tgoop.com/ethio27info/50277
Last Update:
በኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አማካኝነት ከ1.5 ሚልዮን ዶላር በላይ ተሰበሰበ!
ኮመዲያን እሸቱ መለሰ "በሀገረ አሜሪካ ለሚቋቋመው ግዙፍ ስፋት ያለው ገዳም ቦታ መግዣ" ከ 1,500,000 የአሜሪካ ዶላር በላይ በአንድ ቀን መሰብሰብ ችሏል።
ሰሞኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በአሜሪካ ካሊፎርኒያ በመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ ገዳም ሥም ከ1497 ሄክታር በላይ ስፋት ያለው መሬት ልትገዛ እንደሆነ ማስታወቋ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎ ለገዳሙ መግዣ የሚሆነው ቅድመ ክፍያ ገንዘብ ለማሰባሰብ ኮሜዲያን እሸቱ በትናንትናው እለት ባዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ ከ15ሰአት በላይ በላይቭ(live) በመቆየት በአጠቃላይ ከ1.5ሚሊዮን ዶላር በላይ በማሰባሰብ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው የሆነውን ፈጣን የገቢ ማሰባሰብ ስራን አከናዉኗል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የሰሜን ካሊፎርኒያ፣ ኔቫዳ እና አሪዞና ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስም የገቢ ማሰባሰቡን ያካሄዱትን ኮሜዲያን እሸቱን እና የዶንኪ ቲዩብ አባላቶችን ከልብ አመስግነዋል።
በዚህ ሰፊ ይዞታ ላይም የአብነት ትምህርት ቤት፣ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ዘመናዊ ዩኒቨርሲቲ፣ ሆስፒታል እንዲሁም ሌሎች በርካታ ተቋማትን ለማቋቋም እንደታቀደ የገለጹት ሊቀ ጳጳሱ፣ ለቦታው መግዣ የሚሆነውን 8 ሚሊዮን ዶላር ከምዕመናን ለማሰባሰብ እንደታሰበም ተናግረዋል።
Via:- Fidel Post
ለበለጠ መረጃና ጥቆማ በዚህ ላኩልን፡፡
@ethio27info_bot @ethio27info
BY Bekulu Entertainment
Share with your friend now:
tgoop.com/ethio27info/50277