tgoop.com/tseomm/6179
Create:
Last Update:
Last Update:
በጥምቀት በዓል መዳረሻ በርካታ ወጣቶች በአዲስ አበባ ከተማ እየታፈሱ መሆኑ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ ስፍራዎች በተለይ በደማቁ የጥምቀት በአል ወቅት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የሚታወቁ ወጣቶች እየታፈሱ መሆኑ ታውቋል።
መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚያሳያው እንደ ሽሮ ሜዳ፣ ፈረንሳይ፣ ካዛንችስ፣ ሳሪስ፣ አዋሬ ወዘተ ባሉ ስፍራዎች የሚገኙ ወጣቶች በብዛት በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው።
ሽሮ ሜዳ አካባቢ ትናንት ማታ ከ30 በላይ ወጣቶችን የሽሮ ሜዳ ፖሊስ አፍሶ እንደወሰዳቸው የአይን እማኞች ተናግረዋል። ወጣቶቹ የቤተክርስቲያን ጥምቀት አስተባባሪዎች እና ምንጣፍ የሚሸከሙ ልጆች መሆናቸው ታውቋል።
በሌላ በኩል በዛሬው እለት ሳሪስ አዲስ ሰፈር እና ብሄረ ፅጌ አካባቢ ለጥምቀት በአል የተሰቀሉ ማስዋቢያዎችን ፖሊስ በሀይል ያነሳ ሲሆን ሰቅላችኋል የተባሉ አንዳንድ ወጣቶችም እንደታሰሩ ታውቋል።
ከዚህ በፊት በየመንገዱ የሚሰቀሉ እና የኦርቶዶክስ አርማ ያለበት ባንዲራ ጭምር በፖሊስ በበርካታ ስፍራዎች እንዲወርድ እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል።
ማምሻውን ከፖሊስ ምላሽ ለማግኘት ያረግነው ሙከራ አልተሳካም።
ፎቶ: ፋይል
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
BY ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu

Share with your friend now:
tgoop.com/tseomm/6179