Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/ethzema/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tgoop/post.php on line 50
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)@ethzema P.4687
ETHZEMA Telegram 4687
#ኢዜማ_ምን_ያስፈልገዋል ?

👉 #የምርጫ_ቅስቀሳ_ሰዓት

#ኢዜማን_በልኩ !!

ኢዜማ በአማራጭ ኃይልነት ጠንካራ ቁመና ያለው ፓርቲ ሆኖ እንዲወጣ አሁን ላይ “ምን ያስፈልገዋል?” ካልን ተራማጅ አስተሳሰብ ያለው የአዲሱ ትውልድ አካል የኾነ፣ ዘመኑን የሚዋጅ ቆራጥ እና ትጉህ አመራር ያስፈልገዋል ብለን እናምናለን።

አሁን የኢዜማ አዲሱ ትውልድ ኃላፊነትን የሚረከብበት ጊዜ ነው። ይህ ደግሞ ላለፉት 50 ዓመት ደጋግመን በሞከርነው እና ተፈትኖ በወደቀ የፖለቲካ ባሕል ውስጥ ተዘፍቆ ሊሳካ የሚችል አይደለም። አሁናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ በአዲስ መንፈስ አዲስ ትግል ይፈልጋል። አዲሱ የፖለቲካ ትግል የአዲሱ ትውልድ ኃላፊነት እና መብትም ጭምር ነው። በተለመደው መንገድ ባረጀ አስተሳሰብ ሄደን የተለየ ቦታ መድረስ ካለመቻላችንም በላይ የምንመኘውን ውጤት አናመጣም።

ይህ የኢዜማ አዲሱ ትውልድ ድምፅ ነው። ይህ ድምፅ አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የተዘጋጀ፣ ፖለቲካን ተስፋ አስቆራጭ በኾነ ዝግታ አልያም በስሜት እየቸኮለም የማይጋልብ “ኢዜማን በልኩ!” ብሎ የተነሳ ቁርጠኛ አመራር ነው። ላለፉት ስድስት ዓመታት ሀገራችን የነበረችበትን አስጊ የጸጥታ ሁኔታ እና የመበተን ስጋት በቅጡ በመረዳት ኢዜማ በእርጋታ እና በስክነት ሲሠራ እንደቆየ የሚታወቅ ነው። አሁን ላይ በሀገራችን ያሉትን ተለዋዋጭ ክስተቶች በጥልቀት በመገንዘብ እና በተለይም ሀገራዊ ምክክሩን እና 7 ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ከግምት በማስገባት በተግባር ኢዜማ በልኩ፣ በራሱ መንገድ፣ የራሱን ጉዞ ለማድረግ ተነስቷል።

ይህ ጉዞ ከኹሉም የፖለቲካ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረግን ሀቀኛ ትብብር የሚፈልግ እንደኾነ አያጠያይቅም። እኛ እንደምናስበው ኢዜማ በዚህ ሰዓት ጠንካራ መዋቅር መዘርጋት እና ተልዕኮውን መሸከም እና መፈጸም የሚችል ቆራጥ ድርጅታዊ አመራር ያስፈልገዋል። ይህ አመራር የጠራ አረዳድ ያለው፣ እርስ በእርስ የማይጓተት፣ ስለ ዓለምአቀፍ፣ ቀጣናዊ እና ሀገራዊ እንዲሁም ውስጣዊ ድርጅታዊ ሁኔታዎች በቂ ግንዛቤ ያለው መኾን አለበት። ኢዜማ የጋራ ግብና ዓላማ ሰንቆ የሚሠራ፣ ኹሌም ለመማር ዝግጁ የኾነ፣ ዘመኑን የሚዋጅ እውነተኛ የአዲሱ ትውልድ አመራር ለመኾን ቆርጦ የተነሳ አመራር ያስፈልገዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግም እኛ አራታችን (ሊቀመንበር፣ ም ሊቀመንበር፣ ዋና ጸሐፊ እና ፋይናንስ) ተግባብተን ለመመረጥ እየሠራን እንገኛለን።


👉 ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇

https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk



tgoop.com/ethzema/4687
Create:
Last Update:

#ኢዜማ_ምን_ያስፈልገዋል ?

👉 #የምርጫ_ቅስቀሳ_ሰዓት

#ኢዜማን_በልኩ !!

ኢዜማ በአማራጭ ኃይልነት ጠንካራ ቁመና ያለው ፓርቲ ሆኖ እንዲወጣ አሁን ላይ “ምን ያስፈልገዋል?” ካልን ተራማጅ አስተሳሰብ ያለው የአዲሱ ትውልድ አካል የኾነ፣ ዘመኑን የሚዋጅ ቆራጥ እና ትጉህ አመራር ያስፈልገዋል ብለን እናምናለን።

አሁን የኢዜማ አዲሱ ትውልድ ኃላፊነትን የሚረከብበት ጊዜ ነው። ይህ ደግሞ ላለፉት 50 ዓመት ደጋግመን በሞከርነው እና ተፈትኖ በወደቀ የፖለቲካ ባሕል ውስጥ ተዘፍቆ ሊሳካ የሚችል አይደለም። አሁናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ በአዲስ መንፈስ አዲስ ትግል ይፈልጋል። አዲሱ የፖለቲካ ትግል የአዲሱ ትውልድ ኃላፊነት እና መብትም ጭምር ነው። በተለመደው መንገድ ባረጀ አስተሳሰብ ሄደን የተለየ ቦታ መድረስ ካለመቻላችንም በላይ የምንመኘውን ውጤት አናመጣም።

ይህ የኢዜማ አዲሱ ትውልድ ድምፅ ነው። ይህ ድምፅ አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የተዘጋጀ፣ ፖለቲካን ተስፋ አስቆራጭ በኾነ ዝግታ አልያም በስሜት እየቸኮለም የማይጋልብ “ኢዜማን በልኩ!” ብሎ የተነሳ ቁርጠኛ አመራር ነው። ላለፉት ስድስት ዓመታት ሀገራችን የነበረችበትን አስጊ የጸጥታ ሁኔታ እና የመበተን ስጋት በቅጡ በመረዳት ኢዜማ በእርጋታ እና በስክነት ሲሠራ እንደቆየ የሚታወቅ ነው። አሁን ላይ በሀገራችን ያሉትን ተለዋዋጭ ክስተቶች በጥልቀት በመገንዘብ እና በተለይም ሀገራዊ ምክክሩን እና 7 ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ከግምት በማስገባት በተግባር ኢዜማ በልኩ፣ በራሱ መንገድ፣ የራሱን ጉዞ ለማድረግ ተነስቷል።

ይህ ጉዞ ከኹሉም የፖለቲካ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረግን ሀቀኛ ትብብር የሚፈልግ እንደኾነ አያጠያይቅም። እኛ እንደምናስበው ኢዜማ በዚህ ሰዓት ጠንካራ መዋቅር መዘርጋት እና ተልዕኮውን መሸከም እና መፈጸም የሚችል ቆራጥ ድርጅታዊ አመራር ያስፈልገዋል። ይህ አመራር የጠራ አረዳድ ያለው፣ እርስ በእርስ የማይጓተት፣ ስለ ዓለምአቀፍ፣ ቀጣናዊ እና ሀገራዊ እንዲሁም ውስጣዊ ድርጅታዊ ሁኔታዎች በቂ ግንዛቤ ያለው መኾን አለበት። ኢዜማ የጋራ ግብና ዓላማ ሰንቆ የሚሠራ፣ ኹሌም ለመማር ዝግጁ የኾነ፣ ዘመኑን የሚዋጅ እውነተኛ የአዲሱ ትውልድ አመራር ለመኾን ቆርጦ የተነሳ አመራር ያስፈልገዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግም እኛ አራታችን (ሊቀመንበር፣ ም ሊቀመንበር፣ ዋና ጸሐፊ እና ፋይናንስ) ተግባብተን ለመመረጥ እየሠራን እንገኛለን።


👉 ሙሉውን ሰነድ ለማንበብ ከታች የተያያዘውን ማሥፈንጠሪያ ይጫኑ 👇

https://drive.google.com/file/d/1prqfUjj2PzXojUVGNCVYyviZ5Qb-lS6Y/view?usp=drivesdk

BY የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)


Share with your friend now:
tgoop.com/ethzema/4687

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Invite up to 200 users from your contacts to join your channel The optimal dimension of the avatar on Telegram is 512px by 512px, and it’s recommended to use PNG format to deliver an unpixelated avatar. The administrator of a telegram group, "Suck Channel," was sentenced to six years and six months in prison for seven counts of incitement yesterday. With the sharp downturn in the crypto market, yelling has become a coping mechanism for many crypto traders. This screaming therapy became popular after the surge of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May or early June. Here, holders made incoherent groaning sounds in late-night Twitter spaces. They also role-played as urine-loving Goblin creatures. Hashtags
from us


Telegram የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
FROM American