SAMUELBELETE Telegram 1653
ጸጋዬ በአፍሪካ ሥነ ጽሁፍ ሰማይ ሥር
ሰውየው የአፍሪካ የቲያትር ታሪክ ተመራማሪ ነው እንደ ደራሲም የገነነ ነው። በዚምባብዌ ሥነ ጽሁፍ ዘረፍ ደማቅ አሻራዎችን ካሳረፉት መካከል ሲጠቅስ የሱ ሥም አይጠፋም ቤተሰቦቹ ሮበርት ምሼንጉ ካቫናግ የሚል ሥም ሰጥተውታል። በሥራ አጋጣሚ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በምጣበት ወቅት ሎሬት ጸጋዬን ተዋወቀው ሮበርት ምሼንጉ ካቫናግ ወደ አገሩ ተመለሰ በቀጣይ ጊዜ ሲመለስ ጸጋዬን አንድ ሆቴል አገኘው ወደ አግሩ በተመለሰ ማግስት ሮበርት ምሼንጉ ካቫናግ “TSEGAYE GEBRE-MEDHIN: LET HIS LIGHT SHINE” የሚል ጽሁፍ በሰባት ገጽ ጻፈ ጽሁፉን አንብቤ ስጨርስ ጋሽ ጽጋዬ በጣም ራቀብኝ ምናቤ ሊቆጣጠረው አልቻለም ምንም እንኩዋ ጋሽ ጽጋዬ በህይወት ባይኖርም ሁለተኑ የአፍሪካ ቀንድ እንቁዎች መንፈሳቸውን ላቀራርብ ብዬ ይህንን ለመጻፍ ኮሚፒተሬን ከፈትኩ። በዚህ ጽሁፍ አብዛኛው በመሃል ከምሰነዝራቸው ጥቂት ሃሳቦች በቀር ሃሳቡ የሚያጠነጥነው “TSEGAYE GEBRE-MEDHIN: LET HIS LIGHT SHINE” በሚለው መጣጥፍ ላይ እንደሆነ አንባቢ ልብ ሊል ይገባል።
ወትሮ እኛ እፍሪካውያን ጣታችን እጅ የፈታው በጠብመንጃ ነው ማለት ይቻላል ዳዴ ስንል አፈር ለመላስ አልታደልንም ለጋ መላሳችን ባሩድ ቀመሰ አፍሪካዊ ጎለመሰም፣ መሪም ሆነ ተመሪ የጦርነት አታሞ ሲደልቅ ጣቱ ለብዕር አይታዘዝለትም ከኪነት ለሚገኝም የነፍስ ሃሴት መንፈሱ እሩቅ ነው። በአጠቃላይ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ አፍሪካዊ ኪነት የኦግስታቮ ቫሳን የቅኝ ግዛት ትረካን ከማጫወቻ ሸክላው አላወረደም ወደ አገራችን የኪነት ዘርፍ ስንመጣ ምንም እንኩዋ አገሪቱዋ ቀኝ ባትገዛም የጎረቤቶቹዋ ቅኝ የመገዛት መንፈስ ተጭኑዋት እንደቆየ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል። ስለ አፍሪካ ሥነ ጽሁፍ የሚያትቱ ድርሳናትን፣ የግብጽ ጥንታዊ ሥነ ጽሁፍ በስሱ የአረብ ሥነ ጽሁፍ ላይ ተጽኖ አድርጉዋል። ይላሉ አገራችንም በጥንታዊነቱዋ ከዚህ የምትጋራው የስልጣኔ ማውረስ ባህሪ አለ ይሁንና አገራችንን ጨምሮ ሌሎችም የአፍሪካ አገራት በቁዋንቀዋቸው ዘገምተኛ ባህሪ ምክንያት ሥነ ጽሁፋቸው አላደገም ጋዜጠኛና ገጣሚ ሰለሞን ደሬሳ በአንድ ቃለመጠይቁ ላይ “በግዕዝ አለሳይንስ አልተጻፈም” ይላል።
ከላይ በተነሱት ምክኛቶች የአገራችን ከያኒያን ልፋታቸው አልሰመረም ሮበርት ምሼንጉ በአፍሪካ ሥነ ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ድርሻ ያላቸውን ኬንያዊውን ደራሲ ናግዋጊ ዋ ቱንጊዎን ጠቅሶ የአፍሪካ ጽሃፊዎች የቅኝ ግዛት ታሪካቸው እንደፈተናቸው ሰፊ ተነባቢነት ለማግኝት ሲሉ በሌላ ቁዋንቁዋ ለመጻፍ ተገደዋል ይላል። “Still, Tsegaye’s fate is an object demonstration of what an African writer must sacrifice if he writes in his native tongue – fame and love among his people but insignificance in the Anglophone or Francophone international mainstream. Almost all Africa’s best-known writers write in a European language in order to reach a wider readership or audience though there is a slight suspicion that many African writers who write in European languages, write with at last half an eye on their European market – and their publishers probably with a lot more than half.” በእኔ አተያይ ኢትዮጵያ ቅኝ አለመገዛቱዋ ለተውኔና ለግጥም ስራዎቹ ትልቅ መንፈስ የሰጠው ይመስለኛል።
ሃያሲ ቴዎድሮስ ገብሬ ጸጋዬን ከ አዳም ጋር አነጻጽረው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በዳሰሱበት ጥናታቸው ላይ ጋሽ ጸጋዬን እንዲህ ይገልጹታል። “ጸጋዬ ተሰርቶ ያለቀ symbol ይፈልጋል። የጸጋዬ narrative ወይንም national myth ሙከራ በግዙፋን እሴቶች ላይ ለምሳሌ በአባይ፣ በአዋሽ፣ በምኒልክ፣ በዓድዋ፣ በቴዎድሮስና በዘርዓይ ታሪክ ላይ ይመሰረታል። እዛ ላይ ተመስርቶ seriously የሚፈልገውን ይሰራል።” ለእኔጋሽ ጸጋዬ በአሁንችን፣ በሁኔታችን አስቆጥቶት ሁዋላችንን ሊከስትልን በቅርጽ ሊያሳየን የለፋ ይመስለኛል። ዓድዋ ሩቅዋ-የዓለት ምሰሶ ጥግዋ-ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ-ዓድዋ…-ባንቺ ህልውና - በትዝታሽ ብጽዕና ማለቱ ከላይ ለጠቅስኩት አጽንኦት ማስረጃ ይሆነኛል። ሮበርት ምሼንጉ ምን አልባት የቁዋንቁዋ ነገር ይዞት ይሆነንጂ ጋሽ ጸጋዬ ስራዎች ላይ ታሪካዊና ሂሳዊ ምልከታዎቹን ቢያጋራል በአማርኛ ለተጻፉት ማጀቢያ አድርን እናነባቸው ነበር.።
ጋሽ ጸጋዬ በበርካታ አገራት ዘይቤና ቁዋንቁዋ መጻፍ ሲችል ለምን በአማርኛ በስፋት ጻፈ? ለሮበርት ምሼንጉ ሰለሞን ደሬሳ አንድ ዕድሜ ለአንድ ህይወት ላይበቃ አይነት አባባል በሚመስል መልኩ እንዲህ ነበር ያለው“ I have only one life and that life I have dedicated to writing plays for my people in our own language.” በቀኝ የተገዙ የአፍሪካ አገራት ቅኝ የመገዛት መንፈስ መጅ ሆኖ ወደሁዋላ ሲጎትታቸው ጋሽ ጸጋዬ ደግሞ በአገሪቱ ተንሰራፍቶ የነበረው የፊውዳል ስርአት በተለይ በተውኔት ስራዎቹ ላይ ፈተና እንደሆነበት ለለሮበርት ምሼንጉ አጫውቶታል። ስለ ጋሽ ጸጋዬ ለመጻፍ አንድ እድሜ ይበቃል? ገጣሚ ነው፣ እንዳንል ጽሃፌ ተውኔት ነው፣ ደራሲ ነው እንዳንል የታሪክ ተመራማሪ ነው፣ አፍሪካዊ ነው እንዳንል፣ አለማቀፋዊ ነው፣ አለማቀፋዊ ነው ብለን እንዳንዘጋው አዋሽን አረሳውም በአፍሪካ ሰማይ ስር ግን ጸጋዬ እንዲህ ይታወቃል “For Tsegaye Gebre-Medhin Qawasa was a unique polymath, a poet, a writer and an extraordinary man. He deserves an honoured place in the African theatre Hall of Fame.” ሮበርት ምሼንጉ ካቫናግ የአፍሪካ የቲያትር ታሪክ ተመራማሪና ደራሲ



tgoop.com/samuelbelete/1653
Create:
Last Update:

ጸጋዬ በአፍሪካ ሥነ ጽሁፍ ሰማይ ሥር
ሰውየው የአፍሪካ የቲያትር ታሪክ ተመራማሪ ነው እንደ ደራሲም የገነነ ነው። በዚምባብዌ ሥነ ጽሁፍ ዘረፍ ደማቅ አሻራዎችን ካሳረፉት መካከል ሲጠቅስ የሱ ሥም አይጠፋም ቤተሰቦቹ ሮበርት ምሼንጉ ካቫናግ የሚል ሥም ሰጥተውታል። በሥራ አጋጣሚ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በምጣበት ወቅት ሎሬት ጸጋዬን ተዋወቀው ሮበርት ምሼንጉ ካቫናግ ወደ አገሩ ተመለሰ በቀጣይ ጊዜ ሲመለስ ጸጋዬን አንድ ሆቴል አገኘው ወደ አግሩ በተመለሰ ማግስት ሮበርት ምሼንጉ ካቫናግ “TSEGAYE GEBRE-MEDHIN: LET HIS LIGHT SHINE” የሚል ጽሁፍ በሰባት ገጽ ጻፈ ጽሁፉን አንብቤ ስጨርስ ጋሽ ጽጋዬ በጣም ራቀብኝ ምናቤ ሊቆጣጠረው አልቻለም ምንም እንኩዋ ጋሽ ጽጋዬ በህይወት ባይኖርም ሁለተኑ የአፍሪካ ቀንድ እንቁዎች መንፈሳቸውን ላቀራርብ ብዬ ይህንን ለመጻፍ ኮሚፒተሬን ከፈትኩ። በዚህ ጽሁፍ አብዛኛው በመሃል ከምሰነዝራቸው ጥቂት ሃሳቦች በቀር ሃሳቡ የሚያጠነጥነው “TSEGAYE GEBRE-MEDHIN: LET HIS LIGHT SHINE” በሚለው መጣጥፍ ላይ እንደሆነ አንባቢ ልብ ሊል ይገባል።
ወትሮ እኛ እፍሪካውያን ጣታችን እጅ የፈታው በጠብመንጃ ነው ማለት ይቻላል ዳዴ ስንል አፈር ለመላስ አልታደልንም ለጋ መላሳችን ባሩድ ቀመሰ አፍሪካዊ ጎለመሰም፣ መሪም ሆነ ተመሪ የጦርነት አታሞ ሲደልቅ ጣቱ ለብዕር አይታዘዝለትም ከኪነት ለሚገኝም የነፍስ ሃሴት መንፈሱ እሩቅ ነው። በአጠቃላይ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ አፍሪካዊ ኪነት የኦግስታቮ ቫሳን የቅኝ ግዛት ትረካን ከማጫወቻ ሸክላው አላወረደም ወደ አገራችን የኪነት ዘርፍ ስንመጣ ምንም እንኩዋ አገሪቱዋ ቀኝ ባትገዛም የጎረቤቶቹዋ ቅኝ የመገዛት መንፈስ ተጭኑዋት እንደቆየ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል። ስለ አፍሪካ ሥነ ጽሁፍ የሚያትቱ ድርሳናትን፣ የግብጽ ጥንታዊ ሥነ ጽሁፍ በስሱ የአረብ ሥነ ጽሁፍ ላይ ተጽኖ አድርጉዋል። ይላሉ አገራችንም በጥንታዊነቱዋ ከዚህ የምትጋራው የስልጣኔ ማውረስ ባህሪ አለ ይሁንና አገራችንን ጨምሮ ሌሎችም የአፍሪካ አገራት በቁዋንቀዋቸው ዘገምተኛ ባህሪ ምክንያት ሥነ ጽሁፋቸው አላደገም ጋዜጠኛና ገጣሚ ሰለሞን ደሬሳ በአንድ ቃለመጠይቁ ላይ “በግዕዝ አለሳይንስ አልተጻፈም” ይላል።
ከላይ በተነሱት ምክኛቶች የአገራችን ከያኒያን ልፋታቸው አልሰመረም ሮበርት ምሼንጉ በአፍሪካ ሥነ ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ድርሻ ያላቸውን ኬንያዊውን ደራሲ ናግዋጊ ዋ ቱንጊዎን ጠቅሶ የአፍሪካ ጽሃፊዎች የቅኝ ግዛት ታሪካቸው እንደፈተናቸው ሰፊ ተነባቢነት ለማግኝት ሲሉ በሌላ ቁዋንቁዋ ለመጻፍ ተገደዋል ይላል። “Still, Tsegaye’s fate is an object demonstration of what an African writer must sacrifice if he writes in his native tongue – fame and love among his people but insignificance in the Anglophone or Francophone international mainstream. Almost all Africa’s best-known writers write in a European language in order to reach a wider readership or audience though there is a slight suspicion that many African writers who write in European languages, write with at last half an eye on their European market – and their publishers probably with a lot more than half.” በእኔ አተያይ ኢትዮጵያ ቅኝ አለመገዛቱዋ ለተውኔና ለግጥም ስራዎቹ ትልቅ መንፈስ የሰጠው ይመስለኛል።
ሃያሲ ቴዎድሮስ ገብሬ ጸጋዬን ከ አዳም ጋር አነጻጽረው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በዳሰሱበት ጥናታቸው ላይ ጋሽ ጸጋዬን እንዲህ ይገልጹታል። “ጸጋዬ ተሰርቶ ያለቀ symbol ይፈልጋል። የጸጋዬ narrative ወይንም national myth ሙከራ በግዙፋን እሴቶች ላይ ለምሳሌ በአባይ፣ በአዋሽ፣ በምኒልክ፣ በዓድዋ፣ በቴዎድሮስና በዘርዓይ ታሪክ ላይ ይመሰረታል። እዛ ላይ ተመስርቶ seriously የሚፈልገውን ይሰራል።” ለእኔጋሽ ጸጋዬ በአሁንችን፣ በሁኔታችን አስቆጥቶት ሁዋላችንን ሊከስትልን በቅርጽ ሊያሳየን የለፋ ይመስለኛል። ዓድዋ ሩቅዋ-የዓለት ምሰሶ ጥግዋ-ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ-ዓድዋ…-ባንቺ ህልውና - በትዝታሽ ብጽዕና ማለቱ ከላይ ለጠቅስኩት አጽንኦት ማስረጃ ይሆነኛል። ሮበርት ምሼንጉ ምን አልባት የቁዋንቁዋ ነገር ይዞት ይሆነንጂ ጋሽ ጸጋዬ ስራዎች ላይ ታሪካዊና ሂሳዊ ምልከታዎቹን ቢያጋራል በአማርኛ ለተጻፉት ማጀቢያ አድርን እናነባቸው ነበር.።
ጋሽ ጸጋዬ በበርካታ አገራት ዘይቤና ቁዋንቁዋ መጻፍ ሲችል ለምን በአማርኛ በስፋት ጻፈ? ለሮበርት ምሼንጉ ሰለሞን ደሬሳ አንድ ዕድሜ ለአንድ ህይወት ላይበቃ አይነት አባባል በሚመስል መልኩ እንዲህ ነበር ያለው“ I have only one life and that life I have dedicated to writing plays for my people in our own language.” በቀኝ የተገዙ የአፍሪካ አገራት ቅኝ የመገዛት መንፈስ መጅ ሆኖ ወደሁዋላ ሲጎትታቸው ጋሽ ጸጋዬ ደግሞ በአገሪቱ ተንሰራፍቶ የነበረው የፊውዳል ስርአት በተለይ በተውኔት ስራዎቹ ላይ ፈተና እንደሆነበት ለለሮበርት ምሼንጉ አጫውቶታል። ስለ ጋሽ ጸጋዬ ለመጻፍ አንድ እድሜ ይበቃል? ገጣሚ ነው፣ እንዳንል ጽሃፌ ተውኔት ነው፣ ደራሲ ነው እንዳንል የታሪክ ተመራማሪ ነው፣ አፍሪካዊ ነው እንዳንል፣ አለማቀፋዊ ነው፣ አለማቀፋዊ ነው ብለን እንዳንዘጋው አዋሽን አረሳውም በአፍሪካ ሰማይ ስር ግን ጸጋዬ እንዲህ ይታወቃል “For Tsegaye Gebre-Medhin Qawasa was a unique polymath, a poet, a writer and an extraordinary man. He deserves an honoured place in the African theatre Hall of Fame.” ሮበርት ምሼንጉ ካቫናግ የአፍሪካ የቲያትር ታሪክ ተመራማሪና ደራሲ

BY ሳሙኤል በለጠ(ባማ)


Share with your friend now:
tgoop.com/samuelbelete/1653

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Image: Telegram. The group’s featured image is of a Pepe frog yelling, often referred to as the “REEEEEEE” meme. Pepe the Frog was created back in 2005 by Matt Furie and has since become an internet symbol for meme culture and “degen” culture. During the meeting with TSE Minister Edson Fachin, Perekopsky also mentioned the TSE channel on the platform as one of the firm's key success stories. Launched as part of the company's commitments to tackle the spread of fake news in Brazil, the verified channel has attracted more than 184,000 members in less than a month. A vandalised bank during the 2019 protest. File photo: May James/HKFP. But a Telegram statement also said: "Any requests related to political censorship or limiting human rights such as the rights to free speech or assembly are not and will not be considered."
from us


Telegram ሳሙኤል በለጠ(ባማ)
FROM American