TSEOMM Telegram 6314
እነዚህ አጋጣሚዎች ለእኔ እጅግ አስተማሪዎች ነበሩ። እውነት ለመናገር ስለሌሎች ከመናገር በፊት እነዚያ አካላት የሚሉትን በትክክል ማወቅ በእጂጉ አስፈላጊ መሆኑንና ስለተለያዩ ብቻ እያነሡ መለጠፍ፣ እንደ ልብ መናገር በጣም አደገኛ መሆኑን የተማርሁት ይህን ከመሰሉ ስለእኛ ከተነገሩ እጂግ የተሳሳቱ ትምህርቶች ፣ ጽሑፎች እና አመለካከቶች ነው። ከዚያም ወዲህ ትላልቅ የሚባሉት የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት ጽሑፎች ውስጥ ሳይቀር ይህን የመሰለውን ስለእኛ ያላቸውን የተሳሳተ እምነታቸውን ሳይ በእጂጉ አዝናለሁ፤ በዚያ ምክንያትም የሥራዎቻቸውን ደኅና ነገር ሁሉ በዚያው ዓይን እያየሁ እንድጠራጠራቸው እሆናለሁ።

ይህን ሁኔታ በሌሎችም አይቻለሁ። በተለይ በእስልምናው ሐዲዝ ላይ እኛን መነኮሳቶቻቸውንና ሊቃውንቶቻቸውን ያመልካሉ ብለው የጻፉት ሁልጊዜ ሲያስቀኝ እና ሲያስገርመኝ ይኖራል። እንዲህ ያለው ችግር በርግጥ በእኛም ዘንድ አለ። በተለይ ካቶሊኮች እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚለው አሳፋሪ ነገር እስካሁንም የሚናገሩት ሞኞች አሉ። በነገራችን ላይ ለእመቤታችን ወላጆች በተለይም ለቅድስት ሀና ብዙ ቤተ ክርስቲያን በመሰየም የካቶሊኮችን ያህል የሚኖር አይመስለኝም። ተመልከቱ እንግዲህ ይህ ሁሉ ባለበት ነው እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚል የስሚ ስሚ ወሬን በአደባባይ ሳይቀር በድፍረት እንናገር የነበረው።

ዋናው የፈለግሁት ነገር ሌሎች እኛ ያልሆንነውን ብለዋል ሲሉ እኛን የሚሰማንን ያህል ወይም ከዚያም በላይ የናም የግምት ንግግር ሌሎቹንም ልክ እንደእኛ እንዲሰማቸው ያደርጋል። በግሌ ስለሌሎች በድፍረት መናገር ምን ያህል ስሐተት እንደሆነ እና እኔን የእነርሱ ደጋግሞ እንደሚያሳዝነኝ እነርሱንም የእኛ እንዲህ ሊያደርጋቸው እንደሚችል እና ስለማንኛውም አካል ስለምንናገረው ነገር በእጂጉ መጠንቀቅ እንዳለብኝ የተማርኩት ከእነዚህ አጋጣሚዎች ነበር።
የሚያሳዝነው ግን አሁንም እየሆነ ያለው እንደዚያው መሆኑ ነው። አሁንም ሰዎች ራሳቸው ስለሚያምኑት ነገር ከሰዎቹ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የሚያምኑት እያሉ መናግር እጂግ በጣም አደገኛ ስሕተት ነው። የተጠራጠረ ሰው ማድረግ ያለበት መጠየቅ ነው። ከዚያ ራሳቸው የተጠየቁት አካላት እምነታቸውን አስተሳሰባቸውን አረዳዳቸውን በግልጽ ያስረዱ። እዚይ ላይ ምን ለማለት እንደፈለጉ ደጋግሞ እየጠየቁ ማጣራት እና በትክክል መረዳት መቅደም አለበት ። ካለበለዚያ ዲዮስቆሮስ አውጣኪያዊ ነው ብለው እስካሁን በስሕተት እንደሚያምኑት እና ስለማናምነው ነገር ከእኛ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የምታምኑት እንደሚሉን አንዳንድ ምሥራቃውያን ከመሆን የዘለለ ጠቀሜታ የለውም።

✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
👍5



tgoop.com/tseomm/6314
Create:
Last Update:

እነዚህ አጋጣሚዎች ለእኔ እጅግ አስተማሪዎች ነበሩ። እውነት ለመናገር ስለሌሎች ከመናገር በፊት እነዚያ አካላት የሚሉትን በትክክል ማወቅ በእጂጉ አስፈላጊ መሆኑንና ስለተለያዩ ብቻ እያነሡ መለጠፍ፣ እንደ ልብ መናገር በጣም አደገኛ መሆኑን የተማርሁት ይህን ከመሰሉ ስለእኛ ከተነገሩ እጂግ የተሳሳቱ ትምህርቶች ፣ ጽሑፎች እና አመለካከቶች ነው። ከዚያም ወዲህ ትላልቅ የሚባሉት የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት ጽሑፎች ውስጥ ሳይቀር ይህን የመሰለውን ስለእኛ ያላቸውን የተሳሳተ እምነታቸውን ሳይ በእጂጉ አዝናለሁ፤ በዚያ ምክንያትም የሥራዎቻቸውን ደኅና ነገር ሁሉ በዚያው ዓይን እያየሁ እንድጠራጠራቸው እሆናለሁ።

ይህን ሁኔታ በሌሎችም አይቻለሁ። በተለይ በእስልምናው ሐዲዝ ላይ እኛን መነኮሳቶቻቸውንና ሊቃውንቶቻቸውን ያመልካሉ ብለው የጻፉት ሁልጊዜ ሲያስቀኝ እና ሲያስገርመኝ ይኖራል። እንዲህ ያለው ችግር በርግጥ በእኛም ዘንድ አለ። በተለይ ካቶሊኮች እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚለው አሳፋሪ ነገር እስካሁንም የሚናገሩት ሞኞች አሉ። በነገራችን ላይ ለእመቤታችን ወላጆች በተለይም ለቅድስት ሀና ብዙ ቤተ ክርስቲያን በመሰየም የካቶሊኮችን ያህል የሚኖር አይመስለኝም። ተመልከቱ እንግዲህ ይህ ሁሉ ባለበት ነው እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚል የስሚ ስሚ ወሬን በአደባባይ ሳይቀር በድፍረት እንናገር የነበረው።

ዋናው የፈለግሁት ነገር ሌሎች እኛ ያልሆንነውን ብለዋል ሲሉ እኛን የሚሰማንን ያህል ወይም ከዚያም በላይ የናም የግምት ንግግር ሌሎቹንም ልክ እንደእኛ እንዲሰማቸው ያደርጋል። በግሌ ስለሌሎች በድፍረት መናገር ምን ያህል ስሐተት እንደሆነ እና እኔን የእነርሱ ደጋግሞ እንደሚያሳዝነኝ እነርሱንም የእኛ እንዲህ ሊያደርጋቸው እንደሚችል እና ስለማንኛውም አካል ስለምንናገረው ነገር በእጂጉ መጠንቀቅ እንዳለብኝ የተማርኩት ከእነዚህ አጋጣሚዎች ነበር።
የሚያሳዝነው ግን አሁንም እየሆነ ያለው እንደዚያው መሆኑ ነው። አሁንም ሰዎች ራሳቸው ስለሚያምኑት ነገር ከሰዎቹ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የሚያምኑት እያሉ መናግር እጂግ በጣም አደገኛ ስሕተት ነው። የተጠራጠረ ሰው ማድረግ ያለበት መጠየቅ ነው። ከዚያ ራሳቸው የተጠየቁት አካላት እምነታቸውን አስተሳሰባቸውን አረዳዳቸውን በግልጽ ያስረዱ። እዚይ ላይ ምን ለማለት እንደፈለጉ ደጋግሞ እየጠየቁ ማጣራት እና በትክክል መረዳት መቅደም አለበት ። ካለበለዚያ ዲዮስቆሮስ አውጣኪያዊ ነው ብለው እስካሁን በስሕተት እንደሚያምኑት እና ስለማናምነው ነገር ከእኛ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የምታምኑት እንደሚሉን አንዳንድ ምሥራቃውያን ከመሆን የዘለለ ጠቀሜታ የለውም።

✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ

BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6314

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Telegram Android app: Open the chats list, click the menu icon and select “New Channel.” How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) Telegram users themselves will be able to flag and report potentially false content. The Channel name and bio must be no more than 255 characters long A Hong Kong protester with a petrol bomb. File photo: Dylan Hollingsworth/HKFP.
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
FROM American