tgoop.com/tseomm/6579
Create:
Last Update:
Last Update:
ማኀበረ ቅዱሳን ለሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ምላሽ የሚያገኙበት አገልግሎት አስጀመረ
#FastMereja I በማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚፈልጉትን ሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ቁጥር ደውለው ማብራሪያ የሚያገኙበት አገልግሎት ማስጀመሩን ፋስት መረጃ ሰምቷል።
«ሃሎ መምህር» የተሰኘው አገልግሎቱ እንዲመለስልዎ የሚፈልጉትን ሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ቁጥር 0111 55 32 32 በመደወል ለጥያቄዎ ማብራሪያ እና መልስ ከመምህራን ያገኛሉ ተብሏል።
ዘወትር ከሰኞ - አርብ ከጠዋቱ 4:00 እስከ ቀኑ 10:00 አገልግሎቱ የሚሰጥ ሲሆን ሰኞ፣ ረቡዕ እና ሐሙስ በአማርኛና በኦሮምኛ፣ ማክሰኞ እና ዓርብ በአማርኛ ቋንቋ ብቻ አግልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu

Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6579