TSEOMM Telegram 6436
ሂሳባዊ አእምሮ የኦርቶዶክስ አይደለም!

ብዙ ጊዜ አንድን ጉዳይ አንስተው "ይህን ባላደርግ ሲኦል እገባለሁ ማለት ነው?" ብለው የሚጠይቁ ክርስቲያኖች አሉ። ለምሳሌ " ቤ/ክ ሀዘን ላይ በነበረችበት ግዜ ጥቁር ባለመልበሴ ብቻ ስእል እገባለሀ? ሌላውን አድርጌ ግን ባልፆም እኮነናለሁ? ሌላውን የክርስትና ትዕዛዛትን ተቀብዬ ግን አንዱን ገድል ባልቀበል፣ ወይም ለአንዱ የቅዱስ ሲኖዶስ ትዕዛዝ ባልገዛ ሲኦል እገባለሁ?" ወዘተ ቀጥተኛ የፍርድ ጉዳይ አድርገው ይጠይቃሉ።

በርግጥ የጥያቄዎቹ መሠረት የተደበቀ ያልተነገረ ፍላጎት ለመሆኑ ይታወቃል። ለምሳሌ ሰው የቅዱስ ሲኖዶስን ትዕዛዝ የማያከብረው ከሃይማኖቱ የፖለቲካ አመለካከቱን ወይም ፍልስፍናውን ሲያስቀድም፣ ወይም በሌላ ትምህርት ተፅዕኖ ምክንያት ነው። በቀጥታ ደግሞ የቅዱስ ሲኖዶስን ትዕዛዝ አለማክበር ኃጥአት ነው። ጥያቄው ደግሞ "ይህ ኃጥአት ብቻ ሲኦል ያስገባኛል?" ብሎ እንደመጠየቅ ነው የሚሆነው።

ይህ ደግሞ ክርስትናን በቀመር፣ በሂሳብ፣ በስሌት መኖር ይሆናል። ይህ ሂሳባዊ አእምሮ ደግሞ የኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት መሠረታዊ ፍኖት (ካርታ) የሌለን ሲሆን የምንገባበት ጉድጓድ ነው። ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ፣ ኦርቶዶክሳዊ ሕሊና፣ ክርስቲያናዊ ልብና ሥነ-ልቦና ሳይኖረን ሲቀር የምንገኝበት የአስተሳሰብ ባህሩ ይህን ይመስላል።

በርግጥ በቅዱስ መጽሐፋችን ይህን ሂሳባዊ አእምሮ (Calculative Mind) ይዘው ኖረው የጠፉበት ሰዎች አሉ። ለምሳሌ የኖህ ዘመን ሰዎችን እንውሰድ! ለየትኛው የኖህ ትምህርት ምላሻቸው ኃጥአት የሚሰሩበትንና ለንስሃ የሚቀራቸውን ጊዜ ማስላት ነበር። የሚሠሩት ኃጥአት መሆኑን አልዘነጉም። ወደ ጥፋት ወሃም የወሰዳቸው ሂሳባዊ አእምሮአቸው ያመጣባቸው ጣጣ ነው። ለኃጥአትና ፅድቅ ጉዳይ የራስን ቀመር መሥራት፣ መቁጠርና ብልጣ ብልጥ ለመሆን መሞከር።

የይሁዳም ሕይወት ይህንኑ ያስተምረናል። ጌታችን እንደሆነ ለመሞት ነበር የመጣ። ይሁዳ ግን ጌታችንን ሲሸጥ ከሚያገኘው ትርፍ አንስቶ እራሱ ቢታነቅ ከሲኦል ነፍሳት ጋር ወደ ገነት የሚገባበትን ፍጥነት እስከማስላት የደረሰ ነበር። ውጤቱ ደግሞ የምናውቀው ነው።

ቤተክርስቲያን ላይ ብልጥ ለመሆን በጣር ቁጥር ልብና ኩላሊትን የሚመረምር አምላካችን ላይ ብልጥ ለመሆን እየሞከርን መሆኑን አንዘንጋ። ሁሉም የጮሌነት ታሪኮች በውርደት ተደምድመዋል። በማንኛውም አስተሳሰብ ውስጥ ሆነው ቤተክርስቲያን ላይ ሂሳብ የሚሰሩ ሰዎችም መጨረሻ ይኸው ነው። ባይሆን የወደቅንበትን የኃጥአት ማጥ አምነን፣ ችግሩ የራሳችን መሆኑን ተቀብለን "እርሱ በፈቀደ ጊዜ ይመልሰን " ማለቱስ ይቀላል። ለዚህም ነው ቅን ልቦና የክርስትና ውበት፣ እግዚአብሔርን የምናይባት መስታወት የሆነችው።
ቤተክርስቲያን ላይ በፍፁም ብልጥ ለመሆን አንሞክር!

አክሊሉ ደበላ እንደጻፈው
1



tgoop.com/tseomm/6436
Create:
Last Update:

ሂሳባዊ አእምሮ የኦርቶዶክስ አይደለም!

ብዙ ጊዜ አንድን ጉዳይ አንስተው "ይህን ባላደርግ ሲኦል እገባለሁ ማለት ነው?" ብለው የሚጠይቁ ክርስቲያኖች አሉ። ለምሳሌ " ቤ/ክ ሀዘን ላይ በነበረችበት ግዜ ጥቁር ባለመልበሴ ብቻ ስእል እገባለሀ? ሌላውን አድርጌ ግን ባልፆም እኮነናለሁ? ሌላውን የክርስትና ትዕዛዛትን ተቀብዬ ግን አንዱን ገድል ባልቀበል፣ ወይም ለአንዱ የቅዱስ ሲኖዶስ ትዕዛዝ ባልገዛ ሲኦል እገባለሁ?" ወዘተ ቀጥተኛ የፍርድ ጉዳይ አድርገው ይጠይቃሉ።

በርግጥ የጥያቄዎቹ መሠረት የተደበቀ ያልተነገረ ፍላጎት ለመሆኑ ይታወቃል። ለምሳሌ ሰው የቅዱስ ሲኖዶስን ትዕዛዝ የማያከብረው ከሃይማኖቱ የፖለቲካ አመለካከቱን ወይም ፍልስፍናውን ሲያስቀድም፣ ወይም በሌላ ትምህርት ተፅዕኖ ምክንያት ነው። በቀጥታ ደግሞ የቅዱስ ሲኖዶስን ትዕዛዝ አለማክበር ኃጥአት ነው። ጥያቄው ደግሞ "ይህ ኃጥአት ብቻ ሲኦል ያስገባኛል?" ብሎ እንደመጠየቅ ነው የሚሆነው።

ይህ ደግሞ ክርስትናን በቀመር፣ በሂሳብ፣ በስሌት መኖር ይሆናል። ይህ ሂሳባዊ አእምሮ ደግሞ የኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት መሠረታዊ ፍኖት (ካርታ) የሌለን ሲሆን የምንገባበት ጉድጓድ ነው። ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ፣ ኦርቶዶክሳዊ ሕሊና፣ ክርስቲያናዊ ልብና ሥነ-ልቦና ሳይኖረን ሲቀር የምንገኝበት የአስተሳሰብ ባህሩ ይህን ይመስላል።

በርግጥ በቅዱስ መጽሐፋችን ይህን ሂሳባዊ አእምሮ (Calculative Mind) ይዘው ኖረው የጠፉበት ሰዎች አሉ። ለምሳሌ የኖህ ዘመን ሰዎችን እንውሰድ! ለየትኛው የኖህ ትምህርት ምላሻቸው ኃጥአት የሚሰሩበትንና ለንስሃ የሚቀራቸውን ጊዜ ማስላት ነበር። የሚሠሩት ኃጥአት መሆኑን አልዘነጉም። ወደ ጥፋት ወሃም የወሰዳቸው ሂሳባዊ አእምሮአቸው ያመጣባቸው ጣጣ ነው። ለኃጥአትና ፅድቅ ጉዳይ የራስን ቀመር መሥራት፣ መቁጠርና ብልጣ ብልጥ ለመሆን መሞከር።

የይሁዳም ሕይወት ይህንኑ ያስተምረናል። ጌታችን እንደሆነ ለመሞት ነበር የመጣ። ይሁዳ ግን ጌታችንን ሲሸጥ ከሚያገኘው ትርፍ አንስቶ እራሱ ቢታነቅ ከሲኦል ነፍሳት ጋር ወደ ገነት የሚገባበትን ፍጥነት እስከማስላት የደረሰ ነበር። ውጤቱ ደግሞ የምናውቀው ነው።

ቤተክርስቲያን ላይ ብልጥ ለመሆን በጣር ቁጥር ልብና ኩላሊትን የሚመረምር አምላካችን ላይ ብልጥ ለመሆን እየሞከርን መሆኑን አንዘንጋ። ሁሉም የጮሌነት ታሪኮች በውርደት ተደምድመዋል። በማንኛውም አስተሳሰብ ውስጥ ሆነው ቤተክርስቲያን ላይ ሂሳብ የሚሰሩ ሰዎችም መጨረሻ ይኸው ነው። ባይሆን የወደቅንበትን የኃጥአት ማጥ አምነን፣ ችግሩ የራሳችን መሆኑን ተቀብለን "እርሱ በፈቀደ ጊዜ ይመልሰን " ማለቱስ ይቀላል። ለዚህም ነው ቅን ልቦና የክርስትና ውበት፣ እግዚአብሔርን የምናይባት መስታወት የሆነችው።
ቤተክርስቲያን ላይ በፍፁም ብልጥ ለመሆን አንሞክር!

አክሊሉ ደበላ እንደጻፈው

BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6436

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

To delete a channel with over 1,000 subscribers, you need to contact user support In the next window, choose the type of your channel. If you want your channel to be public, you need to develop a link for it. In the screenshot below, it’s ”/catmarketing.” If your selected link is unavailable, you’ll need to suggest another option. Hashtags are a fast way to find the correct information on social media. To put your content out there, be sure to add hashtags to each post. We have two intelligent tips to give you: Judge Hui described Ng as inciting others to “commit a massacre” with three posts teaching people to make “toxic chlorine gas bombs,” target police stations, police quarters and the city’s metro stations. This offence was “rather serious,” the court said. Public channels are public to the internet, regardless of whether or not they are subscribed. A public channel is displayed in search results and has a short address (link).
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
FROM American