TSEOMM Telegram 6355
1) የሞተችው ለመበስበስ ሳይኾን የትንሣኤን አካል ገንዘብ ለማድረግ ነው። ይኸውም ኢመዋቲ አካልን ገንዘብ ለማድረግ እንጂ ለመበስበስ አይደለም። ይህ ዮሐንስ ዘደማስቆ በመደነቅ የገለጸው ነው። ሰውነቷ እንዲበሰብስ ልጇ አለመፍቀዱን ሞታ መበስበስ ሳያገኛት ከልጇ ትንሣኤ በኋላ በልጇ ሥልጣን በሦስተኛው ቀን መነሣቷን ብዙዎቹ ቅዱሳን ሊቃውንት የገለጹት እና እኛም የምናምነው ነው።

2) የሞተችው ሰው ስለ ኾነች ነው። አምላክ በመውለዷ ምክንያት በሕሊናቸው ሰው አይደለችም የሚሉ ሰዎች እንዳይኖሩና በእርሷ ሰው የመኾን ጉዳይ ጥርጣሬ እንዳይፈጠር ሞትን ትቀምስ ዘንድ ልጇ ፈቅዷል። ይህ እነ አብሮኮሮስ በአጽንዖት ያስረዱት ነው። ይህ ምክንያት ቃል ሰው አልኾነም የሚለውን ክሕደትናና እርሷም ሰው አይደለችም የሚለው ስሕተት የሚያርም ነው።

3) ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ እንዳለው ያረፈችው የልጇን የሞት ጽዋ ለመቅመስ ነው። ይህም እንዲኾን የእርሱ ፈቃድ ነው።

4) ሞቷ የመሸነፍ ሳይኾን የክብር እና የድል እንደ ኾነ እንድናውቅ ነው። ይህን ለመረዳት የሞቷን ዜና ከልጇ ዘንድ የተላከው ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥራት ሲመጣ የድል ምልክት የኾነውን የዘንባባ ዝንጣፊ ይዞ መምጣቱን እነ ማክሲሞስ ተናዛዚው የቀደሙ ትውፊቶችን ማዕከል አድርገው "The Life of The Virgin" በሚለው መጽሐፍ ዘግበዋልና።

5) ሞቷ ተራ ሞት ሳይኾን በመደነቅና በመገረም የሚናገሩት ሞት ነው። ቅዱስ ያሬድ "ማትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኲሉ" - ሞትማ ለሚሞት ይገባል የማርያም ሞት ግን ለኹሉ ያስደንቃል" የሚለው ለዚህ ነው። እንደ በሥጋና በደም ኾነን በድፍረት ከመናገር ልንቆጠብና ልናደንቅ ይገባል።

ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው እንደጻፈው
👍1



tgoop.com/tseomm/6355
Create:
Last Update:

1) የሞተችው ለመበስበስ ሳይኾን የትንሣኤን አካል ገንዘብ ለማድረግ ነው። ይኸውም ኢመዋቲ አካልን ገንዘብ ለማድረግ እንጂ ለመበስበስ አይደለም። ይህ ዮሐንስ ዘደማስቆ በመደነቅ የገለጸው ነው። ሰውነቷ እንዲበሰብስ ልጇ አለመፍቀዱን ሞታ መበስበስ ሳያገኛት ከልጇ ትንሣኤ በኋላ በልጇ ሥልጣን በሦስተኛው ቀን መነሣቷን ብዙዎቹ ቅዱሳን ሊቃውንት የገለጹት እና እኛም የምናምነው ነው።

2) የሞተችው ሰው ስለ ኾነች ነው። አምላክ በመውለዷ ምክንያት በሕሊናቸው ሰው አይደለችም የሚሉ ሰዎች እንዳይኖሩና በእርሷ ሰው የመኾን ጉዳይ ጥርጣሬ እንዳይፈጠር ሞትን ትቀምስ ዘንድ ልጇ ፈቅዷል። ይህ እነ አብሮኮሮስ በአጽንዖት ያስረዱት ነው። ይህ ምክንያት ቃል ሰው አልኾነም የሚለውን ክሕደትናና እርሷም ሰው አይደለችም የሚለው ስሕተት የሚያርም ነው።

3) ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ እንዳለው ያረፈችው የልጇን የሞት ጽዋ ለመቅመስ ነው። ይህም እንዲኾን የእርሱ ፈቃድ ነው።

4) ሞቷ የመሸነፍ ሳይኾን የክብር እና የድል እንደ ኾነ እንድናውቅ ነው። ይህን ለመረዳት የሞቷን ዜና ከልጇ ዘንድ የተላከው ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥራት ሲመጣ የድል ምልክት የኾነውን የዘንባባ ዝንጣፊ ይዞ መምጣቱን እነ ማክሲሞስ ተናዛዚው የቀደሙ ትውፊቶችን ማዕከል አድርገው "The Life of The Virgin" በሚለው መጽሐፍ ዘግበዋልና።

5) ሞቷ ተራ ሞት ሳይኾን በመደነቅና በመገረም የሚናገሩት ሞት ነው። ቅዱስ ያሬድ "ማትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኲሉ" - ሞትማ ለሚሞት ይገባል የማርያም ሞት ግን ለኹሉ ያስደንቃል" የሚለው ለዚህ ነው። እንደ በሥጋና በደም ኾነን በድፍረት ከመናገር ልንቆጠብና ልናደንቅ ይገባል።

ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው እንደጻፈው

BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6355

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

The Standard Channel Some Telegram Channels content management tips During the meeting with TSE Minister Edson Fachin, Perekopsky also mentioned the TSE channel on the platform as one of the firm's key success stories. Launched as part of the company's commitments to tackle the spread of fake news in Brazil, the verified channel has attracted more than 184,000 members in less than a month. Avoid compound hashtags that consist of several words. If you have a hashtag like #marketingnewsinusa, split it into smaller hashtags: “#marketing, #news, #usa. While the character limit is 255, try to fit into 200 characters. This way, users will be able to take in your text fast and efficiently. Reveal the essence of your channel and provide contact information. For example, you can add a bot name, link to your pricing plans, etc.
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
FROM American