘላቂ መሆን እንደምንችል በምርምር ውጤታቸው አስተምረውናል። ታመን እንድንድን እና እድሜያችንን እንዲዘልቅ መንገድ ጠርገውልናል። ኑሯችን በኋላቀርነት ገመድ ተተብትቦ እንዳይቀር፣ አኗኗራችን ምቹ እንዲሆን፣ እመርታችን እንዲጎለብት እና ዕይታችን እንዲሰፋ አድርገዋል።

አሁንም ቢኾን የመጠየቅ ጉዞን መከተል እንዳለበት ተረድቶ የወሰነ እንዲሁም ወስኖ መራመድ የጀመረ ሰው መዳረሻው ከላይ በምሳሌነት ካየነው የኒውተን ታሪክ የተለየ አይሆንም። እንግዲህ ይህን ያወቀ ተጓዥ በጨለማ ውስጥ ብርሃን ማግኝት እንደሚችል ያምናል፤ ያውቃልም። ይህ መንገደኛ ማምለጫ የለሽ በሚመስል ወጥመድ ውስጥ ቢገኝ እንኳን መውጫ እና ማምለጫ ዘዴን ያበጃል እንጂ በፍጹም ተስፋ አይቆርጥም፡፡ እንዲህ ዓይነት ተራማጅ ሰው መሬት ላይ የማያወርደው ህልም እንደሌለው ከእውነቶቹ አንዱ ነው፡፡ ወደ ኋላ ሊጎቱት የሚችሉ እልፍ አእላፍ ነገሮች እንደሚገጥሙት ቀድሞዎንም ያውቃል። ነገር ግን መሮጥ ቢያቅተው ተራምዶ፣ መራመድ ቢሳነው ተንፏቆ፣ መንፏቀቅ ቢያቅተው ወደ ፊት ወድቆ ካለመበት ይደርሳል፤ አሸናፊም ይሆናል። አሸናፊም ሲሆን ከራሱ አልፎ ለብዙዎች በነገሮቹ ኹሉ ይተርፋል።

✍️ፍሬው ማሩፍ
📚ጥያቄዎቹ

@zephilosophy



tgoop.com/Zephilosophy/1054
Create:
Last Update:

የጠየቁ ተሻግረው አሻገሩን

ስንቱ ይሁን የፖሟ ፍሬ ስትወድቅ እየተመለከተ “ለምን? እና እንዴት? ሳይል ያለፈ! አንድ ሰው ግን ጠየቀ፤ አይዛክ ኒውተን፡፡ ኒውተን አእምሮቸውን በተገቢው ተጠቅመው ማለትም ማወቅን ሽተው፣ ያወቁትንም ለወግ አብቅተውና ለማዕረግ አድርሰው ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች ከተረፉት መካከል በምሳሌነት ሊነሳ የሚችል ግለሰብ ነው። ይህ ሳይንቲስት “በምን ምክንያት?፣ ከምን የተነሳ?' ብሎ፤ በመጠየቅ መንገድ ተጉዞ ምላሾችን ፈለገና ስለ መሬት ስበት እንዲገባን አደረገን። የፍጥነት እና የኃይል ምጥነት እንዲሁም የአድራጊ እና ተደራጊ እኩልነት ሕጎችን አጥንቶ ሚስጥራትን ገለጠልን። ይህን ማድረግ የቻለው አእምሮን በሚገባ ለመጠቀም ከሚያስችሉ መንገዶች መካከል የብልህ ምርጫ የሆነውን መጠየቅን በመምረጡ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡

ይህን መንገድ በመምረጥ ብልህነታቸውን ካስመስከሩ መሃከል በምሳሌነት ኒውተንን ብጠቅስም በተመሳሳይ በመጠየቅ መንገድ ተራምደው መዳረሻቸውን ተሻጋሪ እና አሻጋሪ ያደረጉ ሌሎችም አሉ። ኾኖም አሳዛኙ ነገር ለተፈጠረባቸው ጥያቄ መልስ ለማግኝት ዳክረው እውቀትን ያገኙ ሳይንቲስቶች፣ ተመራማሪዎች፣ ፈላስፎች በርካታ አሊያም በቂ የሚባል አለመሆናቸው ነው። ግና ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት እኚህ በቁጥር ውስን የሆኑ ብልሆች ለምን እንዴት የት ብለው በመጠየቃቸው እና ጥቂት የማይባል ምላሾችን ፈልገው በማግኝታቸው ዓለመ ሰማያትን፣ ምድራችንን እና ማንነታችንን እንድናውቅ ረድተውናል፤ እየረዱንም ይገኛሉ፡፡ ከተፈጥሮ ጋር ተስማምተን እንዴት ዘላቂ መሆን እንደምንችል በምርምር ውጤታቸው አስተምረውናል። ታመን እንድንድን እና እድሜያችንን እንዲዘልቅ መንገድ ጠርገውልናል። ኑሯችን በኋላቀርነት ገመድ ተተብትቦ እንዳይቀር፣ አኗኗራችን ምቹ እንዲሆን፣ እመርታችን እንዲጎለብት እና ዕይታችን እንዲሰፋ አድርገዋል።

አሁንም ቢኾን የመጠየቅ ጉዞን መከተል እንዳለበት ተረድቶ የወሰነ እንዲሁም ወስኖ መራመድ የጀመረ ሰው መዳረሻው ከላይ በምሳሌነት ካየነው የኒውተን ታሪክ የተለየ አይሆንም። እንግዲህ ይህን ያወቀ ተጓዥ በጨለማ ውስጥ ብርሃን ማግኝት እንደሚችል ያምናል፤ ያውቃልም። ይህ መንገደኛ ማምለጫ የለሽ በሚመስል ወጥመድ ውስጥ ቢገኝ እንኳን መውጫ እና ማምለጫ ዘዴን ያበጃል እንጂ በፍጹም ተስፋ አይቆርጥም፡፡ እንዲህ ዓይነት ተራማጅ ሰው መሬት ላይ የማያወርደው ህልም እንደሌለው ከእውነቶቹ አንዱ ነው፡፡ ወደ ኋላ ሊጎቱት የሚችሉ እልፍ አእላፍ ነገሮች እንደሚገጥሙት ቀድሞዎንም ያውቃል። ነገር ግን መሮጥ ቢያቅተው ተራምዶ፣ መራመድ ቢሳነው ተንፏቆ፣ መንፏቀቅ ቢያቅተው ወደ ፊት ወድቆ ካለመበት ይደርሳል፤ አሸናፊም ይሆናል። አሸናፊም ሲሆን ከራሱ አልፎ ለብዙዎች በነገሮቹ ኹሉ ይተርፋል።

✍️ፍሬው ማሩፍ
📚ጥያቄዎቹ

@zephilosophy

BY ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy


Share with your friend now:
tgoop.com/Zephilosophy/1054

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

How to Create a Private or Public Channel on Telegram? SUCK Channel Telegram Telegram has announced a number of measures aiming to tackle the spread of disinformation through its platform in Brazil. These features are part of an agreement between the platform and the country's authorities ahead of the elections in October. Today, we will address Telegram channels and how to use them for maximum benefit. The administrator of a telegram group, "Suck Channel," was sentenced to six years and six months in prison for seven counts of incitement yesterday.
from us


Telegram ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
FROM American