TSEOMM Telegram 6277
እመቤታችን ጥንተ አብሶ የለባትም!!!

አምላክን በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ከአዳም ዘር የተላለፈ ኃጢያት (ጥንተ አብሶ ያላገኛት)፣ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለባት፣ ከመውለዷ አስቀድሞ በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር የነበረች፣ በሰው ልማድና ጠባይ ከሚደርሰው ሥጋዊ ሀሳብና ፈቃድ ሁሉ የተጠበቀች፣ከተለዩ የተለየች፣ ንጽሕት ቅድስተ ቅዱሳን ናት። መኃ 4፥7 ምልዕተ ጸጋ፣ምልዕተ ክብር ሆይ ደስ ይበልሽ!ተብላ በመላእክት አንደበት በቅድስናዋ ትመሰገናለች
ሉቃ 1፥28-30።እመቤታችን በውስጥ በአፍአ
በነፍስ በሥጋ ቅድስት ስለሆነች እግዚአብሔር ለልጁ ማደሪያ መርጧታል።

አምላክን ለመውለድ፣ ያስመረጣት፣ ያበቃት፣ ድንግልናዋ ንጽሕናዋ ነው። ንጽሐ ሥጋ፣ ንጽሐ ነፍስ፣ ንጽሐ ልቡና ለእመቤታችን ገንዘቦቿ ናቸው።

እንዲያው ለመሆኑ መንፈስ ቅዱስ ዐቀባ እምከርሠ እማ (መንፈስ ቅዱስ ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ጠበቃት) የሚለው ምንድን ነው? በሉቃ 1፥28-38 ያሉትን የቅዱስ ገብርኤል ብሥራታዊ ቃላት በኃላፊና በትንቢት የግስ ዐመላቸው በመዘርዘር የዐቀባን መሠረትነት ያስረግጣሉ። ጸጋን የተመላሽ ሆይ የሚለው ቃል በኃላፊ (past tense) እንጅ በትንቢት (future tense) አልተነገረም፣ ማለትም ወደፊት ጸጋን ይሞላብሻል፣ ከሴቶችም ሁሉ የተባረክሽ ትሆኛለሽ አላላትም። እንደገና መልአኩ በሰላምታው መደንገጧን አይቶ ማርያም ሆይ
በእግዚአብሔር ፊት ጸጋን አግኝተሻል አትፍሪ
አላት። አሁንም የመላአኩ ማረጋጊያ ዐረፍተ ነገር ኃላፊ እንጅ ትንቢት አይደለም፣ አግኝተሻል
አላት እንጅ ወደፊት ታገኛለሽ አላላትም። ይህ ሁሉ የሚያሳየው ከመፀነሷ በፊት ወይም ወደዚህ ዓለም ከመምጣቷ በፊት ጀምሮ መርገመ ሥጋ፣ መርገመ ነፍስ ያልነበረባት መሆኑን ያሳያል።
ኤርምያስን በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሸሃለሁ ኤር1፥5 ሲል ለነቢይነት ለመረጠው ኤርምያስ ይህን ያህል ክብር የሰጠ አምላክ ለእናትነት የመረጣትን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምን ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ አንጽቶ ቀድሶ ለመጠበቅ ምን ይሳነዋል?
ከቅዳሴ ማርያም ንጽሕናሽን ባወቀ ጌዜ መልአኩን ላከ አለ እንጅ ሊያነጻሽ መልአኩን ላከ አላለም።ቅዱስ ኤራቅሊስ በሃይማኖት አበው የዮሴፍ የእመቤታችን ንጽሕና አለመረዳት ሲገልጽ "ከንጹሕ ዘር የተፈጠረች
ድንግል የእግዚአብሔር ማደሪያ እንድትሆን
አላወቀም።ቅዱስ ቄርሎስ በሥጋ ከመጀመሪያው ሰው ከአዳም፣ከአብርሃም፣ከዳዊት፣ከተገኘ ባሕሪይም ኃጢያት የሌለበት በነፍስ በሥጋም
ፍጹም የሆነ አካልን ሊዋሐደው ፈጠረ እንደሚል በመጥቀስ የእመቤታችን ንጽሕና ጥንቱን በማኅፀነ ሀና ስትፈጠር ከጽንሰቷ ጀምሮ እንጂ ከመልአኩ ብሥራት ወዲህ እንዳልሆነ ልብ ማለት ያስፈልጋል።
ለእናትነት የመረጣት ማደሪያውን ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ከኃጢያት፣ከርኩሰት ከእድፈት፣ሁሉ ጠብቋታል።የሰው ልጆች የተያዙበት በአዳም በደል ወይም በራሳቸው በደል ምክኒያት የረከሱበት የኃጢያት ቅሬት መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የለባትም አላገኛትም።ምክኒያቱም እርሱ ለራሱ ማደሪያ
አድርጎ ስለመረጣት ነው።
እመቤታችን ቅድመ ዓለም በአምላክ ኅሊና ታስባ የኖረች፣የአዳም ኃጢያት ያልነካት፣ለአዳም ድኅነት ምክኒያት የሆነች፣ንጽሕተ ንጹሐን፣ቅድስተ ቅዱሳን፣በመሆኗ በሥጋም በነፍስም ፍጽምት
ትባላለች።ፍጽምት ማለት እንከን እና ጉድለት
የሌለበት ማለት ነው።ስለዚህ ቅድስት ድንግል
ማርያም የአዳም ኃጢያት የሌለባት በሥጋም
በነፍስም ንጽሕት በመሆንዋ መንፈስ ቅዱስ
ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ያ!በዘር የሚተላለፍ የመጀመሪያ በደል ፣ጥፋት ወደርሷ እንዳይተላለፍ ጠብቋታል።ሉቃ 1፥28፤መኃ 4፥12።
© መ/ር ፍሬው እውነቱ።
4👍1



tgoop.com/tseomm/6277
Create:
Last Update:

እመቤታችን ጥንተ አብሶ የለባትም!!!

አምላክን በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ከአዳም ዘር የተላለፈ ኃጢያት (ጥንተ አብሶ ያላገኛት)፣ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለባት፣ ከመውለዷ አስቀድሞ በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖር የነበረች፣ በሰው ልማድና ጠባይ ከሚደርሰው ሥጋዊ ሀሳብና ፈቃድ ሁሉ የተጠበቀች፣ከተለዩ የተለየች፣ ንጽሕት ቅድስተ ቅዱሳን ናት። መኃ 4፥7 ምልዕተ ጸጋ፣ምልዕተ ክብር ሆይ ደስ ይበልሽ!ተብላ በመላእክት አንደበት በቅድስናዋ ትመሰገናለች
ሉቃ 1፥28-30።እመቤታችን በውስጥ በአፍአ
በነፍስ በሥጋ ቅድስት ስለሆነች እግዚአብሔር ለልጁ ማደሪያ መርጧታል።

አምላክን ለመውለድ፣ ያስመረጣት፣ ያበቃት፣ ድንግልናዋ ንጽሕናዋ ነው። ንጽሐ ሥጋ፣ ንጽሐ ነፍስ፣ ንጽሐ ልቡና ለእመቤታችን ገንዘቦቿ ናቸው።

እንዲያው ለመሆኑ መንፈስ ቅዱስ ዐቀባ እምከርሠ እማ (መንፈስ ቅዱስ ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ጠበቃት) የሚለው ምንድን ነው? በሉቃ 1፥28-38 ያሉትን የቅዱስ ገብርኤል ብሥራታዊ ቃላት በኃላፊና በትንቢት የግስ ዐመላቸው በመዘርዘር የዐቀባን መሠረትነት ያስረግጣሉ። ጸጋን የተመላሽ ሆይ የሚለው ቃል በኃላፊ (past tense) እንጅ በትንቢት (future tense) አልተነገረም፣ ማለትም ወደፊት ጸጋን ይሞላብሻል፣ ከሴቶችም ሁሉ የተባረክሽ ትሆኛለሽ አላላትም። እንደገና መልአኩ በሰላምታው መደንገጧን አይቶ ማርያም ሆይ
በእግዚአብሔር ፊት ጸጋን አግኝተሻል አትፍሪ
አላት። አሁንም የመላአኩ ማረጋጊያ ዐረፍተ ነገር ኃላፊ እንጅ ትንቢት አይደለም፣ አግኝተሻል
አላት እንጅ ወደፊት ታገኛለሽ አላላትም። ይህ ሁሉ የሚያሳየው ከመፀነሷ በፊት ወይም ወደዚህ ዓለም ከመምጣቷ በፊት ጀምሮ መርገመ ሥጋ፣ መርገመ ነፍስ ያልነበረባት መሆኑን ያሳያል።
ኤርምያስን በሆድ ሳልሰራህ አውቄሃለሁ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሸሃለሁ ኤር1፥5 ሲል ለነቢይነት ለመረጠው ኤርምያስ ይህን ያህል ክብር የሰጠ አምላክ ለእናትነት የመረጣትን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያምን ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ አንጽቶ ቀድሶ ለመጠበቅ ምን ይሳነዋል?
ከቅዳሴ ማርያም ንጽሕናሽን ባወቀ ጌዜ መልአኩን ላከ አለ እንጅ ሊያነጻሽ መልአኩን ላከ አላለም።ቅዱስ ኤራቅሊስ በሃይማኖት አበው የዮሴፍ የእመቤታችን ንጽሕና አለመረዳት ሲገልጽ "ከንጹሕ ዘር የተፈጠረች
ድንግል የእግዚአብሔር ማደሪያ እንድትሆን
አላወቀም።ቅዱስ ቄርሎስ በሥጋ ከመጀመሪያው ሰው ከአዳም፣ከአብርሃም፣ከዳዊት፣ከተገኘ ባሕሪይም ኃጢያት የሌለበት በነፍስ በሥጋም
ፍጹም የሆነ አካልን ሊዋሐደው ፈጠረ እንደሚል በመጥቀስ የእመቤታችን ንጽሕና ጥንቱን በማኅፀነ ሀና ስትፈጠር ከጽንሰቷ ጀምሮ እንጂ ከመልአኩ ብሥራት ወዲህ እንዳልሆነ ልብ ማለት ያስፈልጋል።
ለእናትነት የመረጣት ማደሪያውን ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ከኃጢያት፣ከርኩሰት ከእድፈት፣ሁሉ ጠብቋታል።የሰው ልጆች የተያዙበት በአዳም በደል ወይም በራሳቸው በደል ምክኒያት የረከሱበት የኃጢያት ቅሬት መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የለባትም አላገኛትም።ምክኒያቱም እርሱ ለራሱ ማደሪያ
አድርጎ ስለመረጣት ነው።
እመቤታችን ቅድመ ዓለም በአምላክ ኅሊና ታስባ የኖረች፣የአዳም ኃጢያት ያልነካት፣ለአዳም ድኅነት ምክኒያት የሆነች፣ንጽሕተ ንጹሐን፣ቅድስተ ቅዱሳን፣በመሆኗ በሥጋም በነፍስም ፍጽምት
ትባላለች።ፍጽምት ማለት እንከን እና ጉድለት
የሌለበት ማለት ነው።ስለዚህ ቅድስት ድንግል
ማርያም የአዳም ኃጢያት የሌለባት በሥጋም
በነፍስም ንጽሕት በመሆንዋ መንፈስ ቅዱስ
ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ያ!በዘር የሚተላለፍ የመጀመሪያ በደል ፣ጥፋት ወደርሷ እንዳይተላለፍ ጠብቋታል።ሉቃ 1፥28፤መኃ 4፥12።
© መ/ር ፍሬው እውነቱ።

BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6277

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

The best encrypted messaging apps 5Telegram Channel avatar size/dimensions Other crimes that the SUCK Channel incited under Ng’s watch included using corrosive chemicals to make explosives and causing grievous bodily harm with intent. The court also found Ng responsible for calling on people to assist protesters who clashed violently with police at several universities in November 2019. It’s yet another bloodbath on Satoshi Street. As of press time, Bitcoin (BTC) and the broader cryptocurrency market have corrected another 10 percent amid a massive sell-off. Ethereum (EHT) is down a staggering 15 percent moving close to $1,000, down more than 42 percent on the weekly chart. With Bitcoin down 30% in the past week, some crypto traders have taken to Telegram to “voice” their feelings.
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
FROM American