Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/maninet1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tgoop/post.php on line 50
ማንነት/ IDENTITY@maninet1 P.2893
MANINET1 Telegram 2893
ፍቅር በዚያ ወራት !

(ክፍል 5)
ሚካኤል.አ

ለምን እንደሆነ ባላውቅም የዛኪን ስልክ አለማንሳት አልቻልኩም። ድምፁ ናፍቆኛል.. .

"ሄሎ "

"ሄሎ ንፁህ.. ."

ዝም አልኩት ። ረጋ ያለ ድምፅ!  ... 

ንፁህ ብሎ ሲጠራኝ እንባዬ ፈሰሰ ። አፍቃሪው ልቤ በክህደት ሰንሰለት ተተብትቦ በፀፀት አርጩሜ እየተወገረ ነው።

"ሄሎ " .. የድምፄን መጥፋት ሲረዳ ደግሞ ተናገረ ።

"ሄሎ ቲቸር "

"በሰላም ነው የጠፋሽው? ህመሙ አልተሻለሽም እንዴ?"

የተሻለኝ ህመም የለም። ጭራሽ የማይድን ሌላ የውስጥ ቁስል አመርቅዣለሁ ።

እወደዋለሁ.. .

የንሰሀዬ መንገድ የሱ ስክነት ነው። እሱ ቢያቅፈኝ...እሱ ቢያስብልኝ... እሱ መዳፉን አውሶ ቢዳብሰኝ እንደስሜ እነፃ ነበር ።

"ምንድነው ለቅሶ ነው የምሰማው ?" 

"አዎ ዛክ "

"ምን ሆነሻል ?" 

"እወ.. .."

ሰውን እወድሀለሁ ብሎ መናገር ለካ ይከብዳል ።

ቃላቶቼን ከምኔው እንደዋጥኳቸው አላቅም። ለሱ ፍቅሬን መግለፅ ስሜቱን የሚገድልብኝ ይመለኛል። ዛክ ከወንዶች ሁሉ ይለያል ብዬ ባስብም ሁሉም ወንዶች ደግሞ የሚያመሳስላቸው የጋራ ባህሪ እንዳላቸው አምናለሁ ። 

ሴት ልጅ ለወንድ ልጅ የውስጧን ስሜት በግልፅ ከነገረችው ለሷ ያለው አመለካከት ይወርዳል። ወንድ ልጅ ከአፍቃሪው ይልቅ በኩራት ገመድ ወጥራ ለምታሰቃየው ሴት የልቡ በራፍ ይከፈታል ።

ኩራት !

ወንዶች መለመን ይፈልጋሉ.. . እንደ ወርቅ ተደብቃ የማህደሯ ክርታስን ለመቆፈር የምታታግል ሴት የወንዶችን ልብ ቁልፍ በእጇ ይዛ ትዞራለች ።

"ምን አልሽ?"

"አወ...ቅማ ዶክተር እባክህ ትንሽ ህመሜ ስለጠነከረ ተጨማሪ ቀናትን ባልመጣ እንዳትቀየመኝ። "

"ለምን እቀየምሻለሁ?  ትምህርትም...ስራም.. .ከጤና በላይ አይሆኑም። ስትኖሪ ነው ሁሉ ነገር የሚኖረው።

በይ ፈጣሪ ይማርሽ ።"

"አሜን !" አልኩት ።

ይሄን ያልኩት ግን ለበሽታዬ ድህነት አይደለም። ፈጣሪ እኔ ላይ የሰራሽውን ሀጥያት ይቅር ብሎ ይማርሽ እንዳለኝ ነው የተረዳሁት የኔ ካህን ።

ስልኩ ሲቋረጥ ከንፈሬን ወደ ስክሪኑ ሰድጄ ሳምኩት ።

እኔ የሱ መቅደላዊት ማርያም ... 

በደሌ በፍቅሩ የሚነፃ ከሆነ ብዬ በእንባዬ ራስኩኝ።

....

በዛኑ ቀን ዶክተር እዘዝ ደወለ።

በሙት ስሜቴ ስልኩን አነሳሁት ። እድለ ቢሶች ከምንወደው ነገር ይልቅ የማንወደው ነገር ይከተለናል ። ዶክተር እዘዝ ን አልወደውም። በተለይ ከዛ ክስተት በኃላ የርኩሰቴ ቤንዚን ሆኖ ይሰማኛል።

"ጣፋጯ " አለኝ።

መራሩ ልበለው ይሆን?

"ይቅርታ ዶክተር ...እንደዚህ አትበለኝ "

" ምነው አንዴ የቀመሽውን ገላ መድገም አትወጅም መሰለኝ። ይሄ እኮ የሴቶች ሳይሆን የእኛ ባህሪ ነበር ለወትሮው ...

ቂ....ቂ...ቂ ..."

ሳቅ ይሄን ያህል ይቀፋል?

"ሁሉም ነገር ባጋጣሚ ነው የሆነው "

ቲቸር እዘዝ ቀፋፊ ሳቁን ቀጠለው ።

"ቂ....ቂ ...ቂ 

ለማንኛውም ተረጋጊ ...ጥሩ ጊዜ ነበረን። ጥሩም ሆነን ሴሚስተሩን እንጨርሳለን"

ይሄን ሲል እየዛተ ነው። ለኔ ጥሩ ካልሆንሽ ጥሩ ጊዜ አይኖረንም ሊለኝ እንደፈለገ ግልፅ ነው።

"እባክህ..."

አላስጨረሰኝም ። ስልኩ ከወዲያኛው አቅጣጫ የመዘጋት ድምፅ አሰማኝ። 

ካሁን በኃላ ትምህርት ቤቴ ገሀነሜ ነው። 

ዶክተር እዘዝ የሰይጣኑ ቁንጮ ሉሲፈሬ ነው።

ዛክን በድዬ ከሱ ጋር ያሳለፍኩትን የአልጋ ላይ ጨዋታ እንደማልደግመው አውቃለሁ።

ገላዬን ስነሳው ደግሞ ነጥብ እንደሚነሳኝ እሙን ነው ። 

የኔና የሱ ግንኙነትን ደግሞ ዛክዬ ከሰማ ሌላ የህይወት ፍላት ላስተናግድ ነው ።

ሁለት ፍላት በአንድ እስትንፋሴ የምሸከምበት አቅም ያለኝ አይመስለኝም።

አልጋዬ ማህፀን ገብቼ ተሸፋፍኜ ተኛሁ ።

የውሸት እንቅልፍ ነበር ...

ሰኞ ትምህርት ቤት ስሄድ ለሚገጥመኝ ጦርነት ልቦናዬን ማዘጋጀት ጀመርኩ ።

አሸናፊው ማን እንደሚሆን እናያለን! 

@maninet1
@maninet1
@betsiroyal



tgoop.com/maninet1/2893
Create:
Last Update:

ፍቅር በዚያ ወራት !

(ክፍል 5)
ሚካኤል.አ

ለምን እንደሆነ ባላውቅም የዛኪን ስልክ አለማንሳት አልቻልኩም። ድምፁ ናፍቆኛል.. .

"ሄሎ "

"ሄሎ ንፁህ.. ."

ዝም አልኩት ። ረጋ ያለ ድምፅ!  ... 

ንፁህ ብሎ ሲጠራኝ እንባዬ ፈሰሰ ። አፍቃሪው ልቤ በክህደት ሰንሰለት ተተብትቦ በፀፀት አርጩሜ እየተወገረ ነው።

"ሄሎ " .. የድምፄን መጥፋት ሲረዳ ደግሞ ተናገረ ።

"ሄሎ ቲቸር "

"በሰላም ነው የጠፋሽው? ህመሙ አልተሻለሽም እንዴ?"

የተሻለኝ ህመም የለም። ጭራሽ የማይድን ሌላ የውስጥ ቁስል አመርቅዣለሁ ።

እወደዋለሁ.. .

የንሰሀዬ መንገድ የሱ ስክነት ነው። እሱ ቢያቅፈኝ...እሱ ቢያስብልኝ... እሱ መዳፉን አውሶ ቢዳብሰኝ እንደስሜ እነፃ ነበር ።

"ምንድነው ለቅሶ ነው የምሰማው ?" 

"አዎ ዛክ "

"ምን ሆነሻል ?" 

"እወ.. .."

ሰውን እወድሀለሁ ብሎ መናገር ለካ ይከብዳል ።

ቃላቶቼን ከምኔው እንደዋጥኳቸው አላቅም። ለሱ ፍቅሬን መግለፅ ስሜቱን የሚገድልብኝ ይመለኛል። ዛክ ከወንዶች ሁሉ ይለያል ብዬ ባስብም ሁሉም ወንዶች ደግሞ የሚያመሳስላቸው የጋራ ባህሪ እንዳላቸው አምናለሁ ። 

ሴት ልጅ ለወንድ ልጅ የውስጧን ስሜት በግልፅ ከነገረችው ለሷ ያለው አመለካከት ይወርዳል። ወንድ ልጅ ከአፍቃሪው ይልቅ በኩራት ገመድ ወጥራ ለምታሰቃየው ሴት የልቡ በራፍ ይከፈታል ።

ኩራት !

ወንዶች መለመን ይፈልጋሉ.. . እንደ ወርቅ ተደብቃ የማህደሯ ክርታስን ለመቆፈር የምታታግል ሴት የወንዶችን ልብ ቁልፍ በእጇ ይዛ ትዞራለች ።

"ምን አልሽ?"

"አወ...ቅማ ዶክተር እባክህ ትንሽ ህመሜ ስለጠነከረ ተጨማሪ ቀናትን ባልመጣ እንዳትቀየመኝ። "

"ለምን እቀየምሻለሁ?  ትምህርትም...ስራም.. .ከጤና በላይ አይሆኑም። ስትኖሪ ነው ሁሉ ነገር የሚኖረው።

በይ ፈጣሪ ይማርሽ ።"

"አሜን !" አልኩት ።

ይሄን ያልኩት ግን ለበሽታዬ ድህነት አይደለም። ፈጣሪ እኔ ላይ የሰራሽውን ሀጥያት ይቅር ብሎ ይማርሽ እንዳለኝ ነው የተረዳሁት የኔ ካህን ።

ስልኩ ሲቋረጥ ከንፈሬን ወደ ስክሪኑ ሰድጄ ሳምኩት ።

እኔ የሱ መቅደላዊት ማርያም ... 

በደሌ በፍቅሩ የሚነፃ ከሆነ ብዬ በእንባዬ ራስኩኝ።

....

በዛኑ ቀን ዶክተር እዘዝ ደወለ።

በሙት ስሜቴ ስልኩን አነሳሁት ። እድለ ቢሶች ከምንወደው ነገር ይልቅ የማንወደው ነገር ይከተለናል ። ዶክተር እዘዝ ን አልወደውም። በተለይ ከዛ ክስተት በኃላ የርኩሰቴ ቤንዚን ሆኖ ይሰማኛል።

"ጣፋጯ " አለኝ።

መራሩ ልበለው ይሆን?

"ይቅርታ ዶክተር ...እንደዚህ አትበለኝ "

" ምነው አንዴ የቀመሽውን ገላ መድገም አትወጅም መሰለኝ። ይሄ እኮ የሴቶች ሳይሆን የእኛ ባህሪ ነበር ለወትሮው ...

ቂ....ቂ...ቂ ..."

ሳቅ ይሄን ያህል ይቀፋል?

"ሁሉም ነገር ባጋጣሚ ነው የሆነው "

ቲቸር እዘዝ ቀፋፊ ሳቁን ቀጠለው ።

"ቂ....ቂ ...ቂ 

ለማንኛውም ተረጋጊ ...ጥሩ ጊዜ ነበረን። ጥሩም ሆነን ሴሚስተሩን እንጨርሳለን"

ይሄን ሲል እየዛተ ነው። ለኔ ጥሩ ካልሆንሽ ጥሩ ጊዜ አይኖረንም ሊለኝ እንደፈለገ ግልፅ ነው።

"እባክህ..."

አላስጨረሰኝም ። ስልኩ ከወዲያኛው አቅጣጫ የመዘጋት ድምፅ አሰማኝ። 

ካሁን በኃላ ትምህርት ቤቴ ገሀነሜ ነው። 

ዶክተር እዘዝ የሰይጣኑ ቁንጮ ሉሲፈሬ ነው።

ዛክን በድዬ ከሱ ጋር ያሳለፍኩትን የአልጋ ላይ ጨዋታ እንደማልደግመው አውቃለሁ።

ገላዬን ስነሳው ደግሞ ነጥብ እንደሚነሳኝ እሙን ነው ። 

የኔና የሱ ግንኙነትን ደግሞ ዛክዬ ከሰማ ሌላ የህይወት ፍላት ላስተናግድ ነው ።

ሁለት ፍላት በአንድ እስትንፋሴ የምሸከምበት አቅም ያለኝ አይመስለኝም።

አልጋዬ ማህፀን ገብቼ ተሸፋፍኜ ተኛሁ ።

የውሸት እንቅልፍ ነበር ...

ሰኞ ትምህርት ቤት ስሄድ ለሚገጥመኝ ጦርነት ልቦናዬን ማዘጋጀት ጀመርኩ ።

አሸናፊው ማን እንደሚሆን እናያለን! 

@maninet1
@maninet1
@betsiroyal

BY ማንነት/ IDENTITY


Share with your friend now:
tgoop.com/maninet1/2893

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Telegram users themselves will be able to flag and report potentially false content. ZDNET RECOMMENDS 1What is Telegram Channels? bank east asia october 20 kowloon Although some crypto traders have moved toward screaming as a coping mechanism, several mental health experts call this therapy a pseudoscience. The crypto community finds its way to engage in one or the other way and share its feelings with other fellow members.
from us


Telegram ማንነት/ IDENTITY
FROM American