tgoop.com/tseomm/6517
Last Update:
በግሌ አመሰግናለሁ አባቶቼ!
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የቅርብ ጊዜ ፈተናዎች ውስጥ አንዱ ሕጉን የሚያውቁና የሚያስተምሩ ሊቃውንት ዝምታ ይመስለኛል።
በተለይም ባለፉት ሁለት ዓመታት በነበረው የታሪክ ጥላሸታችን ውስጥ በቁጥር ካሉን አንጻር ጥቂት የሚባሉት ብቻ ተሟግተዋል። በመናገራቸው ብቻም በራሱ በቤተ ክህነቱ ሳይቀር አናውቃችሁም ተብለው ተገፍተውም ነበር።
ብዙሃኑ ግን ዝምታን መርጠው ነበር። በዚህም እንደምእመን ለምን ብለን ጠይቀናል። ከውጭ ጫና ሲበዛ በትር ሲጠነክር ብቻ ሳይሆን ከውስጥ እሾህ አሜካላ ሲበቅል መጥተው ካልተጋፈጡ ወጥተው ካልመሰከሩ ምኑን አስተማሩን? ቤተ ክርስቲያን የሰጠቻቸውን ስምና ክብርስ ለምናቸው ነው ብለን አምተናቸዋል።
ዛሬ ብፁዕነታቸው በተናገሩት ላይ እነዚህና ሌሎች የመጻሕፍት መመህራን ግር ብለው ቢመጡ እጅግ ደስ አለኝ።
አንድም ስለሃይማኖታቸው አንድም እንተ ስማለማርያም ብለው በስሟ ተማጽነው የተማሩባት ትምክህታቸው ናትና ቅናታቸውን ቀናሁበት።
አንድም ደግሞ ብዙ ጊዜ ጳጳሳቱን ተው ማለት ዶግማ መጣስ ለሚመስለው በእውቀትና በአክብሮት መመለስን አሁንም ስላሳዩን፣ ሃይማኖታችን ከማንም ከምንም የማናስበልጠውና የማንደራደርብት መሆኑን ስላሳዩን እንደአንዲት ምእመን እጅ እነሳለሁ።
በተለይም በቤተ ክህነቱ መዋቅር ሁኖ መታገልን ነውር ለሚያደርጉና በፍርሃት ለተቀፈደዱ ምሳሌ ትሆናላችሁ።
እናንተ ዝም ስትሉ ነው ምእመኑ እመልሳለሁ እያለ የሚያጠፋውና አትጥፉብን።
https://www.facebook.com/share/16N1EEQJGE/?mibextid=wwXIfr
https://www.facebook.com/share/15LeKA2YEj/?mibextid=wwXIfr
https://www.facebook.com/share/12JFpjVbji1/?mibextid=wwXIfr
https://www.facebook.com/share/1RDzsSWj7h/?mibextid=wwXIfr
https://www.facebook.com/share/18uH1wSMr3/?mibextid=wwXIfr
https://www.facebook.com/share/12CmMHqEhXz/?mibextid=wwXIfr
https://www.facebook.com/share/16UmRUdqfC/?mibextid=wwXIfr
👉ጋዜጠኛ መስከረም ጌታቸው እንደጻፈችው
BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6517