tgoop.com/tseomm/6618
Last Update:
https://youtu.be/xeGqlPtO84k
👉👉አስደንጋጩ ሪፖርት በቅዱስ ሲኖዶስ
ከአርባ ዓመት በላይ በኢትዮጵያ ስድስት መቶ ብር ብቻ እየተከፈላቸው የኖሩት
የጀማይካው ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ የብፁዕ አቡነ ታዴዎስ ምን አሉ?
አርባ ዘመን ሰርከ ህብስት የዕለት እንጀራ በማይገኝበት ጀማይካ ሀገር ሳገለግል ስኖር ልኑር ልሙት ሲኖዶሱ ያልጠየቅኝ ለምንድነው ?
ይህን ያህል ዘመን እኔ እና ስራ አስኪያጄ ስድስት መቶ ብር ብቻ እየተከፈለን ስንኖር በያመቱ ለስብሰባ ባለመገኘቴ ለምን እንዴት ብላችሁ አትጠይቁም?
ይህን ካሉ በኋላ አቡነ ታዴዎስ : በሉ እኔም ስራአስኪያጄም አርባ ዓመት በእንግሊዝኛ ሰብክን አገለግልን አሁን ግን ደክሞናል እርጅናው ተጭኖናል ሌላ ሰው መድቡ የጀማይካ ክርስቲያኖች ያለአባት አንድ ቀን ማደር አይችሉም ብለው እርፍ አሉ
ያንጊዜ ምን እንደሚፈጠር መገመት አያቅትም
ስድስት መቶ ብር እየተከፈለው የሚያገለግል ሥራአስኪያጅ እና ሊቀጳጳስ የት ይመጣል የጀማይካን አየር ችግሩን ተቋቁሞ ቅዱስ ሲኖዶስ የጣለብኝን ሀላፊነት እወጣለሁ የሚል አገልጋይ ከየት ይመጣል
አባቶች ሁሉንም ከሰሙ በኋላ እስከጥቅምት ይጠብቁን እናስብበት እንደተባለ እና በብፁዕ አቡነ ታዴዎስ የቀረበው ሪፖርት የብዙዎችን ልብ እንደነካ ሰማን
የብፁዕ አቡነ ታዴዎስ ትዕግሥት ምን አይነት ትዕግሥት ነው
የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን አሜን 🙏🙏🙏
ዛሬም በእውነት እግዚአብሔር ሰው አለው 🙏🙏
ብፁዕ አቡነ ታዴዎስ የካረቢያንና የላቲን አሜሪካ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ናቸው ።
በ1985 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የመጀመሪያዎቹ ተሿሚ ሊቃነ ጳጳሳት አንዱ ናቸው።
ከ Aba Gebremaryam ገጽ የተዛወረ
BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu

Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6618
