tgoop.com/HISCULHEROFETHIOPIA/5733
Last Update:
ክርስቶስ ከሙታን ተነስቷል።
በራሱ ኃይል ስልጣን።
የእግዚአብሔር ሰለም ከእናተ ጋር ይሁን።
የጌታችን የመደኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ
ሞቱ በራሱ መሥዋዕትነት እንጂ በኃይል ወይም በግዳጅ አለመሆኑ ትንሣኤው አረጋግጧል።የክርስቶስን ትንሣኤ ማመን ማለት በእርሱ ፍቅር በእርሱ ምሥዋዕት ሆኖ
መቅረብና በእርሱ የሰው ልጆችን ከሞት ባርነት
ነጻ ማውጣት ማመን ነው። ከዚህ ተጨማሪ
በእርሱ ኃይል አስቀድሞ ስለራሱ በተናገራቸው
ቃላትና ከእግዚአብሔር ጋር አንድ በመሆኑ
ማመን ነው። ይህ ኃይል በሥጋው ሞቶ በመለኮቱ ሕያው የሆነው የአንድዬ የአምላካችን
የኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ነው።
ይህ ኃይል ለዮሐንስ በራዕዩ እንደሚከተለው
የተነገረው የአንድዬ የኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል
ነው።".....አትፍራ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ ሞቼም ነበርሁ እንሆም ከዘላለም አስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ
የሞተና የሲዖል መክፈቻ አለኝ።"ራእ 1:8።
ስለዚህ ኃይል አንድዬ ሐዋርያውን ቅዱስ
ጴጥሮስን በሐምሣኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ
በወረደባቸው ጊዜ ሰክረዋል የሚል ቃል
ከአይሁድ በተነገረባቸው ጊዜ እንዲህ ብሎ
አናግሮታል"እግዚአብሔር ግን የሞትና ጣር
አጥፍቶ አስነሰው ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና።" ሐዋ 2:24። ዳዊትንም ትንቢት
አናግሮታል"...ነፍሴን በሲዖል አትተዋትምና
ቅዱስ መበስበስን ያይ ዘንድ አተሰጠውም። "
መዝ 15: 8-11።ቅዱስ ጳውሎስም ፦
"....ክርስቶስ ከሙታን ተነሥቶ ወደ ፊት
እንዳይሞት ሞትም ወደ ፊት እንዳይገዛው
እናውቃለንና። " ሮሜ 6 :9። ስለዚህ የጌታችን
ትንሣኤ የሚያስተምረን ወደፊት የማይምት ሞት የማይገዛው አምላካችን ነው። አለም ያላት
አምላክ ግን "የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን
አሳብ አሳወረ" 2ኛ ቆሮ 4:4 ተብሎ እንደተነገረ
አለም ያላት አምላክ ወደውጭ የሚጣል እና የሚፈረድበት ነው። ዮሐ 12:31-32 ራእ 20:10። መልካም ጊዜ።
BY ኢትዮጵያ
Share with your friend now:
tgoop.com/HISCULHEROFETHIOPIA/5733