tgoop.com/tseomm/6265
Last Update:
አንዳንድ ነገሮች (ከራሳችን ጋር ሆነን በጽሙና ብናስብባቸው)
1. ኑ*ፋ*ቄ (heresy) እና ስህተት (error) አንድ ናቸው? አንድ ካልሆኑስ ልዩነታቸውን እንዴት እንረዳዋለን? ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ ውስጥ ለሁለቱም በምን ዓይነት ሁኔታ መልስ ስትሰጥ ኖረች?
2. አንድን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት "የቤተ ክርስቲያን ነው" የሚያስብለው ወይም "ይህ የሊቅ አስተያየት ብቻ ነው" የሚያሰኘው ምንድነው? ከዚህ አንጻር የተቀደሰው ትውፊት ድርሻ (ሥልጣን) እስከምን ድረስ ነው?
3. የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በአብነት ጉባኤያት መማር እና በነገረ መለኮት ትምህርት ቤቶች መማር የትምህርት አቀራረብ ስልት ነው ወይስ በራሱ "የትምህርት ይዘት" ነው? ስልት ከሆነስ "ፍጹም" የሚባል አቀራረብ አለ? ሁለቱም መንገዶች ለእንግዳ ትምህርት ያላቸው ተጋላጭነት ላይ ምን ዓይነት መረዳት መያዝ ይገባናል? አንድን ትምህርት "እንግዳ" የሚያሰኙት ነገሮች ምን ምን ናቸው?
4. ክርስቲያን ኹሉ ራሱን ከኑ*ፋ*ቄ የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት። ሌላውን ከኑ*ፋ*ቄ የመጠበቅ ኃላፊነት የማነው? የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ስለዚህ ምን ይለናል? ማነው መልስ የሚሰጠው?
5. ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎች እርስ በእርስ ስለ እምነታቸው የሚወያዩበት "ስሜት"፤ ክርስቲያኖች ከሌላ ቤተ እምነት ሰዎች ጋር ስለ እምነት ከሚነጋገሩበት "ስሜት" ጋር አንድ መሆን ይገባዋል?
✍️ዲያቆን ሚኪያስ አስረስ እንደጻፈው
BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6265