Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/maninet1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tgoop/post.php on line 50
ማንነት/ IDENTITY@maninet1 P.2983
MANINET1 Telegram 2983
ኒላ ዘ መንፈስ 3
(አሌክስ አብርሃም)

የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት አስፈሪ እና ግራ አጋቢ ነበሩ ለፊደል፤ ከባድ ሆነውባት አለፉ! እንቅልፍ ማጣት ግራ መጋባት ...በየቀኑ ፍርሃቷ ቀስ በቀስ እየለቀቃት ቢሄድም መልመድ ያልቻለችው አንድ ነገር መታዘዝን ነበር። ውስጧ ተደላድላ የተቀመጠችው የተረገመች ኒላ ደግሞ ማዘዝ ነፍሷ ነው። መታዘዝ ነፍስ ስጋና መንፈስን ለአዛዢ ማስገዛት ነው! ፊደል ከልጅነቷ በነፃነት ያደገች ልጅ ናት።ከፍ ስትል ከተማሪ እስከአስተማሪ፣ ከመንደር ጎረምሳ እስከሚጠጓት ወንዶች ለውበቷ ተንበርክከው ስትጠራቸው አቤት ስትልካቸው ወዴት ባይ አሽከሮቿ ነበሩ! አሞጋሿ ብዙ ነበር! ዞር ስትል የሚያሟት ፊት ለፊት ይሽቆጠቆጡላታል።

ሌሎችን በአይን እይታ ብቻ ቁጭ ብድግ የምታደርጋቸው ፊደል ዛሬ ምንነቷ ለማይታወቅ መንፈስ በእሷ አባባል«ገረድ» ሁናለች። ለምሳሌ ፊደል በተፈጥሮ ውበቷም ይሁን በሽቅርቅር ፋሽን ተከታይነቷ ሊነኳት እንኳን የምታስፈራ ንፁህና ቆንጆ ትሁን እንጅ ቤት ውስጥ ዝርክርክ ነበረች። የበላችበት ዕቃ ለቀናት ሊከመር ልብሷ እዚህና እዛ ተዝረክርኮ ለሳምንታት ሊቆይ ይችላል። ኒላ ደግሞ ፈፅሞ ከዚህ ተቃራኒ ናት። አይደለምና መዝረክረክ ፊደል በራሷ ቤት ከነጫማዋ ምንጣፍ ላይ ከወጣች ታብዳለች!
«አንች የማትረቢ ቆሻሻ . . .» ብላ ነው የምትጀምረው!

አንድ ቀን ጧት (ሌሊት ማለት ይቀላል ከጧቱ አስር ሰዓት ) ፊደል በጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ እንዳለች በሚያስበረግግ ጩኸት «ተነሽ» አለቻት ኒላ !ጩኸቱ ፊደልን አስበርግጎ ቀኑን ሙሉ ለእራስ ምታት ዳረጋት ! ቢሆንም ፊቷን እንዳጨፈገገች ተነስታ አልጋዋ ጫፍ ላይ ተቀመጠች!
«ዛሬ ይሄን ቤት እናፀዳለን»
«እንዴ . . .»
«አፍሽን ዝጊ ! እንደዚህ የተግማማ ቤት ውስጥ ልኖር አልችም! ገና ለገና መንፈስ ነኝ ታይፎይድና ታይፈስ አይዘኝም ብየ ዝም ልል አልችልም! ድብርት ራሱ ከታይፎይድ እኩል ነው! ቆሻሻ አልወድም ነገርኩሽ! ቆይ ለመሆኑ የምትኖሪው ለእነዚህ ተጎልተው የአንችን የማይረባ ፎቶና አርቲ ቡርቲ ፊልም ለሚያዩ ድንዙዞች ነው ወይስ ለራስሽ? ውጭ አፈር አይንካኝ ትያለሽ ቤትሽ ግን በክቷል ለራስሽ ክብር የለሽም ? በዚህ ቤት ነው እንግዳ የምንጋብዘው? »
«የምን እንግዳ ነው ! እኔ ማንንም እቤቴ አልጋብዝም. .»
«እኔ እጋብዛለኋ»
«ምን. . .?»
«እ ን ግ ዳ እጋብዛለሁ!!
«የምን እንግዳ ነው በቤቴ የምትጋብዥው ? አልበዛም?»
« ቤ ታ ች ን በይ!»

«አልልም ቤቴ ነው! »

«ቤታችን ነው» ፊደል ደከማት ! መንፈስ ግን አይደክመውም ይሆን ስትል አሰበች! የዛን ቀን ለዓመታት ያልተፀዳ ቤቷን ለማፅዳት ስትፈጋ ዋለች!ከኪችን እስከሸንት ቤት ከበረንዳ እስከግቢው ወገቧ እስኪንቀጠቀጥ አፀዳች! ኒላ ዘና ብላ ታዛታለች! ትሰድባታለች ልክ የባሪያ አሳዳሪ ነበር የምትመስለው! » ራሷን እስክትስት ቢደክማትም ውጤቱ ለራሷ ገረማት።

በዚህ ሁኔታ አንዴ ሲጣሉ ሌላ ጊዜ ሲኮራረፉ ቀናት ነጎዱ! ይች ግራ የገባት መንፈስ እንደባሪያ ያዘዝኩሽን አድርጊ ስትላት ያለመደችው መታዘዝ ከእልህ ጋር እየተቀላቀለ ግራ የገባት ልጅ አደረጋት! ቢሆንም ይች ወፈፌ ከታዘዘቻት የማትቆጣ እንደውም ትሁትና የጓደኝነት መንፈስ ያላት ፍጥረት መሆኗን ተረድታለች። አንዳንዴ ለቀናት ድምፅዋን ስለምታጠፋ ትታት የሄደች ይመስላት ነበር። ይሁንና ስሟን ጠርታ አለሽ ወይ ማለት ትፈራለች!አብረው በቆዩበት ጊዜ አንዳንድ ባህሪዎቿን ማወቅ ችላለች። እና በፀባይ ልትይዛትና እስከወዲያኛው የምትሸኝባትን መንገድ ለመፈለግ ወሰነች!

አንድ ቀን እንዲሁ ሲነታረኩ ውለው እንደተኮራረፉ ፊደል ለመጀመሪያ ጊዜ መንፈሷን በስሟ ጠራቻት
«ኒላ »
«ምን ፈለግሽ?»
«ይቅርታ ስላስቀየምኩሽ . . . ግራ ገብቶኝ ነው » ኒላ ዝም አለች! «እንደምታይው አድናቂ እንጅ ጓደኛም ዘመድም የለኝም! ብቸኛ ነኝ! የሚመጡት ሁሉ ወይ እውቅናየን አልያም ሴትቴን ፈልገው የሚመጡ ናቸው ጥልቅ ብቸኝነት ውስጥ የምኖር ብቸኛ ሴት ነኝ! እባክሽ ተረጅኝ»

« የነገርሽኝ ነገር አያሳዝንም. . .እዛ ሂጅና አብራሽ የምታለቃቅስ ሴት ፈልጊ! ልፍስፍስ ሴት አልወድም!ኢትዯጵያዊያን ተያይዘን እንውጣ ከሚላችሁ ይልቅ ሙሾ የሚያወርድላችሁን አስለቃሽ ነው የምትወዱት! አንች ራስሽ ራስሽን የምታደንቂው መስተዋት ፊትኮ ነው! የራስሽ እንኳን ጓደኛ አይደለሽም! ማንም የሚገዛሽ ለገበያ ያቀረብሽውን ነው! መቀመጫሽን ያቀረብሽለት አለም አዕምሮሽን ሊመርጥ አይችልም! ምኔን አይተው ተጠጉኝ ከማለትሽ በፊት ምንሽን አሳየሻቸው? ታዋቂ ነሽ እንጅ አያውቁሽም! ራስን ሸፍኖ እወቁኝ እያሉ ማልቀስ አለ እንዴ? ኪንኪ ፀጉርሽን እንኳን በእኔ ፀጉር ነው የሸፈንሸው! አየሽ የቤት ኪራይ ባልከፍልም በፀጉሬ የመጣልሽን በረከት ተካፋይ ነኝ! ሸበላ ወንድም ከመጣ ተካፋይ ነኝ ሂሂሂሂሂሂሂ! በነፃ አይደለም አንች ውስጥ የምኖረው ሰው ለእናት አገሩ እጁን እግሩን አይንና ሌላ አካሉን እንደሚሰጥ ፀጉሬን ሰጥቸሻለሁ፤ ፀጉር አካል ነው! አፍንጫሽ ላይ ያለው ዲኤን ኤ ፀጉርሽም ውስጥ አለ! ስለዚህ ጡረታ የምወጣው አንች ውስጥ ነው» ፊደል በዝምታ ስትሰማት ቆየች!

ኒላ ቀጠለች «ለመሆኑ ሶሻል ሚዲያው ላይ ስንት ተከታይ አለሽ?»
«ወደአንድ ሚሊየን. . .»አለች ፊደል!
«ለዚህ ሁሉ ተከታይሽ ምን ሰጠሽው? ፎቶ ፎቶ አሁንም ፎቶ . . . ፎቶሽ ምንሽን ያሳያል ? ቂ . . .ሽን ፣ ጡትሽን ፣ እግርሽን ፣ ጥፍርሽን . . . ጥፍራም! ባለፈው ፊልምሽን ልታስመርቂ ስትዘጋጅ ፀጉር ቤት ስንት ሰዓት ቆየሽ . . . አምስት ሰዓት ፣ ማሳጅ ቤት ሶስት ሰዓት ልብስ ስትለኪ ስታወልቂ አራት ሰዓታት ! ቢያንስ በየሳምንቱ «ራስን መጠበቅ» በሚል ሰበብ እድሜሽን መስተዋት ፊት እንደሽንኩርት በመላጥ የምታጠፊውን ጊዜ አስቢ! በዚህ መሃበረሰብ ውስጥ የአንች ቂ . . . ጤና ጣቢያ ነው ትምህርት ቤት? ቁንጅና ጥሩ ነው ! ግን ትንሽ ክፍተት ትንሽ መስኮት ነገር ከቁንጅናሽ አልፈው ወደአንች ሊገቡ ለሚፈልጉ ተይላቸው!

ድፍን ቆንጆ ብቻ አትሁኝ!በርና መስኮት የሌለው ደረጃ የሌለው ውብ ህንፃ ጥቅሙ ከውጭ መታየትና ለዙሪያው አዳማቂ መሆን ብቻ ነው!ሰዎች እንዲያርፉብሽ ውስጥሽ ትንሽ ወንበሮች ይኑሩ! እንደዛ ስልሽ እንደመሰል ጓደኞችሽ ነጠላሽን አደግድገሽ ለበዓል ካሜራ ፊት ድሆችን አሰልፈሽ ብሉልኝ ጠጡልኝ የምትይውን የሚያቅለሸልሽ «በጎ ስራ» አይደም! እሱ በጎ ስራ ሳይሆን «በጎ አድናቆት» ነው ! ምግብ መፀወትሽ እውቅናና አድናቆት ተመፀወትሽ! የለማኝ ሰልፍ ውስጥ ነሽ! ተደነቅሽበት ተወደሽበት ግን ባዶ ነሽ! ለራስሽ ስምና ዝና የምትቃርሚበት በጎ ስራ የስም ሜካፕ ነው! ራስሽን ብቻ ነው የሚያሳምረው! አንድ ቀን ሲዘንብ ታጥቦ አስቀያሚነትሽ ያገጣል!

«እስኪ ስለራስሽ ንገሪኝ » አለች ፊደል ትንሽ ጨዋታውን ለማስቀየር! ትችት አትወድም!

«ወሬኛ አትሁኝ ! እድሜ ልክሽን ስለሌሎች ሰምተሻል ፤አሁን ቢመርም ስለራስሽ መስሚያሽ ነው!. . .ለምንድነው ግን ኢትዯጵያዊያን አብዝታችሁ ስለሌሎች መስማት የምትወዱት? ራሳችሁን ትፀየፋላችሁ ወይስ በራሳችሁ ታፍራላችሁ?» ፊደል ዝም አለች! «ከድህነታችሁ በላይ አስከፊው ባህሪያችሁ ከእራሳችሁ መራቃችሁ ነው! ዙሪያችሁ ገደል እና ሚስጥር ነው . . .
1



tgoop.com/maninet1/2983
Create:
Last Update:

ኒላ ዘ መንፈስ 3
(አሌክስ አብርሃም)

የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት አስፈሪ እና ግራ አጋቢ ነበሩ ለፊደል፤ ከባድ ሆነውባት አለፉ! እንቅልፍ ማጣት ግራ መጋባት ...በየቀኑ ፍርሃቷ ቀስ በቀስ እየለቀቃት ቢሄድም መልመድ ያልቻለችው አንድ ነገር መታዘዝን ነበር። ውስጧ ተደላድላ የተቀመጠችው የተረገመች ኒላ ደግሞ ማዘዝ ነፍሷ ነው። መታዘዝ ነፍስ ስጋና መንፈስን ለአዛዢ ማስገዛት ነው! ፊደል ከልጅነቷ በነፃነት ያደገች ልጅ ናት።ከፍ ስትል ከተማሪ እስከአስተማሪ፣ ከመንደር ጎረምሳ እስከሚጠጓት ወንዶች ለውበቷ ተንበርክከው ስትጠራቸው አቤት ስትልካቸው ወዴት ባይ አሽከሮቿ ነበሩ! አሞጋሿ ብዙ ነበር! ዞር ስትል የሚያሟት ፊት ለፊት ይሽቆጠቆጡላታል።

ሌሎችን በአይን እይታ ብቻ ቁጭ ብድግ የምታደርጋቸው ፊደል ዛሬ ምንነቷ ለማይታወቅ መንፈስ በእሷ አባባል«ገረድ» ሁናለች። ለምሳሌ ፊደል በተፈጥሮ ውበቷም ይሁን በሽቅርቅር ፋሽን ተከታይነቷ ሊነኳት እንኳን የምታስፈራ ንፁህና ቆንጆ ትሁን እንጅ ቤት ውስጥ ዝርክርክ ነበረች። የበላችበት ዕቃ ለቀናት ሊከመር ልብሷ እዚህና እዛ ተዝረክርኮ ለሳምንታት ሊቆይ ይችላል። ኒላ ደግሞ ፈፅሞ ከዚህ ተቃራኒ ናት። አይደለምና መዝረክረክ ፊደል በራሷ ቤት ከነጫማዋ ምንጣፍ ላይ ከወጣች ታብዳለች!
«አንች የማትረቢ ቆሻሻ . . .» ብላ ነው የምትጀምረው!

አንድ ቀን ጧት (ሌሊት ማለት ይቀላል ከጧቱ አስር ሰዓት ) ፊደል በጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ እንዳለች በሚያስበረግግ ጩኸት «ተነሽ» አለቻት ኒላ !ጩኸቱ ፊደልን አስበርግጎ ቀኑን ሙሉ ለእራስ ምታት ዳረጋት ! ቢሆንም ፊቷን እንዳጨፈገገች ተነስታ አልጋዋ ጫፍ ላይ ተቀመጠች!
«ዛሬ ይሄን ቤት እናፀዳለን»
«እንዴ . . .»
«አፍሽን ዝጊ ! እንደዚህ የተግማማ ቤት ውስጥ ልኖር አልችም! ገና ለገና መንፈስ ነኝ ታይፎይድና ታይፈስ አይዘኝም ብየ ዝም ልል አልችልም! ድብርት ራሱ ከታይፎይድ እኩል ነው! ቆሻሻ አልወድም ነገርኩሽ! ቆይ ለመሆኑ የምትኖሪው ለእነዚህ ተጎልተው የአንችን የማይረባ ፎቶና አርቲ ቡርቲ ፊልም ለሚያዩ ድንዙዞች ነው ወይስ ለራስሽ? ውጭ አፈር አይንካኝ ትያለሽ ቤትሽ ግን በክቷል ለራስሽ ክብር የለሽም ? በዚህ ቤት ነው እንግዳ የምንጋብዘው? »
«የምን እንግዳ ነው ! እኔ ማንንም እቤቴ አልጋብዝም. .»
«እኔ እጋብዛለኋ»
«ምን. . .?»
«እ ን ግ ዳ እጋብዛለሁ!!
«የምን እንግዳ ነው በቤቴ የምትጋብዥው ? አልበዛም?»
« ቤ ታ ች ን በይ!»

«አልልም ቤቴ ነው! »

«ቤታችን ነው» ፊደል ደከማት ! መንፈስ ግን አይደክመውም ይሆን ስትል አሰበች! የዛን ቀን ለዓመታት ያልተፀዳ ቤቷን ለማፅዳት ስትፈጋ ዋለች!ከኪችን እስከሸንት ቤት ከበረንዳ እስከግቢው ወገቧ እስኪንቀጠቀጥ አፀዳች! ኒላ ዘና ብላ ታዛታለች! ትሰድባታለች ልክ የባሪያ አሳዳሪ ነበር የምትመስለው! » ራሷን እስክትስት ቢደክማትም ውጤቱ ለራሷ ገረማት።

በዚህ ሁኔታ አንዴ ሲጣሉ ሌላ ጊዜ ሲኮራረፉ ቀናት ነጎዱ! ይች ግራ የገባት መንፈስ እንደባሪያ ያዘዝኩሽን አድርጊ ስትላት ያለመደችው መታዘዝ ከእልህ ጋር እየተቀላቀለ ግራ የገባት ልጅ አደረጋት! ቢሆንም ይች ወፈፌ ከታዘዘቻት የማትቆጣ እንደውም ትሁትና የጓደኝነት መንፈስ ያላት ፍጥረት መሆኗን ተረድታለች። አንዳንዴ ለቀናት ድምፅዋን ስለምታጠፋ ትታት የሄደች ይመስላት ነበር። ይሁንና ስሟን ጠርታ አለሽ ወይ ማለት ትፈራለች!አብረው በቆዩበት ጊዜ አንዳንድ ባህሪዎቿን ማወቅ ችላለች። እና በፀባይ ልትይዛትና እስከወዲያኛው የምትሸኝባትን መንገድ ለመፈለግ ወሰነች!

አንድ ቀን እንዲሁ ሲነታረኩ ውለው እንደተኮራረፉ ፊደል ለመጀመሪያ ጊዜ መንፈሷን በስሟ ጠራቻት
«ኒላ »
«ምን ፈለግሽ?»
«ይቅርታ ስላስቀየምኩሽ . . . ግራ ገብቶኝ ነው » ኒላ ዝም አለች! «እንደምታይው አድናቂ እንጅ ጓደኛም ዘመድም የለኝም! ብቸኛ ነኝ! የሚመጡት ሁሉ ወይ እውቅናየን አልያም ሴትቴን ፈልገው የሚመጡ ናቸው ጥልቅ ብቸኝነት ውስጥ የምኖር ብቸኛ ሴት ነኝ! እባክሽ ተረጅኝ»

« የነገርሽኝ ነገር አያሳዝንም. . .እዛ ሂጅና አብራሽ የምታለቃቅስ ሴት ፈልጊ! ልፍስፍስ ሴት አልወድም!ኢትዯጵያዊያን ተያይዘን እንውጣ ከሚላችሁ ይልቅ ሙሾ የሚያወርድላችሁን አስለቃሽ ነው የምትወዱት! አንች ራስሽ ራስሽን የምታደንቂው መስተዋት ፊትኮ ነው! የራስሽ እንኳን ጓደኛ አይደለሽም! ማንም የሚገዛሽ ለገበያ ያቀረብሽውን ነው! መቀመጫሽን ያቀረብሽለት አለም አዕምሮሽን ሊመርጥ አይችልም! ምኔን አይተው ተጠጉኝ ከማለትሽ በፊት ምንሽን አሳየሻቸው? ታዋቂ ነሽ እንጅ አያውቁሽም! ራስን ሸፍኖ እወቁኝ እያሉ ማልቀስ አለ እንዴ? ኪንኪ ፀጉርሽን እንኳን በእኔ ፀጉር ነው የሸፈንሸው! አየሽ የቤት ኪራይ ባልከፍልም በፀጉሬ የመጣልሽን በረከት ተካፋይ ነኝ! ሸበላ ወንድም ከመጣ ተካፋይ ነኝ ሂሂሂሂሂሂሂ! በነፃ አይደለም አንች ውስጥ የምኖረው ሰው ለእናት አገሩ እጁን እግሩን አይንና ሌላ አካሉን እንደሚሰጥ ፀጉሬን ሰጥቸሻለሁ፤ ፀጉር አካል ነው! አፍንጫሽ ላይ ያለው ዲኤን ኤ ፀጉርሽም ውስጥ አለ! ስለዚህ ጡረታ የምወጣው አንች ውስጥ ነው» ፊደል በዝምታ ስትሰማት ቆየች!

ኒላ ቀጠለች «ለመሆኑ ሶሻል ሚዲያው ላይ ስንት ተከታይ አለሽ?»
«ወደአንድ ሚሊየን. . .»አለች ፊደል!
«ለዚህ ሁሉ ተከታይሽ ምን ሰጠሽው? ፎቶ ፎቶ አሁንም ፎቶ . . . ፎቶሽ ምንሽን ያሳያል ? ቂ . . .ሽን ፣ ጡትሽን ፣ እግርሽን ፣ ጥፍርሽን . . . ጥፍራም! ባለፈው ፊልምሽን ልታስመርቂ ስትዘጋጅ ፀጉር ቤት ስንት ሰዓት ቆየሽ . . . አምስት ሰዓት ፣ ማሳጅ ቤት ሶስት ሰዓት ልብስ ስትለኪ ስታወልቂ አራት ሰዓታት ! ቢያንስ በየሳምንቱ «ራስን መጠበቅ» በሚል ሰበብ እድሜሽን መስተዋት ፊት እንደሽንኩርት በመላጥ የምታጠፊውን ጊዜ አስቢ! በዚህ መሃበረሰብ ውስጥ የአንች ቂ . . . ጤና ጣቢያ ነው ትምህርት ቤት? ቁንጅና ጥሩ ነው ! ግን ትንሽ ክፍተት ትንሽ መስኮት ነገር ከቁንጅናሽ አልፈው ወደአንች ሊገቡ ለሚፈልጉ ተይላቸው!

ድፍን ቆንጆ ብቻ አትሁኝ!በርና መስኮት የሌለው ደረጃ የሌለው ውብ ህንፃ ጥቅሙ ከውጭ መታየትና ለዙሪያው አዳማቂ መሆን ብቻ ነው!ሰዎች እንዲያርፉብሽ ውስጥሽ ትንሽ ወንበሮች ይኑሩ! እንደዛ ስልሽ እንደመሰል ጓደኞችሽ ነጠላሽን አደግድገሽ ለበዓል ካሜራ ፊት ድሆችን አሰልፈሽ ብሉልኝ ጠጡልኝ የምትይውን የሚያቅለሸልሽ «በጎ ስራ» አይደም! እሱ በጎ ስራ ሳይሆን «በጎ አድናቆት» ነው ! ምግብ መፀወትሽ እውቅናና አድናቆት ተመፀወትሽ! የለማኝ ሰልፍ ውስጥ ነሽ! ተደነቅሽበት ተወደሽበት ግን ባዶ ነሽ! ለራስሽ ስምና ዝና የምትቃርሚበት በጎ ስራ የስም ሜካፕ ነው! ራስሽን ብቻ ነው የሚያሳምረው! አንድ ቀን ሲዘንብ ታጥቦ አስቀያሚነትሽ ያገጣል!

«እስኪ ስለራስሽ ንገሪኝ » አለች ፊደል ትንሽ ጨዋታውን ለማስቀየር! ትችት አትወድም!

«ወሬኛ አትሁኝ ! እድሜ ልክሽን ስለሌሎች ሰምተሻል ፤አሁን ቢመርም ስለራስሽ መስሚያሽ ነው!. . .ለምንድነው ግን ኢትዯጵያዊያን አብዝታችሁ ስለሌሎች መስማት የምትወዱት? ራሳችሁን ትፀየፋላችሁ ወይስ በራሳችሁ ታፍራላችሁ?» ፊደል ዝም አለች! «ከድህነታችሁ በላይ አስከፊው ባህሪያችሁ ከእራሳችሁ መራቃችሁ ነው! ዙሪያችሁ ገደል እና ሚስጥር ነው . . .

BY ማንነት/ IDENTITY


Share with your friend now:
tgoop.com/maninet1/2983

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Image: Telegram. The imprisonment came as Telegram said it was "surprised" by claims that privacy commissioner Ada Chung Lai-ling is seeking to block the messaging app due to doxxing content targeting police and politicians. How to create a business channel on Telegram? (Tutorial) As of Thursday, the SUCK Channel had 34,146 subscribers, with only one message dated August 28, 2020. It was an announcement stating that police had removed all posts on the channel because its content “contravenes the laws of Hong Kong.” To view your bio, click the Menu icon and select “View channel info.”
from us


Telegram ማንነት/ IDENTITY
FROM American