TSEOMM Telegram 6242
ት/ቤቶቻችን እና መስተጋብራቸው
***
በቤተ ክርስቲያን የአብነት ት/ቤት ወጥ የሆነ ዘመናትን የተሻገረ ርቱዕ ትምህርት ይሰጣል፤ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ይወጡበታል። እነዚህ መምህራን የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና እና አዋልድ መጻሕፍትን ሁሉ በዚህ የአብነት መሠረታቸው ይመለከታሉ፤ ያብራራሉ።
ቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ቅርጽ ያላቸው የሥነ መለኮት ት/ቤቶችም አሏት። እነዚህ ት/ቤቶች ሰፋ ያሉ የጥንት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ፣ ታሪክ፣ የአበው ድርሳናት (ወደ ግእዝ ተተርጉመው የማናገኛቸውን ወይም ቀድሞ ኖረው በኋላ የጠፉትን ጨምሮ)፣ ንጽጽራዊ ሥነ መለኮት እና ነገረ-መለኮትን ለመረዳት የሚጠቅሙ ልዩ ልዩ ጥንታውያን ቋንቋዎች ይሰጡባቸዋል። ምርምር እንደሚያስፈልጋቸው በሚታመንባቸው ጉዳዮች ላይ ጥናቶችም ይሠሩባቸዋል።
ቤተ ክርስቲያን አብነቱን እንደያዘች ሥነ መለኮት ት/ቤቶች እንደሚያስፈልጓት አምና ሁለቱንም ይዛለች። ይህ የሌሎች ኦርቶዶክሳውያን አብያተ ክርስቲያናት እውነታም ነው።
ለወደፊቱ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ተግዳሮት ከሚፈጥሩ ነገሮች አንዱ የሁለቱ ት/ቤቶች መስተጋብር ነው። መፈራረጅ እና መቆሳሰል ብዙ ጉዳት አድርሶ የግለሰቦች መጣያ እና መጠላለፊያ ከመሆኑ በፊት በትልቁ ምሥል ላይ በቂ ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል። በጉዳዮች ላይ በቂ ውይይት ሳይደረግ ሲቀር ጉዳይ ግለሰባዊ መነቃቀፊያ ወደ መሆን ይወርዳልና።
ጤናማው የአካሄድ መሥመር የቱ ነው? በአብነቱ የማናገኛቸውን ነገር ግን በዘመኑ ለሚነሡ ጥያቄዎች አስፈላጊ የሆኑ የአበው ድርሳናት እና የታሪክ ምንጮች እንዴት እንጠቀም? ተቃርኖ የሚመስሉ ነገሮች ሲገጥሙ እንዴት እንፍታ? የሌሎች ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሊቃውንት መጻሕፍት ስናነብ የሚያስፈልገው ጥንቃቄ ምንድር ነው? የሚሉት እና መሰል ጉዳዮች ሳይረፍድ እና ችግሮች ሳይገነግኑ ለውይይት መቅረብ ይኖርባቸዋል።
የእኔን አጭር እይታ ላስቀምጥ። በሥነ መለኮት ት/ቤቶች የሚማሩ ሰዎች የአብነቱን ትምህርት ትልቅ ዋጋ ሰጥተው ማጥናት ይገባቸዋል፤ የአብነቱን ት/ት ዜማውን ለመማር ቢከብድ እንኳ ይዘቱን (መልእክቱን) አክብሮ ማወቅ እና መረዳት ግዴታ ይመስለኛል። በአብነት ት/ቤት ያሉ ሊቃውንት ደግሞ የሥነ መለኮት ት/ቤት ውስጥ የሚገኙ ተጨማሪ እውቀቶች እና ምንጮች ቢያገኙ የአብነቱን የበለጠ በጥልቀት ለመረዳት እና ለማብራራት ይረዳቸዋል። ነገሮችን ከታሪካዊ ዳራቸው ለመረዳት እና ታሪካዊ ዓውዳቸውን ለመረዳት የሥነ መለኮት ምንጮች ጠቃሚ ናቸው። በመሆኑም ሳይጠራጠሩት በበጎ ኅሊና ሊያዩት፣ እድሉ ከተገኘም ሊማሩት ይገባል። በተለይ ደግሞ የአብነት መሠረት ያላቸው ሊቃውንት የሥነ መለኮት ት/ቤቶች ውስጥ መኖራቸው ሁለቱንም በአግባቡ የመያዝ ሕያው ምስክሮች ስለሚሆኑ በእጅጉ ጠቃሚ ይሆናል። በዚህ መንገድ ለቤተ ክርስቲያን የሠመረ አገልግሎት ትልቅ መመጋገብ ሊኖራቸው ይችላል።

✍️ዲያቆን በረከት አዝመራው



tgoop.com/tseomm/6242
Create:
Last Update:

ት/ቤቶቻችን እና መስተጋብራቸው
***
በቤተ ክርስቲያን የአብነት ት/ቤት ወጥ የሆነ ዘመናትን የተሻገረ ርቱዕ ትምህርት ይሰጣል፤ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ይወጡበታል። እነዚህ መምህራን የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና እና አዋልድ መጻሕፍትን ሁሉ በዚህ የአብነት መሠረታቸው ይመለከታሉ፤ ያብራራሉ።
ቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ቅርጽ ያላቸው የሥነ መለኮት ት/ቤቶችም አሏት። እነዚህ ት/ቤቶች ሰፋ ያሉ የጥንት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ፣ ታሪክ፣ የአበው ድርሳናት (ወደ ግእዝ ተተርጉመው የማናገኛቸውን ወይም ቀድሞ ኖረው በኋላ የጠፉትን ጨምሮ)፣ ንጽጽራዊ ሥነ መለኮት እና ነገረ-መለኮትን ለመረዳት የሚጠቅሙ ልዩ ልዩ ጥንታውያን ቋንቋዎች ይሰጡባቸዋል። ምርምር እንደሚያስፈልጋቸው በሚታመንባቸው ጉዳዮች ላይ ጥናቶችም ይሠሩባቸዋል።
ቤተ ክርስቲያን አብነቱን እንደያዘች ሥነ መለኮት ት/ቤቶች እንደሚያስፈልጓት አምና ሁለቱንም ይዛለች። ይህ የሌሎች ኦርቶዶክሳውያን አብያተ ክርስቲያናት እውነታም ነው።
ለወደፊቱ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ተግዳሮት ከሚፈጥሩ ነገሮች አንዱ የሁለቱ ት/ቤቶች መስተጋብር ነው። መፈራረጅ እና መቆሳሰል ብዙ ጉዳት አድርሶ የግለሰቦች መጣያ እና መጠላለፊያ ከመሆኑ በፊት በትልቁ ምሥል ላይ በቂ ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል። በጉዳዮች ላይ በቂ ውይይት ሳይደረግ ሲቀር ጉዳይ ግለሰባዊ መነቃቀፊያ ወደ መሆን ይወርዳልና።
ጤናማው የአካሄድ መሥመር የቱ ነው? በአብነቱ የማናገኛቸውን ነገር ግን በዘመኑ ለሚነሡ ጥያቄዎች አስፈላጊ የሆኑ የአበው ድርሳናት እና የታሪክ ምንጮች እንዴት እንጠቀም? ተቃርኖ የሚመስሉ ነገሮች ሲገጥሙ እንዴት እንፍታ? የሌሎች ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሊቃውንት መጻሕፍት ስናነብ የሚያስፈልገው ጥንቃቄ ምንድር ነው? የሚሉት እና መሰል ጉዳዮች ሳይረፍድ እና ችግሮች ሳይገነግኑ ለውይይት መቅረብ ይኖርባቸዋል።
የእኔን አጭር እይታ ላስቀምጥ። በሥነ መለኮት ት/ቤቶች የሚማሩ ሰዎች የአብነቱን ትምህርት ትልቅ ዋጋ ሰጥተው ማጥናት ይገባቸዋል፤ የአብነቱን ት/ት ዜማውን ለመማር ቢከብድ እንኳ ይዘቱን (መልእክቱን) አክብሮ ማወቅ እና መረዳት ግዴታ ይመስለኛል። በአብነት ት/ቤት ያሉ ሊቃውንት ደግሞ የሥነ መለኮት ት/ቤት ውስጥ የሚገኙ ተጨማሪ እውቀቶች እና ምንጮች ቢያገኙ የአብነቱን የበለጠ በጥልቀት ለመረዳት እና ለማብራራት ይረዳቸዋል። ነገሮችን ከታሪካዊ ዳራቸው ለመረዳት እና ታሪካዊ ዓውዳቸውን ለመረዳት የሥነ መለኮት ምንጮች ጠቃሚ ናቸው። በመሆኑም ሳይጠራጠሩት በበጎ ኅሊና ሊያዩት፣ እድሉ ከተገኘም ሊማሩት ይገባል። በተለይ ደግሞ የአብነት መሠረት ያላቸው ሊቃውንት የሥነ መለኮት ት/ቤቶች ውስጥ መኖራቸው ሁለቱንም በአግባቡ የመያዝ ሕያው ምስክሮች ስለሚሆኑ በእጅጉ ጠቃሚ ይሆናል። በዚህ መንገድ ለቤተ ክርስቲያን የሠመረ አገልግሎት ትልቅ መመጋገብ ሊኖራቸው ይችላል።

✍️ዲያቆን በረከት አዝመራው

BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6242

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

During a meeting with the president of the Supreme Electoral Court (TSE) on June 6, Telegram's Vice President Ilya Perekopsky announced the initiatives. According to the executive, Brazil is the first country in the world where Telegram is introducing the features, which could be expanded to other countries facing threats to democracy through the dissemination of false content. In the “Bear Market Screaming Therapy Group” on Telegram, members are only allowed to post voice notes of themselves screaming. Anything else will result in an instant ban from the group, which currently has about 75 members. With the “Bear Market Screaming Therapy Group,” we’ve now transcended language. Telegram channels fall into two types: There have been several contributions to the group with members posting voice notes of screaming, yelling, groaning, and wailing in different rhythms and pitches. Calling out the “degenerate” community or the crypto obsessives that engage in high-risk trading, Co-founder of NFT renting protocol Rentable World emiliano.eth shared this group on his Twitter. He wrote: “hey degen, are you stressed? Just let it out all out. Voice only tg channel for screaming”.
from us


Telegram ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu
FROM American