Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tgoop/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/eiasc1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tgoop/post.php on line 50
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council@eiasc1 P.39
EIASC1 Telegram 39
ትኩረት የሚሻው የጉራ ፈርዳው የሰላማዊ ዜጎች ጭፍጨፋ

በቤንች ሸኮ ዞን በጉራ ፈርዳ ወረዳ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት የአያሌ ንፁኃን ሰዎች ህይወት ማለፉን ከተለያየ አካላት ያገኘናቸው መረጃዎች ያመለክታሉ። ባለፉት ሳምንታት መሰል ጥቃቶች በቤኒሻንጉል ክልል የብዙዎችን ህይወት ቀጥፏል።

በጉራ ፈርዳ ወረዳ በአሮጌ ብርሃን፣ ሹጲ እና ዠኒቃ ቀበሌዎች የደረሰው ጥቃት በኋይማኖት አባት (ቓዲ)፣ ወላድ፣ እርጉዝ እና ህፃናት ሳይቀሩ የተጨፈጨፉበት በመሆኑ ጥቃቱን የከፋ ያደርገዋል።

በዚህ ጥቃት ሳቢያ ከቤታቸው ተፈናቅለው ቢፍቱ ወረዳ አካባቢ ለተጠለሉት ወገኖች ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ስንጠይቅ መንግስት በዚህ እኩይ ወንጀል እጃቸው ያለበትን አካላት በአስቸኳይ ለፍርድ በማቅረብ በቦታው መረጋጋት የማስፈን ሚናውን በተገቢው ሁኔታ እንዲወጣ እንዲሁም ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን አስቸኳይ እርዳታ እንዲሰጥ እንጠይቃለን።

በአጠቃላይ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ማንኛውም በንፁኋን ሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚቃጡ ጥቃቶች እያወገዘ የሃገሪቱ ህልውና መሰረት የሆኑትን የአብሮነት፣ መከባበርና እና መተዛዘን እሴቶች መመናመንና የስርአት አልበኝነትና ጭካኔ መበራከት ጉዳዩን የበለጠ አሳሳቢ ያደርገዋል።

በመሰረቱ የሰው ልጅ ህይወት (ዘር፣ ጎሳም ሆነ እምነት ሳይልይ) እጅግ የተከበረ እንደመሆኑና የህዝባችን መገለጫ የሆነውን ሰላማዊነት የመጠበቅ የሁሉም ወገን ኋላፊነት ሆኖ የጋራ ሃገር ግንባታ ያለ ሰላም እና ደህንነት የማይታሰብ እንደሆነ እናምናለን።

የሃይማኖት ተቋማትን ጨምሮ የመንግስት አካላትና ሌሎች የሚመለከታቸው ወገኖች በዚህ ረገድ የበኩላቸውን ኋላፊነት በመወጣት መሰል ጥቃቶች እንዳይከሰቱ የመፍትሄ መንገዶች ላይ መስራት እንዳለባቸው ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በዚህ ረገድ ጠቅላይ ምክር ቤቱ በተለይም የአስተዳደር እና ስራ አመራር ቦርዱ የበኩሉን ሚና ለመወጣት ያለውን ዝግጁነት እየገለፀ የትብብር ጥሪውን ያቀርባል።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት
የስራ አመራር ቦርድ
ጥቅምት 14/ 2013



tgoop.com/eiasc1/39
Create:
Last Update:

ትኩረት የሚሻው የጉራ ፈርዳው የሰላማዊ ዜጎች ጭፍጨፋ

በቤንች ሸኮ ዞን በጉራ ፈርዳ ወረዳ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት የአያሌ ንፁኃን ሰዎች ህይወት ማለፉን ከተለያየ አካላት ያገኘናቸው መረጃዎች ያመለክታሉ። ባለፉት ሳምንታት መሰል ጥቃቶች በቤኒሻንጉል ክልል የብዙዎችን ህይወት ቀጥፏል።

በጉራ ፈርዳ ወረዳ በአሮጌ ብርሃን፣ ሹጲ እና ዠኒቃ ቀበሌዎች የደረሰው ጥቃት በኋይማኖት አባት (ቓዲ)፣ ወላድ፣ እርጉዝ እና ህፃናት ሳይቀሩ የተጨፈጨፉበት በመሆኑ ጥቃቱን የከፋ ያደርገዋል።

በዚህ ጥቃት ሳቢያ ከቤታቸው ተፈናቅለው ቢፍቱ ወረዳ አካባቢ ለተጠለሉት ወገኖች ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ስንጠይቅ መንግስት በዚህ እኩይ ወንጀል እጃቸው ያለበትን አካላት በአስቸኳይ ለፍርድ በማቅረብ በቦታው መረጋጋት የማስፈን ሚናውን በተገቢው ሁኔታ እንዲወጣ እንዲሁም ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን አስቸኳይ እርዳታ እንዲሰጥ እንጠይቃለን።

በአጠቃላይ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ማንኛውም በንፁኋን ሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚቃጡ ጥቃቶች እያወገዘ የሃገሪቱ ህልውና መሰረት የሆኑትን የአብሮነት፣ መከባበርና እና መተዛዘን እሴቶች መመናመንና የስርአት አልበኝነትና ጭካኔ መበራከት ጉዳዩን የበለጠ አሳሳቢ ያደርገዋል።

በመሰረቱ የሰው ልጅ ህይወት (ዘር፣ ጎሳም ሆነ እምነት ሳይልይ) እጅግ የተከበረ እንደመሆኑና የህዝባችን መገለጫ የሆነውን ሰላማዊነት የመጠበቅ የሁሉም ወገን ኋላፊነት ሆኖ የጋራ ሃገር ግንባታ ያለ ሰላም እና ደህንነት የማይታሰብ እንደሆነ እናምናለን።

የሃይማኖት ተቋማትን ጨምሮ የመንግስት አካላትና ሌሎች የሚመለከታቸው ወገኖች በዚህ ረገድ የበኩላቸውን ኋላፊነት በመወጣት መሰል ጥቃቶች እንዳይከሰቱ የመፍትሄ መንገዶች ላይ መስራት እንዳለባቸው ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በዚህ ረገድ ጠቅላይ ምክር ቤቱ በተለይም የአስተዳደር እና ስራ አመራር ቦርዱ የበኩሉን ሚና ለመወጣት ያለውን ዝግጁነት እየገለፀ የትብብር ጥሪውን ያቀርባል።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት
የስራ አመራር ቦርድ
ጥቅምት 14/ 2013

BY Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council


Share with your friend now:
tgoop.com/eiasc1/39

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Matt Hussey, editorial director at NEAR Protocol also responded to this news with “#meIRL”. Just as you search “Bear Market Screaming” in Telegram, you will see a Pepe frog yelling as the group’s featured image. Hashtags are a fast way to find the correct information on social media. To put your content out there, be sure to add hashtags to each post. We have two intelligent tips to give you: Concise Choose quality over quantity. Remember that one high-quality post is better than five short publications of questionable value. Select: Settings – Manage Channel – Administrators – Add administrator. From your list of subscribers, select the correct user. A new window will appear on the screen. Check the rights you’re willing to give to your administrator.
from us


Telegram Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
FROM American