Notice: file_put_contents(): Write of 4033 bytes failed with errno=28 No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 50

Warning: file_put_contents(): Only 16384 of 20417 bytes written, possibly out of free disk space in /var/www/tgoop/post.php on line 50
ፍኖተ ሕይወት@nshachannel P.1034
NSHACHANNEL Telegram 1034
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አሐዱ አምላክ አሜን! †


እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል እና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን።

በአንድ ሀገር አስተራኒቆስ የሚባል መኮንንና ሚስቱ አፎምያ ይኖሩ ነበር፡፡ሁለቱም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ቅዱስ ሚካኤልን የሚወዱ ነበሩ፡፡ ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤል የበዓሉን መታሰቢያ ያደርጉ ነበር፡፡ በቅዱስ ሚካኤልም ስም ድሆችን እየረዱ ሲኖሩ አስተራኒቆስ ይታመማል፡፡ ያን ጊዜም ሚስቱ አፎምያ እኔን ይጠብቀኝ ዘንድ የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አሠርተህ ስጠኝ አለችው፡፡ እርሱም እንደለመነችው በልዩ ልዩ ጌጣጌጥ በወርቅ ቅብ አሠርቶ ሰጣት፤ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ባሏ ሞተ፡፡

ቅድስት አፎምያ ባሏ ከሞተ በኋላ ዘወትር በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት እየቆመች የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እዘንልኝ ምሕረትን ከአምላክህ ለምንልኝ ጠብቀኝ እያለች ትፀልይ ነበር፡፡ ሰይጣንም በጾም በጸሎቷ በምጽዋቷ ቀናባት ሊያሳስታትም ፈልጎ ብዙ ልጆች የየዘች ሴት መስሎ ወደ እርሷ መጣ፡፡ ቅድስት አፎምያንም ‹‹ጾም አታብዢ በኋላ ትከሻለሽ ፤ ለድሆች አትመጽውቺ በኋላ ድሀ ትሆኛለሽ፤ ጸሎት ማብዛት ምንም አይጠቅምሽም፡፡ ደግሞ ባል አግብተሽ ልትኖሪ ይገባል፤ እኔም የመጣሁት ከንጉሡ ተልኬ ነው፤ ንጉሡ አንቺን ሊያገባ ይፈልጋል፤ አንቺም ይህን እድል ተጠቀሚበት›› አላት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን በሰይጣን ንግግር አልተታለለችም፤ ይልቅ ጾም ጸሎት እንደሚያስፈልግ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ እየጠቀሰች ነገረችው፡፡ ከዚህም በኋላ የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል እንዲሳለም ብታመጣ ሰይጣን ፈርቶ ሮጠ፡፡ ቅድስት አፎምያንም ‹‹በያዝሽው ሥዕል አትመኪ በሰኔ 12 ቀን ሚካኤል በአምላኩ ፊት ሊሰግድና የሰዎችን ልመና ሊያቀርብ በእግዚአበሔር ፊት ሲቆም ያን ጊዜ መጥቼ አስትሻለሁ›› አላት፡፡ እርሷም በትእምርተ መስቀል ብታማትብ ከአጠገቧ ጠፋ፡፡ እርሷ ግን ዘወትር በጾም በጸሎት ትተጋ ነበር፡፡

በሰኔ 12 ቀን ሰይጣን የብርሃን መልአክ መስሎ ተገለጠ፡፡ ለቅድስት አፎምያም "ሰይጣን ያለውን ሰምቻለሁ እጠብቅሽም ዘንድ ከሰማይ ወረድኩ ስለዚህ ለእኔ ስገጂልኝ" አላት፡፡ ቅድስት አፎምያም "እውነት አንተ ሚካኤል ከሆንክ በቤቴ ውስጥ እንዳለው ሥዕል የመስቀል ምልክት የታለ የያዝከው? አለችው፡፡ ሰይጣንም "ለእኛ ለመላእክት እኮ ምንም ምልክት የለንም አላት፡፡ እርሷም መልሳ ንጉሥ ማኅተም የሌለውን ደብዳቤ ቢልክ የሚያመነው የለም እንዲሁ መስቀል ያልያዘን መልአክ ሁሉም ይንቀዋል አይቀበሉትም" አለችው፡፡ ያን ጊዜም ሰይጣን መልኩን ለውጦ ጨለማ መስሎ ዘሎ አነቃት፤ እርሷም ‹‹የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ከጠላቴ አድነኝ›› አለች፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ሊያጽናናት ታላቅ ብርሃን ለብሶ መጣ ቤቱንም በብርሃን ሞላው፡፡ ሰይጣንንም በበትረ መስቀሉ መታውና መሬት ላይ ጣለው ሰይጣንም "እባክህን አታጥፋኝ" ከእንግዲህ ሥዕልህ ወዳለበት ስምህ ወደተጠራበት አልደርስም አለው፡፡ ያኔም ሰይጣንን አዋርዶ አሳፍሮ ተወው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም "አፎምያ ሆይ! ዛሬ ነፍስሽ ከሥጋሽ ትለያለች መላእክትም ነፍስሽን ወደ ገነት ያሳርጓታል ስለዚህም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒጂና ጸሎት አድርጊ" አላት፡፡ እርሷም ንጹሕ ልብስ ለብሳ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደችና የጌታችንን ሥጋና ደሙን ተቀበለች፡፡ ከዚያም ንብረቷን በሙሉ ሸጣ ለድሆች እንዲሰጥ ለጳጳሱ አደራ ሰጠችው፡፡ በቤቷ የነበረውም ሥዕል በርሮ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ገባ ካለ ገመድ ተንጠለጠለ፤ ቅጠል አወጣ ፍሬም አፈራ፡፡ ብዙ አጋንንት ያደረባቸው የታመሙም ሰዎች ቅጠሉን ቆርጠው ወስደው ይታጠቡበትና ይድኑ ነበር፡፡

"ኦ ሚካኤል! ኦ ሚካኤል! ኦ መተንብል!
ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል፥
ዘእምርኡሳን ርኡስ ወዘእምልዑላን ልዑል
ጊዜ ጸዋዕኩከ ቅረበኒ በምሕረት ወሣህል!"

ቅዱሳን መላእክት እንደ ታላቅ ወንድም የሚያስቡልን የሚንከባከቡን ከሰይጣን ወጥመድ የሚያድኑን ናቸው። የቅዱሱ መልአክ ተራዳኢነት አይለየን!!!
👍5



tgoop.com/nshachannel/1034
Create:
Last Update:

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አሐዱ አምላክ አሜን! †


እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል እና ለቅዱሳኑ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣አደረሰን።

በአንድ ሀገር አስተራኒቆስ የሚባል መኮንንና ሚስቱ አፎምያ ይኖሩ ነበር፡፡ሁለቱም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ቅዱስ ሚካኤልን የሚወዱ ነበሩ፡፡ ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤል የበዓሉን መታሰቢያ ያደርጉ ነበር፡፡ በቅዱስ ሚካኤልም ስም ድሆችን እየረዱ ሲኖሩ አስተራኒቆስ ይታመማል፡፡ ያን ጊዜም ሚስቱ አፎምያ እኔን ይጠብቀኝ ዘንድ የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አሠርተህ ስጠኝ አለችው፡፡ እርሱም እንደለመነችው በልዩ ልዩ ጌጣጌጥ በወርቅ ቅብ አሠርቶ ሰጣት፤ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ባሏ ሞተ፡፡

ቅድስት አፎምያ ባሏ ከሞተ በኋላ ዘወትር በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት እየቆመች የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ እዘንልኝ ምሕረትን ከአምላክህ ለምንልኝ ጠብቀኝ እያለች ትፀልይ ነበር፡፡ ሰይጣንም በጾም በጸሎቷ በምጽዋቷ ቀናባት ሊያሳስታትም ፈልጎ ብዙ ልጆች የየዘች ሴት መስሎ ወደ እርሷ መጣ፡፡ ቅድስት አፎምያንም ‹‹ጾም አታብዢ በኋላ ትከሻለሽ ፤ ለድሆች አትመጽውቺ በኋላ ድሀ ትሆኛለሽ፤ ጸሎት ማብዛት ምንም አይጠቅምሽም፡፡ ደግሞ ባል አግብተሽ ልትኖሪ ይገባል፤ እኔም የመጣሁት ከንጉሡ ተልኬ ነው፤ ንጉሡ አንቺን ሊያገባ ይፈልጋል፤ አንቺም ይህን እድል ተጠቀሚበት›› አላት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን በሰይጣን ንግግር አልተታለለችም፤ ይልቅ ጾም ጸሎት እንደሚያስፈልግ
ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ እየጠቀሰች ነገረችው፡፡ ከዚህም በኋላ የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል እንዲሳለም ብታመጣ ሰይጣን ፈርቶ ሮጠ፡፡ ቅድስት አፎምያንም ‹‹በያዝሽው ሥዕል አትመኪ በሰኔ 12 ቀን ሚካኤል በአምላኩ ፊት ሊሰግድና የሰዎችን ልመና ሊያቀርብ በእግዚአበሔር ፊት ሲቆም ያን ጊዜ መጥቼ አስትሻለሁ›› አላት፡፡ እርሷም በትእምርተ መስቀል ብታማትብ ከአጠገቧ ጠፋ፡፡ እርሷ ግን ዘወትር በጾም በጸሎት ትተጋ ነበር፡፡

በሰኔ 12 ቀን ሰይጣን የብርሃን መልአክ መስሎ ተገለጠ፡፡ ለቅድስት አፎምያም "ሰይጣን ያለውን ሰምቻለሁ እጠብቅሽም ዘንድ ከሰማይ ወረድኩ ስለዚህ ለእኔ ስገጂልኝ" አላት፡፡ ቅድስት አፎምያም "እውነት አንተ ሚካኤል ከሆንክ በቤቴ ውስጥ እንዳለው ሥዕል የመስቀል ምልክት የታለ የያዝከው? አለችው፡፡ ሰይጣንም "ለእኛ ለመላእክት እኮ ምንም ምልክት የለንም አላት፡፡ እርሷም መልሳ ንጉሥ ማኅተም የሌለውን ደብዳቤ ቢልክ የሚያመነው የለም እንዲሁ መስቀል ያልያዘን መልአክ ሁሉም ይንቀዋል አይቀበሉትም" አለችው፡፡ ያን ጊዜም ሰይጣን መልኩን ለውጦ ጨለማ መስሎ ዘሎ አነቃት፤ እርሷም ‹‹የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ከጠላቴ አድነኝ›› አለች፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ሊያጽናናት ታላቅ ብርሃን ለብሶ መጣ ቤቱንም በብርሃን ሞላው፡፡ ሰይጣንንም በበትረ መስቀሉ መታውና መሬት ላይ ጣለው ሰይጣንም "እባክህን አታጥፋኝ" ከእንግዲህ ሥዕልህ ወዳለበት ስምህ ወደተጠራበት አልደርስም አለው፡፡ ያኔም ሰይጣንን አዋርዶ አሳፍሮ ተወው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም "አፎምያ ሆይ! ዛሬ ነፍስሽ ከሥጋሽ ትለያለች መላእክትም ነፍስሽን ወደ ገነት ያሳርጓታል ስለዚህም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒጂና ጸሎት አድርጊ" አላት፡፡ እርሷም ንጹሕ ልብስ ለብሳ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደችና የጌታችንን ሥጋና ደሙን ተቀበለች፡፡ ከዚያም ንብረቷን በሙሉ ሸጣ ለድሆች እንዲሰጥ ለጳጳሱ አደራ ሰጠችው፡፡ በቤቷ የነበረውም ሥዕል በርሮ ወደ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ገባ ካለ ገመድ ተንጠለጠለ፤ ቅጠል አወጣ ፍሬም አፈራ፡፡ ብዙ አጋንንት ያደረባቸው የታመሙም ሰዎች ቅጠሉን ቆርጠው ወስደው ይታጠቡበትና ይድኑ ነበር፡፡

"ኦ ሚካኤል! ኦ ሚካኤል! ኦ መተንብል!
ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል፥
ዘእምርኡሳን ርኡስ ወዘእምልዑላን ልዑል
ጊዜ ጸዋዕኩከ ቅረበኒ በምሕረት ወሣህል!"

ቅዱሳን መላእክት እንደ ታላቅ ወንድም የሚያስቡልን የሚንከባከቡን ከሰይጣን ወጥመድ የሚያድኑን ናቸው። የቅዱሱ መልአክ ተራዳኢነት አይለየን!!!

BY ፍኖተ ሕይወት


Share with your friend now:
tgoop.com/nshachannel/1034

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

To upload a logo, click the Menu icon and select “Manage Channel.” In a new window, hit the Camera icon. Polls With the sharp downturn in the crypto market, yelling has become a coping mechanism for many crypto traders. This screaming therapy became popular after the surge of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May or early June. Here, holders made incoherent groaning sounds in late-night Twitter spaces. They also role-played as urine-loving Goblin creatures. Invite up to 200 users from your contacts to join your channel Telegram has announced a number of measures aiming to tackle the spread of disinformation through its platform in Brazil. These features are part of an agreement between the platform and the country's authorities ahead of the elections in October.
from us


Telegram ፍኖተ ሕይወት
FROM American