tgoop.com/tseomm/6614
Last Update:
አንዳንዱ ሰባኪ ዐውደ ምሕረት ላይ ቆሞ "በእኔ አድሮ የሚናገር መንፈስ ቅዱስ ነው" እያለ ሲናገር ይስተዋላል። ነገር ግን ይህ ሰው ክሕደትን ቢያስተምር የመንፈስ ቅዱስ ትምህርት ነው ሊባል ነው? በጭራሽ።
ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ ይመራል የሚለውን አነጋገር ይዘውም አንዳንዶች በሲኖዶስ የሚወሰኑ ውሳኔዎች ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ናቸው ሲሉ ይስተዋላል። ይህ ዓይነት ንግግር ይታረም። የኬልቄዶን ሲኖዶስ ክርስቶስን አንድ አካል ሁለት ባሕርይ ብሎ ክዷል። ፓትርያርክ አይሳሳትም፣ የሰዎች ስብስብ የሆነው ሲኖዶስ አይሳሳትም ብሎ መናገር ካቶሊካዊ እሳቤ ነው።
ለምሳሌ ባለፈው የእኛ ሲኖዶስ ለብዙ ምእመናን ሞት ምክንያት የሆነውን ሕገ ወጥ ሹመት በቀኖናዊ አካሄድ ሳይሆን በፖለቲካዊ ስምምነት ዝም ብሎ ማለፉን የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ነው ማለት መንፈስ ቅዱስን የብልጽግና ፓርቲ አባል የማድረግ የተሳሳተ አነጋገር ነው።
ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ ይመራል የሚባለው በመንፈስ ቅዱስ አስተምህሮ ከተመራ ነው። ሰባኪውም በእኔ አድሮ የሚናገረው መንፈስ ቅዱስ ነው ማለት የሚገባው የመንፈስ ቅዱስን ትምህርት ካስተማረ ነው። ከዚህ ውጭ ስሕተትን በመንፈስ ቅዱስ ማሳበብ ነውር ነው።
© በትረ ማርያም አበባው
ስለ ፎቶው ማብራርያ👇
ከስድስት ቀን በፊት ይችን ጽሑፍ ልከውልኝ ነበረ። እኔ እየቀለዱ ስለመሰለኝ ስቄው አልፌ ነበር። ለካ የምር ኖሯል።
መቼም ለዚህ ገጽ ባለቤት መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ነው አትሉኝም 😀😀😀😀።
ፖለቲካዊ ሹመትን የመንፈስ ቅዱስ ነው አትበሉን።
BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu

Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6614