TSEOMM Telegram 6510
አንድም በአላዋቂነትና ድንቁርና፣ አንድም ነገር አማረልኝ ብለው የማይገባ ማራቀቅ ውስጥ ሲገቡ ፣አንድም ትኩረት ለመሳብ ካላቸው የትኩረት ጥማት ፣ አንድም ሆነ ብለው ልባቸውን ከውጭ እግራቸውን ከቤተክርስቲያን አጸድ ያቆሙ በሁለት ቢላዋ የሚበሉ ሰዎች፣ አንድም ሰውን ለማስደሰት የሚናገሯቸው ንግግሮች በቤተክርስቲያን ዐውደ ምሕረት የሚነገሩ ግን ደግሞ በጣም አደገኛና አንዳንዴም ኑ*ፋ*ቄ ጭምር ናቸው።

የቅድስት ቤተክርስቲያን ትምህርት ያልሆኑ፣ ከአበው ወይም ከመጻሕፍት ያልተገኙ፣ ትውፊታዊ መሠረትም የሌላቸው "ትምህርቶች" በየዐውደ ምሕረቱ መነገር ከጀመሩ ከራርመዋል። ከሰሞኑ ከአባ ገብርኤል 'ትምህርት' በተጨማሪ እኔ የገጠመኝን እና አንድ ወንድም ገጥሞት ያጫወተኝን ሁለት ታሪኮች ላንሳ።

የመጀመሪያው እና ባለፈው በጸሎተ ሐሙስ አንድ የደብር አስተዳዳሪ የተናገሩት ነው ብሎ አንድ ወንድም የነገረኝ ነወ። በቅዳሴው ወቅት ምዕመናን ሥጋ ወደሙን እየተቀበሉ አስተዳዳሪው እያስተማሩ በመሐል እንዲህ አሉ አለኝ። "የዛሬው ሥጋ ወደም እስከዛሬ ከምንቀበለው ሁሉ የተለዬ ነው።" አሉ አለ። ይህ በጣም ስሕተት ያለበት ንግግር ነው።

ቤተክርስቲያን በየዕለቱ በቅዳሴው የምትሰዋው ቅዱስ ሥጋውና ደሙ ያኔ ጌታ ለሐዋርያት ካቀበላቸው የተለየ መስዋዕት አትሰዋም። ምናልባት ሊሉ የፈለጉት ሌላ ሊሆን ይችላል። የዕለቱን ታላቅነት ለማጉላትም ሊሆን ይችላል።ምንም ይሁን ግን ንግግሩ ስሕተት ነው።ወዳጄ እንደነገረኝ ይህንን ከተናገሩም በሗላ ምን ማለት እንደፈለጉ አላብራሩትም። ቤተክርስቲያን ግን እስከ ዓለም ፍጻሜ የምትሰዋው ያንኑ አንዱን የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው።ሕይወቷም እርሱ ነው።

ሁለተኛውና እኔ የገጠመኝ ደግሞ በአንድ ቤተክርስቲያን ቤተመቅደስ ውስጥ አንድ መምህር እያስተማሩ ነው። የሚያስተምሩት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ይጠብቃት ዘንድ ስለተሰጣት ስለ አረጋዊው ዮሴፍ ነበር። እና እስካሁን ባልገባኝ ከእሳቸውም ፈጽሞ በማልጠብቀው አገላለጥ "ዮሴፍ የጌታ የእንጀራ አባቱ ነው" አሉ።ዳኅፀ ልሳን ነው እንዳልል ወዲያው አላስተባበሉም።እዚያ የነበረው ብዙ ሰው መሠረታዊ የሚባል የቤተክርስቲያን ትምህርት የተማረ ነበርና ሁሉም በንግግሩ ደነገጠ። ጎን ለጎን አጉረመረመ።በዚህ መሐል አንድ ደቀመዝሙር ተነስቶ በድፍረት "አሁን የተናገሩት ስሕተት ነው" አላቸው::ከዚያ በሗላ የሆነው እዚህ ላይ አስፈላጊ ስላልሆነ ይቆይ።ዋናው ነጥብ ግን መምህሩ የተናገሩት ፍጹም ስሕተት ነበር።

እናም

አንዳንድ መምህራን ሆይ የምትናገሩትን ጠንቅቁ። ቃል ለማራቀቅ፣ በመድረክ ሙቀት በመገፋፋት፣ወይም የሆኑ አካላትን ደስ ለማሰኘት፣ ከዝግጅት ማነስ ወይም በሌላ ምክንያት ኦርቶዶክሳዊ ላሕይና መሠረት የሌለው፣ ትውፊታዊ፣ መጽሐፋዊ ያልሆነ ወይም ከአበው ያልተገኘ ጉሥዐተ ልባችሁን በቤተክርስቲያን መድረክና ዐውደ ምሕረት አትናገሩ።

እኛም ምዕመናን ሆይ ሁሌም ከዐውደ ምሕረትና ከመድረክ የሚነገረው ሁሉ ጥርት ያለ የቤተክርስቲያን ትምህርት ላይሆን ይችላል። መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት እንማር። ቤተክርስቲያንን በሕይወትም በትምህርትም እንወቃት። ከዚያ ያፈነገጠ ነገር ስንሰማ እንጠይቅ።ቤተክርስቲያን የእኛም ናትና።

ጸልዩ በእንተ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት!

👉ዮሴፍ ፍስሐ እንደጻፈው
👍21



tgoop.com/tseomm/6510
Create:
Last Update:

አንድም በአላዋቂነትና ድንቁርና፣ አንድም ነገር አማረልኝ ብለው የማይገባ ማራቀቅ ውስጥ ሲገቡ ፣አንድም ትኩረት ለመሳብ ካላቸው የትኩረት ጥማት ፣ አንድም ሆነ ብለው ልባቸውን ከውጭ እግራቸውን ከቤተክርስቲያን አጸድ ያቆሙ በሁለት ቢላዋ የሚበሉ ሰዎች፣ አንድም ሰውን ለማስደሰት የሚናገሯቸው ንግግሮች በቤተክርስቲያን ዐውደ ምሕረት የሚነገሩ ግን ደግሞ በጣም አደገኛና አንዳንዴም ኑ*ፋ*ቄ ጭምር ናቸው።

የቅድስት ቤተክርስቲያን ትምህርት ያልሆኑ፣ ከአበው ወይም ከመጻሕፍት ያልተገኙ፣ ትውፊታዊ መሠረትም የሌላቸው "ትምህርቶች" በየዐውደ ምሕረቱ መነገር ከጀመሩ ከራርመዋል። ከሰሞኑ ከአባ ገብርኤል 'ትምህርት' በተጨማሪ እኔ የገጠመኝን እና አንድ ወንድም ገጥሞት ያጫወተኝን ሁለት ታሪኮች ላንሳ።

የመጀመሪያው እና ባለፈው በጸሎተ ሐሙስ አንድ የደብር አስተዳዳሪ የተናገሩት ነው ብሎ አንድ ወንድም የነገረኝ ነወ። በቅዳሴው ወቅት ምዕመናን ሥጋ ወደሙን እየተቀበሉ አስተዳዳሪው እያስተማሩ በመሐል እንዲህ አሉ አለኝ። "የዛሬው ሥጋ ወደም እስከዛሬ ከምንቀበለው ሁሉ የተለዬ ነው።" አሉ አለ። ይህ በጣም ስሕተት ያለበት ንግግር ነው።

ቤተክርስቲያን በየዕለቱ በቅዳሴው የምትሰዋው ቅዱስ ሥጋውና ደሙ ያኔ ጌታ ለሐዋርያት ካቀበላቸው የተለየ መስዋዕት አትሰዋም። ምናልባት ሊሉ የፈለጉት ሌላ ሊሆን ይችላል። የዕለቱን ታላቅነት ለማጉላትም ሊሆን ይችላል።ምንም ይሁን ግን ንግግሩ ስሕተት ነው።ወዳጄ እንደነገረኝ ይህንን ከተናገሩም በሗላ ምን ማለት እንደፈለጉ አላብራሩትም። ቤተክርስቲያን ግን እስከ ዓለም ፍጻሜ የምትሰዋው ያንኑ አንዱን የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው።ሕይወቷም እርሱ ነው።

ሁለተኛውና እኔ የገጠመኝ ደግሞ በአንድ ቤተክርስቲያን ቤተመቅደስ ውስጥ አንድ መምህር እያስተማሩ ነው። የሚያስተምሩት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ይጠብቃት ዘንድ ስለተሰጣት ስለ አረጋዊው ዮሴፍ ነበር። እና እስካሁን ባልገባኝ ከእሳቸውም ፈጽሞ በማልጠብቀው አገላለጥ "ዮሴፍ የጌታ የእንጀራ አባቱ ነው" አሉ።ዳኅፀ ልሳን ነው እንዳልል ወዲያው አላስተባበሉም።እዚያ የነበረው ብዙ ሰው መሠረታዊ የሚባል የቤተክርስቲያን ትምህርት የተማረ ነበርና ሁሉም በንግግሩ ደነገጠ። ጎን ለጎን አጉረመረመ።በዚህ መሐል አንድ ደቀመዝሙር ተነስቶ በድፍረት "አሁን የተናገሩት ስሕተት ነው" አላቸው::ከዚያ በሗላ የሆነው እዚህ ላይ አስፈላጊ ስላልሆነ ይቆይ።ዋናው ነጥብ ግን መምህሩ የተናገሩት ፍጹም ስሕተት ነበር።

እናም

አንዳንድ መምህራን ሆይ የምትናገሩትን ጠንቅቁ። ቃል ለማራቀቅ፣ በመድረክ ሙቀት በመገፋፋት፣ወይም የሆኑ አካላትን ደስ ለማሰኘት፣ ከዝግጅት ማነስ ወይም በሌላ ምክንያት ኦርቶዶክሳዊ ላሕይና መሠረት የሌለው፣ ትውፊታዊ፣ መጽሐፋዊ ያልሆነ ወይም ከአበው ያልተገኘ ጉሥዐተ ልባችሁን በቤተክርስቲያን መድረክና ዐውደ ምሕረት አትናገሩ።

እኛም ምዕመናን ሆይ ሁሌም ከዐውደ ምሕረትና ከመድረክ የሚነገረው ሁሉ ጥርት ያለ የቤተክርስቲያን ትምህርት ላይሆን ይችላል። መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት እንማር። ቤተክርስቲያንን በሕይወትም በትምህርትም እንወቃት። ከዚያ ያፈነገጠ ነገር ስንሰማ እንጠይቅ።ቤተክርስቲያን የእኛም ናትና።

ጸልዩ በእንተ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት!

👉ዮሴፍ ፍስሐ እንደጻፈው

BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6510

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

How to Create a Private or Public Channel on Telegram? With the administration mulling over limiting access to doxxing groups, a prominent Telegram doxxing group apparently went on a "revenge spree." Ng Man-ho, a 27-year-old computer technician, was convicted last month of seven counts of incitement charges after he made use of the 100,000-member Chinese-language channel that he runs and manages to post "seditious messages," which had been shut down since August 2020. But a Telegram statement also said: "Any requests related to political censorship or limiting human rights such as the rights to free speech or assembly are not and will not be considered."
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
FROM American