tgoop.com/IbnShifa/5099
Last Update:
👉 በውጭም በሀገርም ላሉ ሰለፍዮች
አላህ ካለ የፊታችን ሰኞ ግንቦት 25/2017 ለሀራ ሰለፍዮች ሀገር አቀፍ ድጋፍ እንዲደረግ የሀገራችን ሰለፍይ መሻኢኾች አደራ ብለዋል ። በመሆኑም በዚሁ እለት ለሀራ ሰለፍዮች የቦታ ግዢና የመስጂድ ግንባታ ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ይኖራል ።
አላህ ካለ በዚህ ፕሮግራም ላይ ሀገር ውስጥም ከሀገር ውጪም ያሉ መሻኢኾች የሚሳተፉ ይሆናል ። የተለመደው አይነት ተራ ፕሮግራም ሳይሆን በአይነቱ ለየት ያለ ለመላው የሀገራችን ሰለፍዮች የሀራ ወንድሞቻችን ላቀረቡት ከጎናችን ሁኑ አንገታችንን ቀና እንድናደርግ አድርጉን ለሚለው ጥሪ ምላሽ የሚሰጥበትና በወሎ ምድር ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሸይኽን አስሮ ደረሶችን የማባረር ጥቁር ታሪክ ፍቀን ሌላ ታሪክ የምንሰራበት ቀን ነው ። ታዲያ ውድ የሀገራችን ሰለፍዮች በሙሉ በየሰፈራችንና መንደራችን ያሉትን ፕሮግራሞች ለአንድ ሳምንት ቆም አድርገን በዚህ ታሪካዊ የሰለፍዮች ርብርብ አሻራችንን ለማኖርና የሸይኻችንን የተሰበረ ቅስም ለመጠገን የምንችለውን እናድርግ ።
በሚያልፍ ቀን የማያልፍ ታሪክ ሰርተን ሀራ ላይ የተከሰተውን አሳዛኝ ክስተት ወደ አስደሳች ታሪክ በመቀየር የተባረሩ ደረሶች እንዲመለሱ እናድርግ ። ወኔና ፍላጎት ከሌለ ገንዘብ ምንም አይሰራም ። ፍላጎት ካለ ተባብሮ የማይሰራ ነገር የለምና ከልባችን እንነሳ ።
https// www.tgoop.com/haraselefi
BY [ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]

Share with your friend now:
tgoop.com/IbnShifa/5099