LEARN_WITH_JOHN Telegram 771
++ የሰይጣን ነጻ አውጪ +++

ብዙ ጊዜ በsocial mideaም ይሁን በብዙኃን መገናኛ በስፋት የሚታዩና ትልቅ ተደራሽነት የሚኖራቸው ነገሮች በማኅበረሰቡ ዘንድ የተከለከሉ እና ተቀባይነት የሌላቸው ድርጊቶች ናቸው። እነዚያን ጉዳዮች በማውገዝም ይሁን "ጉድ እኮ ነው" በሚል አግራሞት ለሌሎች የሚያጋራቸውና አስተያየት የሚሰጥባቸው ተመልካች ቁጥር ጥቂት የማይባል ነው። ይህ ግርግር በራሱ ሙሉ በሙሉም ባይሆን በከፊል ግን በውስጣችን ያለውን "በተከለከለ ነገር የሚማረክ" ማንነታችንን በደንብ ያሳያል። አይሆንም ተብለን እየተከለከልን በገባንበት ሱስ፣ ወዳጅነት፣ ፍቅር፣ ትዳር የምንሰቃይ ስንቶቻችን እንሆን?

ለመንፈሳዊ ሕይወታችንም ትልቅ እንቅፋት የሚሆንብን ይህ የተከለከለውን የሚያሳድድ ክፉ አመላችን ነው። ፈጣሪያችን "አታድርጉ" ሲለን እኛን ለመጠበቅ ሳይሆን የእኛን ዓለም ለማጥበብ ሲል ያሰረን ያህል ይሰማናል። የተሰጡንን ሕግጋት ካልጣስንም ነጻነታችንን ተግባራዊ ያደረግን አይመስለንም። የተፈቀደልንን አናደርግም፣ ያልተፈቀደልን ያንንም ሳናደርግ አንውልም። እኛ እንዲህ ነን፦ ቀኝ ሲጠብቁን በግራ፣ በግራ ሲያስሱን በቀኝ ብቅ የምንል ጉራማይሌ ነን።

ከሁሉ የሚያስደንቀው ደግሞ በዚህ ጠባያችን "የሰይጣን ነጻ አውጪ" እስከ መሆን መድረሳችን ነው። ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው መድኃኒታችን ክርስቶስ ለዘመናት ባሪያ ያደረገንንና ሲረግጠን የኖረውን ሰይጣን በመስቀሉ ጠርቆ (አስሮ) ከመንገድ አስወግዶልናል።(ቆላ 2፥14) እኛን ከእርሱ ጋር በትንሣኤው ሲያስነሣን ያን ዕቡይ ጠላታችንን ግን እንሳለቅበት ዘንድ ከእግራችን ስር ጥሎልናል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሰይጣን ጌታ ከተሰቀለባት እለተ አርብ በኋላ በብረት ሳጥን እንደ ታሰረ ውሻ ሆኗል ይለናል። ስለዚህ እንደ ፈቃዱ ሊፈነጭና ማንም ላይ ሊሰለጥን አይችልም ማለት ነው። ነገር ግን ሰው በፍላጎቱ ወደ ታሰረው ሰይጣን በሄደና መዝጊያውን በከፈተለት ጊዜ ለታሠረው ሰይጣን ነጻነት ይሰብካል። በክፋት ጥርሶቹ ነካክሶ ያደማው ዘንድ በገዛ እጁ በራሱ ላይ ያነግሠዋል። በዚህም ሰው የተፈቀደለትን ንግሥና ትቶ የተከለከለውን የዲያብሎስ ባርያነት ኑሮን ይገፋል።

አባ መቃርስ እንዳለው "የሚወደውን ባለጠጋ እግዚአብሔርን ጠልቶ የሚጠላውን ደሃ ሰይጣንን ወድዶ የሚከተል" ሰው ምን ያህል ሞኝ ነው?!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ

ድረ ገጹን ይጎብኙ
https://dnabel.com

ቴሌግራም
https://www.tgoop.com/Dnabel



tgoop.com/learn_with_John/771
Create:
Last Update:

++ የሰይጣን ነጻ አውጪ +++

ብዙ ጊዜ በsocial mideaም ይሁን በብዙኃን መገናኛ በስፋት የሚታዩና ትልቅ ተደራሽነት የሚኖራቸው ነገሮች በማኅበረሰቡ ዘንድ የተከለከሉ እና ተቀባይነት የሌላቸው ድርጊቶች ናቸው። እነዚያን ጉዳዮች በማውገዝም ይሁን "ጉድ እኮ ነው" በሚል አግራሞት ለሌሎች የሚያጋራቸውና አስተያየት የሚሰጥባቸው ተመልካች ቁጥር ጥቂት የማይባል ነው። ይህ ግርግር በራሱ ሙሉ በሙሉም ባይሆን በከፊል ግን በውስጣችን ያለውን "በተከለከለ ነገር የሚማረክ" ማንነታችንን በደንብ ያሳያል። አይሆንም ተብለን እየተከለከልን በገባንበት ሱስ፣ ወዳጅነት፣ ፍቅር፣ ትዳር የምንሰቃይ ስንቶቻችን እንሆን?

ለመንፈሳዊ ሕይወታችንም ትልቅ እንቅፋት የሚሆንብን ይህ የተከለከለውን የሚያሳድድ ክፉ አመላችን ነው። ፈጣሪያችን "አታድርጉ" ሲለን እኛን ለመጠበቅ ሳይሆን የእኛን ዓለም ለማጥበብ ሲል ያሰረን ያህል ይሰማናል። የተሰጡንን ሕግጋት ካልጣስንም ነጻነታችንን ተግባራዊ ያደረግን አይመስለንም። የተፈቀደልንን አናደርግም፣ ያልተፈቀደልን ያንንም ሳናደርግ አንውልም። እኛ እንዲህ ነን፦ ቀኝ ሲጠብቁን በግራ፣ በግራ ሲያስሱን በቀኝ ብቅ የምንል ጉራማይሌ ነን።

ከሁሉ የሚያስደንቀው ደግሞ በዚህ ጠባያችን "የሰይጣን ነጻ አውጪ" እስከ መሆን መድረሳችን ነው። ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው መድኃኒታችን ክርስቶስ ለዘመናት ባሪያ ያደረገንንና ሲረግጠን የኖረውን ሰይጣን በመስቀሉ ጠርቆ (አስሮ) ከመንገድ አስወግዶልናል።(ቆላ 2፥14) እኛን ከእርሱ ጋር በትንሣኤው ሲያስነሣን ያን ዕቡይ ጠላታችንን ግን እንሳለቅበት ዘንድ ከእግራችን ስር ጥሎልናል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሰይጣን ጌታ ከተሰቀለባት እለተ አርብ በኋላ በብረት ሳጥን እንደ ታሰረ ውሻ ሆኗል ይለናል። ስለዚህ እንደ ፈቃዱ ሊፈነጭና ማንም ላይ ሊሰለጥን አይችልም ማለት ነው። ነገር ግን ሰው በፍላጎቱ ወደ ታሰረው ሰይጣን በሄደና መዝጊያውን በከፈተለት ጊዜ ለታሠረው ሰይጣን ነጻነት ይሰብካል። በክፋት ጥርሶቹ ነካክሶ ያደማው ዘንድ በገዛ እጁ በራሱ ላይ ያነግሠዋል። በዚህም ሰው የተፈቀደለትን ንግሥና ትቶ የተከለከለውን የዲያብሎስ ባርያነት ኑሮን ይገፋል።

አባ መቃርስ እንዳለው "የሚወደውን ባለጠጋ እግዚአብሔርን ጠልቶ የሚጠላውን ደሃ ሰይጣንን ወድዶ የሚከተል" ሰው ምን ያህል ሞኝ ነው?!

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ

ድረ ገጹን ይጎብኙ
https://dnabel.com

ቴሌግራም
https://www.tgoop.com/Dnabel

BY እልመስጦአግያ+++




Share with your friend now:
tgoop.com/learn_with_John/771

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

The administrator of a telegram group, "Suck Channel," was sentenced to six years and six months in prison for seven counts of incitement yesterday. Add the logo from your device. Adjust the visible area of your image. Congratulations! Now your Telegram channel has a face Click “Save”.! The Channel name and bio must be no more than 255 characters long The channel also called on people to turn out for illegal assemblies and listed the things that participants should bring along with them, showing prior planning was in the works for riots. The messages also incited people to hurl toxic gas bombs at police and MTR stations, he added. Hui said the time period and nature of some offences “overlapped” and thus their prison terms could be served concurrently. The judge ordered Ng to be jailed for a total of six years and six months.
from us


Telegram እልመስጦአግያ+++
FROM American