tgoop.com/learn_with_John/527
Create:
Last Update:
Last Update:
🌾 ታዛዥነትና ተዘክሮተ እግዚአብሔር 🌾
🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃
አባ ዮሐንስ ኃፂር ከሚታወቅባቸው መልካም ምግባራት መካከል የሚጠቀሱለት ናቸው ታዛዥነትና ተዘክሮተ እግዚአብሔር፡፡ አንደ ቀን አባ ባሞይ ዮሐንስ ኃፂርን የደረቀ እንጨት ተክሎ ለምልማ እስክታፈራ ድረስ ውኃ እንዲያጠጣት አዘዘው፡፡ ያለማንገራገር በትኅትና ሆኖ አሥራ ሁለት ምዕራፍ ያህል ከሚርቅ ቦታ በቀን ሁለት ጊዜ ውኃ እያመላለሰ ያጠጣ ጀመር፡፡ በሦስተኛው ዓመት ያቺ በትር ለምልማና አብባ ያማረ ፍሬ አፈራች፡፡ አባ ባሞይ በዮሐንስ ታዛዥነት እጅግ ተደሰተ፡፡ ፍሬውን ለቅሞ ለገዳሙ መነኮሳት እንካችሁ ይህ የታዛዥነት ፍሬ ነው እያለ ሰጣቸው፡፡ መነኮሳቱም ይህን ተአምር ባዩ ጊዜ አደነቁ፡፡ ለቅን እና ታዛዥ ሰው ይህን ጸጋ የሰጠ እግዚአብሔርንም አመሰገኑ፡፡
"መልካም ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስ ያገኛል፡፡" ምሳሌ 12፤2
🌿🌹🌿🌹🌿🌹🌿🌹🌿🌹🌿🌹
🕊 🕊 🕊 🕊 🕊
ቃለ ሕይወትን ያሰማን
@Learn_with_John
BY እልመስጦአግያ+++
Share with your friend now:
tgoop.com/learn_with_John/527