TSEOMM Telegram 6290
በሰሞኑ ጉዳይ
--
#የተደነቅሁባቸው
ከ‹‹ታማልዳለች አታማልድም›› የፌርማታ ነዋሪ ነባሪ ንትርክ ሻገር ያለ ሐሳብ ያነሣ አዲስ ትውልድ በማየቴ ደስ ብሎኛል፡፡ ምሥጢራት ላይ በመሠረታዊነት ደክመዋል፡፡ ‹‹አምስቱ ብቻዎች››ን የሚሞግቱበት መንገድ ደንቆኛል፡፡ የተዋሥኦ ባሕል አነቃቅተዋል፡፡ ያ ሜዳ የዝነኞችና የአርቲስቶች የብቻ ርስት እንዳይሆን እጃቸው አለበት፡፡ ስለ ቅዳሴ ስለ ጸሎት ሕይወት ደጋግመው ይናገራሉ፡፡ መልካም ነው፡፡
--
#ቅሬታዬ
አቀራረብ ላይ አብዝተው ቀሊልና ዋዘኛ አቀራረብን ይከተላሉ፡፡ ለኦርቶዶክሳዊው አድማጭ የሌላ ቤት ዘዬ ተደርገው የሚወሰዱ ቋንቋዎችንና ዘይቤዎችን ይጠቀማሉ፡፡ መጽሐፍ ላይ ስለሌሉ አይደለም፡፡ ግን በቃ … ቃላቱ በአሉታ ተዛምደዋል፡፡ የሆነ ዓይነት sensitivity ያስፈልጋል፡፡ አከራካሪ ጉዳዮች ላይ ውሳኔውን ወደ መምህራን ማሳለፍ፣ ከዚያም የእነሱን ምላሽ ይዞ መቅረብ የተሻለ ነው፡፡ ቤቱ ‹‹ምስክር መምህራን›› የሚባሉ ሊቃውንት አሉበት፡፡ ገርበብ አድርጎ ማለፍም አንድ ነገር ነው፡፡ እንዲህ የሚል አለ፣ እንዲህም የሚል አለና በጋራ እንጠይቅ፣ አንብበን ጠይቀን እንገናኝ ብሎ ረዘም ያለ ቀጠሮ መውሰድም ፈሊጥ ነው፡፡ ግብግብ ይጎዳል፣ ልጅ ሲሆኑ ደግሞ መቀጨትም ያመጣል፡፡ እዚህ ላይ በማልጠብቀው መልኩ አንድን አከራካሪ ርእስ በራስ ሐሳብ ዙሪያ ብቻ በማሽከርከር ‹‹ግግም!›› ማለትን አያለሁ፡፡ ያደክማል! ጊዜ ይፍታው ብሎ ማሰለፍምኮ አለ፡፡ ኃፊረ ገጽ የተለየው ድርቅ ያለ የአደባባይ ድግግሞሽ አያንጽም፡፡ የኢኦተቤክ በትምህርተ ሃይማኖት ምንጭ ረገድ ያላት አብነትነት የአኃትን ማረጋገጫ የሚፈልግ የሚያስመስል ጥንቃቄ የጎደለው አቀራረብም ያስቆጣል፡፡ በዚህ ቅር ይለኛል፡፡
--
#ሌላው_ቅሬታዬ
በቀጥታም በተዘዋዋሪም የዕቅበተ እምነት ሥራ የቲዎሎጂና የአብነት መምህራን ሥራ ብቻ እንደሆነ ተደርጎ መቅረቡ ትክክል ሆኖ አይታየኝም፡፡ ያለፉት ዓመታት ተጋድሎም ያንን አያሳይም፡፡ ካህናትም. ሰንበት ት/ቤቶችም፣ ማኅበራትም፣ ሰንበቴዎችም፣ ምዕመናን/ትም ድርሻ አላቸው፡፡ ባይሆን እንደ ሰሞኑ ዓይነት አካራካሪ የሆነ፣ ማብራሪያ የሚፈልግ፣ ትርጓሜ የሚያሻው ንባብ ሲገጥም የወንበር መምህራንን ማናገር ይገባል ቢባል የቀና ነው፡፡ እንደ እውነቱ አልፎ አልፎ ብቅ የሚለው ልጆቹ በጉባኤ አልዋሉም በሚል የሚሰነዝር ምሁራዊ ትምክሕት (Clericalism) የተጫነው አነጋገር የሚጎዳ እንጂ የሚጠቅም አይደለም፡፡ አሁንም በፍቅርና በርኅራኄ አቅርቦ መያዝንና ማረቅን ሳይሆን በ‹‹ብለን ነበር›› የታጀበ የኃይለ ቃል ውርወራችን ያስጨንቃል፡፡
--
#መውጫ
አሁንም ጊዜና ዕድል አለ፡፡ ንግግሮች በውስጥ ይቀጥሉ፡፡ የአሸናፊ ተሸናፊና የነጥብ ማስቆጠሪያ ቅኝቶች ይርገቡ፡፡ ሰብእና ተኮር ነቀፋዎች ይወገዱ፡፡ የተነሡት ርእሶች ወደ ጉባኤ መምህራን ይሄዱ፣ የእነሱ ቃል እስኪሰማ ያጨቃጨቁት አርእስት ከዲጂታል ሚዲያ ተዋሥኦ ዕረፍት ያግኙ፡፡ ሰሚዎች የሰማንበት መንገድና እነርሱ የሚያብራሩበት መንገድ መካከል ክፍተት ካለ ይፈተሽ፣ ያሉበትን ነጥብ ያብራሩ፡፡ ነጥቡ ይንጠር፡፡ በጉባኤ ቤት ሰዎች እልባት ይሰጥ፣ በዚያውም በፕላትፎርሙ ላይ በምን ርእስና እንዴት እንወያይ የሚለው ይታይ፡፡ ከሁሉም በላይ ግን አንዳችን ለሌላችን ጸሎት እናድርግ!

✍️በአማን ነጸረ እንደጻፈው
2



tgoop.com/tseomm/6290
Create:
Last Update:

በሰሞኑ ጉዳይ
--
#የተደነቅሁባቸው
ከ‹‹ታማልዳለች አታማልድም›› የፌርማታ ነዋሪ ነባሪ ንትርክ ሻገር ያለ ሐሳብ ያነሣ አዲስ ትውልድ በማየቴ ደስ ብሎኛል፡፡ ምሥጢራት ላይ በመሠረታዊነት ደክመዋል፡፡ ‹‹አምስቱ ብቻዎች››ን የሚሞግቱበት መንገድ ደንቆኛል፡፡ የተዋሥኦ ባሕል አነቃቅተዋል፡፡ ያ ሜዳ የዝነኞችና የአርቲስቶች የብቻ ርስት እንዳይሆን እጃቸው አለበት፡፡ ስለ ቅዳሴ ስለ ጸሎት ሕይወት ደጋግመው ይናገራሉ፡፡ መልካም ነው፡፡
--
#ቅሬታዬ
አቀራረብ ላይ አብዝተው ቀሊልና ዋዘኛ አቀራረብን ይከተላሉ፡፡ ለኦርቶዶክሳዊው አድማጭ የሌላ ቤት ዘዬ ተደርገው የሚወሰዱ ቋንቋዎችንና ዘይቤዎችን ይጠቀማሉ፡፡ መጽሐፍ ላይ ስለሌሉ አይደለም፡፡ ግን በቃ … ቃላቱ በአሉታ ተዛምደዋል፡፡ የሆነ ዓይነት sensitivity ያስፈልጋል፡፡ አከራካሪ ጉዳዮች ላይ ውሳኔውን ወደ መምህራን ማሳለፍ፣ ከዚያም የእነሱን ምላሽ ይዞ መቅረብ የተሻለ ነው፡፡ ቤቱ ‹‹ምስክር መምህራን›› የሚባሉ ሊቃውንት አሉበት፡፡ ገርበብ አድርጎ ማለፍም አንድ ነገር ነው፡፡ እንዲህ የሚል አለ፣ እንዲህም የሚል አለና በጋራ እንጠይቅ፣ አንብበን ጠይቀን እንገናኝ ብሎ ረዘም ያለ ቀጠሮ መውሰድም ፈሊጥ ነው፡፡ ግብግብ ይጎዳል፣ ልጅ ሲሆኑ ደግሞ መቀጨትም ያመጣል፡፡ እዚህ ላይ በማልጠብቀው መልኩ አንድን አከራካሪ ርእስ በራስ ሐሳብ ዙሪያ ብቻ በማሽከርከር ‹‹ግግም!›› ማለትን አያለሁ፡፡ ያደክማል! ጊዜ ይፍታው ብሎ ማሰለፍምኮ አለ፡፡ ኃፊረ ገጽ የተለየው ድርቅ ያለ የአደባባይ ድግግሞሽ አያንጽም፡፡ የኢኦተቤክ በትምህርተ ሃይማኖት ምንጭ ረገድ ያላት አብነትነት የአኃትን ማረጋገጫ የሚፈልግ የሚያስመስል ጥንቃቄ የጎደለው አቀራረብም ያስቆጣል፡፡ በዚህ ቅር ይለኛል፡፡
--
#ሌላው_ቅሬታዬ
በቀጥታም በተዘዋዋሪም የዕቅበተ እምነት ሥራ የቲዎሎጂና የአብነት መምህራን ሥራ ብቻ እንደሆነ ተደርጎ መቅረቡ ትክክል ሆኖ አይታየኝም፡፡ ያለፉት ዓመታት ተጋድሎም ያንን አያሳይም፡፡ ካህናትም. ሰንበት ት/ቤቶችም፣ ማኅበራትም፣ ሰንበቴዎችም፣ ምዕመናን/ትም ድርሻ አላቸው፡፡ ባይሆን እንደ ሰሞኑ ዓይነት አካራካሪ የሆነ፣ ማብራሪያ የሚፈልግ፣ ትርጓሜ የሚያሻው ንባብ ሲገጥም የወንበር መምህራንን ማናገር ይገባል ቢባል የቀና ነው፡፡ እንደ እውነቱ አልፎ አልፎ ብቅ የሚለው ልጆቹ በጉባኤ አልዋሉም በሚል የሚሰነዝር ምሁራዊ ትምክሕት (Clericalism) የተጫነው አነጋገር የሚጎዳ እንጂ የሚጠቅም አይደለም፡፡ አሁንም በፍቅርና በርኅራኄ አቅርቦ መያዝንና ማረቅን ሳይሆን በ‹‹ብለን ነበር›› የታጀበ የኃይለ ቃል ውርወራችን ያስጨንቃል፡፡
--
#መውጫ
አሁንም ጊዜና ዕድል አለ፡፡ ንግግሮች በውስጥ ይቀጥሉ፡፡ የአሸናፊ ተሸናፊና የነጥብ ማስቆጠሪያ ቅኝቶች ይርገቡ፡፡ ሰብእና ተኮር ነቀፋዎች ይወገዱ፡፡ የተነሡት ርእሶች ወደ ጉባኤ መምህራን ይሄዱ፣ የእነሱ ቃል እስኪሰማ ያጨቃጨቁት አርእስት ከዲጂታል ሚዲያ ተዋሥኦ ዕረፍት ያግኙ፡፡ ሰሚዎች የሰማንበት መንገድና እነርሱ የሚያብራሩበት መንገድ መካከል ክፍተት ካለ ይፈተሽ፣ ያሉበትን ነጥብ ያብራሩ፡፡ ነጥቡ ይንጠር፡፡ በጉባኤ ቤት ሰዎች እልባት ይሰጥ፣ በዚያውም በፕላትፎርሙ ላይ በምን ርእስና እንዴት እንወያይ የሚለው ይታይ፡፡ ከሁሉም በላይ ግን አንዳችን ለሌላችን ጸሎት እናድርግ!

✍️በአማን ነጸረ እንደጻፈው

BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu




Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6290

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

A new window will come up. Enter your channel name and bio. (See the character limits above.) Click “Create.” The best encrypted messaging apps Hashtags are a fast way to find the correct information on social media. To put your content out there, be sure to add hashtags to each post. We have two intelligent tips to give you: Private channels are only accessible to subscribers and don’t appear in public searches. To join a private channel, you need to receive a link from the owner (administrator). A private channel is an excellent solution for companies and teams. You can also use this type of channel to write down personal notes, reflections, etc. By the way, you can make your private channel public at any moment. Choose quality over quantity. Remember that one high-quality post is better than five short publications of questionable value.
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
FROM American