TSEOMM Telegram 6537
እንኳን ለዳግም ትንሳኤው በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ፤ ማለት ሲገባኝ .......። አንዳንድ ድርጅቶች እና አንዳንድ አስመሳይ ሰዎች ክህደትን እና የደም ዋጋን የሚያሳንስ እጅግ በጣም መራር ነገር በማር ለውሰው እንጋታችሁ ሲሉ ይህንን ለመጻፍ ተገደድኩ ፡፡
=========================================
+ አርእስት ፦ "" መች ተለመደና ከተኩላ ዝምድና ፤ አሁን ግን አየነው ወልዶ ከብዶ ገና ""
+ ዓላማ ፦ የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ሁለንተና በመጨፍለቅ ፤ ቤተክርስቲያን ለትውልድ ፣ ለሀገር እንዲሁም ለዓለም ያበረከተችውን እጅግ ከፍተኛ በምንም ሊተመን የማይችል አስተዋጾ ጥላሸት የሚያለብስ .... አባቷን አታውቅ አያቷን ትናፍቃለች አይነት እጅግ አስነዋሪ ፤ ሥጋን ቁጠር ቢሉት ጣፊን እንደ ሙዳ አይነት እጅግ ዘኛኝ እና ትውልድ የሚቀጩ ድርጊቶችን ለሚያስተላልፉ ሚዲያዎች በተለይ ኢቲቪ እና ሌሎች ላይ የመፋረጃ ሰነድ እንዲሆን ፡፡
+ የሚመለከተው ፦ ሁሉም የዚች ሀገር ዜጋ
+ ማስረጃ ፦ ምንጩን በማጠቃለያው ላይ እንደ ጉድ ተዘርግፎ ያገኙታል
=========================================
ክፍል አንድ ፦ " ተኩላው ማነው ......... ? " ፤ ምልክቶቹ ............
=========================================
ተኩላው እጅግ በጣም ዘገምተኛ ነገር ግን ድምጹም ፣ ቁመናውም ፣ አለባበሱም ከመንጋው ጋር የሚመሳሰል እና አደገኛ ነው ፡፡ ይህ ተኩላ ሃይማኖት የለውም ነገር ግን ሃይማኖት ሲሰብክ እና ባለ ሥነ ምግባር ሊያደርግክ ይሞክራል ፡፡
ምሳሌ አንደ ፦
1። "በቫቲካን የሚገኘው የኢትዮጵያ አሻራ ምንድን ነው ? ETV | EBC | EBCDOTSTREAM " በሚል ዶክመንተሪ ከአራት ቀን በፊት ሰርቶ ኢትዮጲያውያን ወደ ቫቲካን አይናቸውን እንዲተክሉ ለማድረግ እና ልክ በለሱን ሳትበላው "ኦሪት ዘፍጥረት 3፥6 ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ " የተባልለውን መልክ ቀይረው የሞት ዶክመንት የጋቱን አይነት ነው ፡፡
++ የሚገርመው ፦ ቫቲካን በኢትዮጲያ ህዝብ ላይ በተለይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ ያደርሰችው ለዘመናት ያላቋረጠ የግፍ ዓይነት እንደ ኢያን ካምፕቤል የዘገበልን ማን አለ ? ከአራቱ መጽሐፍቶቹ በተለይ "Holy War: The Untold Story of Catholic Italy's Crusade Against the Ethiopian Orthodox Church" የተባለው አንባቢ ቢችል ገዝቶ ቢያነበው ግድ ይላል ፡፡ እንኳን ወደ ቫቲካን ልናይና አሻራ ልንሻ የአባቶቻችን ደም በእምነት ፣ በመንፈስ ፣ በሥጋ እሾክ ሆኖ ይወጋናል ፡፡
ጥላቻ መስሎክ እንዳትታለል ...... የብራና መጽሐፍቶችክ ፣ ሰነዶችክ ምናልባት ለዚህ ትውልድ ትልልቅ መፍትሄ የሚሆኑ የጥበብ ቀመሮችህ ቫቲካን ዘግተው ቆልፈው እንኳን አንተ ባለቤቱን ሌላንም አያስነኩም ፤ ቀለበቱን ስመክ እንኳን ካቶሊክ ብትሆን ሲያምርክ ይቀራል አታገኘውም ፡፡ ድንቄም አሻራ !!!
++ አባዜው ፦ ኢትዮጵያ እያሉ ጠቅልለው ይናገሩታል እንጂ ካቶሊኮቹ ፤ ኢትዮጵያው የሆኑት መጽሐፍቱን እና ጥናታዊ አውደርእያቸውን እንኳን እውቅና አይሰጡም ፤ እውቅና የሚሰጡት መቼ ብቻ ነው ........፤ ካቶሊክ እንዳደረጉህ ሊነግሩህ እና ሊነግሩልክ ሲፈልጉ ነው ልክ እንደ አሻራው ፡፡ ባዶ አዳራሽ እና የምንፍቅና ትምህርታቸው ያታለላቸው ጥቂቶች ማስደሰቻ ፡፡ ለሌላው ዓለም ግን ኦርቶዶክሳዊነትህን ያደበዝዙበታል ትልቅ ፖለቲካ ነው ይሄ ከገባክ ፡፡
==========
ከምሳሌው የምንረዳው
1. የተኩላው = ካቶሊክ
2. ድምጹ = ታላቂቷ ኢትዮጲያ እና ኢትዮጲያውያን
3. ቁመናው = ድንበር የተሻግረ ቅርስ አለክ የሚል ፌዝ
4. አለባበስ = ክርስትና
5. ዝምድናው = ከገዳይ ፣ ከሌባ ፣ ከመናፍቅ ፣ ከሰይጣን ደቀ መዝሙር ጋር አንሶላ መጋፈፍ
6. ሴራው ምንድነው = "ሴራው ግብጽ ከምታገሳበት ከዴር ሱልጣን ፣ ይሄ ይቀርብካል የሚል ትውከት " ፤ " ዲማ ጊዮርጊስን በድሮን አፍርሼ ፣ ቫቲካንን በድሮን ቀርጬ ላሳይክ አይነት ድድብና " ፤ " የዝቋላን ጫካ ከቃጠሎ ከማድን ፣ መከኮሳቱን ከገዳይ ከምጠብቅ ... ልሻገር ቫቲካን ባህር አቋርጬ ልቅረጽና ልላክ ዶክመንተሪ አይነት ጊልዶ የቀረው የሰዶም ዘፈን "
7. ጋብቻውን የሚያስፈጽሙት = ዶክመንተሪ የሚሰሩ ፣ መጽሐፍ የሚጽፉ ባንዳዎች ፣ የምንግስት አካላት ፣ የማያፍሩት ተኩላው ተቋማት !
=========================
ለአዛኝ ቅቤ አንጓቾች .........
1። ዴር ሱልጣን ይከበርልን ፤ የወሰዱትን ድርሻችንን ይመልሱልን !!!
2። ቫቲካን የቆለፈችውን ከፍታ ፤ መዛግብቶቻችን ይመለሱልን !!!
3። የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን እውቅና የነፈገ ምንም አይነት ፕሮግራም ለኢትዮጵያውያን መቅረብ የለበትም እንዳያቀርቢ ራሳቸውን ያግዱልን !!!
=========================
ክፍል ሁለት ይቀጥላል ....

©ሰናይ ጥበቡ
👍3



tgoop.com/tseomm/6537
Create:
Last Update:

እንኳን ለዳግም ትንሳኤው በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ፤ ማለት ሲገባኝ .......። አንዳንድ ድርጅቶች እና አንዳንድ አስመሳይ ሰዎች ክህደትን እና የደም ዋጋን የሚያሳንስ እጅግ በጣም መራር ነገር በማር ለውሰው እንጋታችሁ ሲሉ ይህንን ለመጻፍ ተገደድኩ ፡፡
=========================================
+ አርእስት ፦ "" መች ተለመደና ከተኩላ ዝምድና ፤ አሁን ግን አየነው ወልዶ ከብዶ ገና ""
+ ዓላማ ፦ የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ሁለንተና በመጨፍለቅ ፤ ቤተክርስቲያን ለትውልድ ፣ ለሀገር እንዲሁም ለዓለም ያበረከተችውን እጅግ ከፍተኛ በምንም ሊተመን የማይችል አስተዋጾ ጥላሸት የሚያለብስ .... አባቷን አታውቅ አያቷን ትናፍቃለች አይነት እጅግ አስነዋሪ ፤ ሥጋን ቁጠር ቢሉት ጣፊን እንደ ሙዳ አይነት እጅግ ዘኛኝ እና ትውልድ የሚቀጩ ድርጊቶችን ለሚያስተላልፉ ሚዲያዎች በተለይ ኢቲቪ እና ሌሎች ላይ የመፋረጃ ሰነድ እንዲሆን ፡፡
+ የሚመለከተው ፦ ሁሉም የዚች ሀገር ዜጋ
+ ማስረጃ ፦ ምንጩን በማጠቃለያው ላይ እንደ ጉድ ተዘርግፎ ያገኙታል
=========================================
ክፍል አንድ ፦ " ተኩላው ማነው ......... ? " ፤ ምልክቶቹ ............
=========================================
ተኩላው እጅግ በጣም ዘገምተኛ ነገር ግን ድምጹም ፣ ቁመናውም ፣ አለባበሱም ከመንጋው ጋር የሚመሳሰል እና አደገኛ ነው ፡፡ ይህ ተኩላ ሃይማኖት የለውም ነገር ግን ሃይማኖት ሲሰብክ እና ባለ ሥነ ምግባር ሊያደርግክ ይሞክራል ፡፡
ምሳሌ አንደ ፦
1። "በቫቲካን የሚገኘው የኢትዮጵያ አሻራ ምንድን ነው ? ETV | EBC | EBCDOTSTREAM " በሚል ዶክመንተሪ ከአራት ቀን በፊት ሰርቶ ኢትዮጲያውያን ወደ ቫቲካን አይናቸውን እንዲተክሉ ለማድረግ እና ልክ በለሱን ሳትበላው "ኦሪት ዘፍጥረት 3፥6 ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ " የተባልለውን መልክ ቀይረው የሞት ዶክመንት የጋቱን አይነት ነው ፡፡
++ የሚገርመው ፦ ቫቲካን በኢትዮጲያ ህዝብ ላይ በተለይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ ያደርሰችው ለዘመናት ያላቋረጠ የግፍ ዓይነት እንደ ኢያን ካምፕቤል የዘገበልን ማን አለ ? ከአራቱ መጽሐፍቶቹ በተለይ "Holy War: The Untold Story of Catholic Italy's Crusade Against the Ethiopian Orthodox Church" የተባለው አንባቢ ቢችል ገዝቶ ቢያነበው ግድ ይላል ፡፡ እንኳን ወደ ቫቲካን ልናይና አሻራ ልንሻ የአባቶቻችን ደም በእምነት ፣ በመንፈስ ፣ በሥጋ እሾክ ሆኖ ይወጋናል ፡፡
ጥላቻ መስሎክ እንዳትታለል ...... የብራና መጽሐፍቶችክ ፣ ሰነዶችክ ምናልባት ለዚህ ትውልድ ትልልቅ መፍትሄ የሚሆኑ የጥበብ ቀመሮችህ ቫቲካን ዘግተው ቆልፈው እንኳን አንተ ባለቤቱን ሌላንም አያስነኩም ፤ ቀለበቱን ስመክ እንኳን ካቶሊክ ብትሆን ሲያምርክ ይቀራል አታገኘውም ፡፡ ድንቄም አሻራ !!!
++ አባዜው ፦ ኢትዮጵያ እያሉ ጠቅልለው ይናገሩታል እንጂ ካቶሊኮቹ ፤ ኢትዮጵያው የሆኑት መጽሐፍቱን እና ጥናታዊ አውደርእያቸውን እንኳን እውቅና አይሰጡም ፤ እውቅና የሚሰጡት መቼ ብቻ ነው ........፤ ካቶሊክ እንዳደረጉህ ሊነግሩህ እና ሊነግሩልክ ሲፈልጉ ነው ልክ እንደ አሻራው ፡፡ ባዶ አዳራሽ እና የምንፍቅና ትምህርታቸው ያታለላቸው ጥቂቶች ማስደሰቻ ፡፡ ለሌላው ዓለም ግን ኦርቶዶክሳዊነትህን ያደበዝዙበታል ትልቅ ፖለቲካ ነው ይሄ ከገባክ ፡፡
==========
ከምሳሌው የምንረዳው
1. የተኩላው = ካቶሊክ
2. ድምጹ = ታላቂቷ ኢትዮጲያ እና ኢትዮጲያውያን
3. ቁመናው = ድንበር የተሻግረ ቅርስ አለክ የሚል ፌዝ
4. አለባበስ = ክርስትና
5. ዝምድናው = ከገዳይ ፣ ከሌባ ፣ ከመናፍቅ ፣ ከሰይጣን ደቀ መዝሙር ጋር አንሶላ መጋፈፍ
6. ሴራው ምንድነው = "ሴራው ግብጽ ከምታገሳበት ከዴር ሱልጣን ፣ ይሄ ይቀርብካል የሚል ትውከት " ፤ " ዲማ ጊዮርጊስን በድሮን አፍርሼ ፣ ቫቲካንን በድሮን ቀርጬ ላሳይክ አይነት ድድብና " ፤ " የዝቋላን ጫካ ከቃጠሎ ከማድን ፣ መከኮሳቱን ከገዳይ ከምጠብቅ ... ልሻገር ቫቲካን ባህር አቋርጬ ልቅረጽና ልላክ ዶክመንተሪ አይነት ጊልዶ የቀረው የሰዶም ዘፈን "
7. ጋብቻውን የሚያስፈጽሙት = ዶክመንተሪ የሚሰሩ ፣ መጽሐፍ የሚጽፉ ባንዳዎች ፣ የምንግስት አካላት ፣ የማያፍሩት ተኩላው ተቋማት !
=========================
ለአዛኝ ቅቤ አንጓቾች .........
1። ዴር ሱልጣን ይከበርልን ፤ የወሰዱትን ድርሻችንን ይመልሱልን !!!
2። ቫቲካን የቆለፈችውን ከፍታ ፤ መዛግብቶቻችን ይመለሱልን !!!
3። የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን እውቅና የነፈገ ምንም አይነት ፕሮግራም ለኢትዮጵያውያን መቅረብ የለበትም እንዳያቀርቢ ራሳቸውን ያግዱልን !!!
=========================
ክፍል ሁለት ይቀጥላል ....

©ሰናይ ጥበቡ

BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6537

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Unlimited number of subscribers per channel During the meeting with TSE Minister Edson Fachin, Perekopsky also mentioned the TSE channel on the platform as one of the firm's key success stories. Launched as part of the company's commitments to tackle the spread of fake news in Brazil, the verified channel has attracted more than 184,000 members in less than a month. The imprisonment came as Telegram said it was "surprised" by claims that privacy commissioner Ada Chung Lai-ling is seeking to block the messaging app due to doxxing content targeting police and politicians. The court said the defendant had also incited people to commit public nuisance, with messages calling on them to take part in rallies and demonstrations including at Hong Kong International Airport, to block roads and to paralyse the public transportation system. Various forms of protest promoted on the messaging platform included general strikes, lunchtime protests and silent sit-ins. Image: Telegram.
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
FROM American