DRAW_DRAW_DRAW Telegram 3462
😂አሳዬና ኮሮና ምንና ምን ናቸው?

«በዘውድአለም ታደሠ»


ለውጡ ከመጣ በኋላ ግራ እያጋባኝ ያለው የባልንጀራዬ አሳዬ
ደርቤ ጉዳይ ነው። በአጭር ግዜ ፀጉሩ ሸሽቶ ሸሽቶ ዳርፉር ሊደርስ
ነው። አናቱ ላይ የቀሩት ለነፍሳቸው ያደሩ ሶስት ፀጉሮች ናቸው።
ፖለቲከኛ ከሆነ ወዲህ «ለዚች ሐገር ስል ተመለጥኩ» ይላል አሉ
ትናንት ቤቱ ስሄድ ሶስት ፌስ ማስክ ደራርቦ አድርጎ በላዩ ላይ ጋቢ
ተከናንቦ ሊታከም የሚሄድ ብርድ በሽተኛ ይመስላል። ወደቤቱ
ልገባ ስል ተንደርድሮ መጥቶ በሁለት ሜትር ርቀት አቆመኝና
ሙቀቴን በአይኑ ለመለካት ከሞከረ በኋላ «ሳይህ ኮሮና የያዘህ
አትመስልም ግባ» አለኝ። ጥንቃቄው እየገረመኝ ወደቤቱ ስገባ
ልጆቹን ሳፋ ውስጥ በሳኒታይዘር ዘፍዝፏቸዋል
ገብቼ ሶፋው ላይ ስቀመጥ ሜትር አምጥቶ በጥንቃቄ ለካና
በሁለት ሜትር ርቀት በጥንቃቄ ተቀመጠ። ፍልቅልቋ ባለቤቱ
ከጓዳ መጣችና (ያው የኔ ነገር አይሆንላትም)
«ውይ ዜድዬ መጣህ እንዴ?» ብላ ልትጨብጠኝ ስትጠጋኝ
እንደተቀመጠ ሁለት ሜትር ዘሎ ተጠመጠመባት። ቀልቧ
የተገፈፈው ሚስቱ «ምን ሆነሃል አንተ ሰውዬ?» ስትለው
«በበሽታ ልትጨርሺን ነው እንዴ ሴትዮ የምን ሰላምታ ነው በዚህ
በከፋ ዘመን?» ብሎ እየተንቀተቀጠ ጮኸባት።
የጓደኛዬ አሳዬ ሁኔታ ምንም የጤና አልመሰለኝም። ኮሮና አስም
ያለበትን ሰው የበለጠ ይጎዳል የሚል ወሬ ከሰማ ወዲህ ለሽንት
ራሱ ከክፍሉ አይወጣም። የሆነ በሽታው እሱን ፈልጎ ኢትዮጵያ
የመጣ ነው ያስመሰለው። በዚያ ላይ በሽታውን ይከላከላል የተባለ
ነገር ሁሉ ይሞክራል። እስፖርት ጥሩ ነው ሲባል ከሰማ እዚያው
ሳሎኑ ውስጥ እስፖርት ይሰራል። ሚስቱ እንደነገረቺኝ ከሆነ
ባለፈው ገመድ እዘላለሁ ብሎ በዚያ ቁመቱ ሲዘል የገዛ ገመዱ
ጠልፎት ወድቆ የልጆቹ አምላክ ነው ያተረፈው።
ገዳም ያሉ ሰዎች ፌጦ ነጭ ሽንኩርትና ዚንጅብል በሽታውን
ይከላከላል ብለዋል የሚል ወሬ ሲሰማ አንድ ኪሎ ፌጦ በሁለት
እንጀራ በልቶ የሰውነቱ ሙቀት 45 ዲግሪ ደርሶ ነበር። መከረኛ
ሚስቱ በረዶ ውስጥ ዘፍዝፋው ነው ከሞት የተረፈው። ያም ሆኖ
አልተማረም። መድሃኒት ነው የተባለውን ሁሉ ይበላል። እስካሁን
ያልበላው ያለም ዋንጫ ብቻ ነው። አሁን ደሞ የደምበጫ አረቄ
ጥሩ ነው ብለውት በየቀኑ አንድ ጠርሙስ አረቄ ጨርሶ ያድራል
አሉ። ባለቤቱ እንደነገረቺኝ ከሆነ ተኮራምቶ አረቄውን ይጀምርና
ሞቅ እያለው ሲመጣ ጋቢውንና ፌስ ማስኩን ያወልቃል። ቀን
ሙሉ ሳኒታይዘር ውስጥ የሚዘፈዝፋቸውን መከረኛ ልጆቹንም ከሳፋ
ውስጥ ያወጣል። ወደመስከሩ ሲጠጋ ደግሞ
«ይሁን ብለን ነው እንጂ እንኳን ለኮሮና ለጣሊያንም
አልተንበረከክንም» ብሎ እየፎከረ ከቤት ይወጣና ያገኘውን ሁሉ
ወልዶ እንዳሳደገ ሰው አገላብጦ እየሳመ ዞሮ ዞሮ ይመለሳል
አለችኝ።😂😂



tgoop.com/draw_draw_draw/3462
Create:
Last Update:

😂አሳዬና ኮሮና ምንና ምን ናቸው?

«በዘውድአለም ታደሠ»


ለውጡ ከመጣ በኋላ ግራ እያጋባኝ ያለው የባልንጀራዬ አሳዬ
ደርቤ ጉዳይ ነው። በአጭር ግዜ ፀጉሩ ሸሽቶ ሸሽቶ ዳርፉር ሊደርስ
ነው። አናቱ ላይ የቀሩት ለነፍሳቸው ያደሩ ሶስት ፀጉሮች ናቸው።
ፖለቲከኛ ከሆነ ወዲህ «ለዚች ሐገር ስል ተመለጥኩ» ይላል አሉ
ትናንት ቤቱ ስሄድ ሶስት ፌስ ማስክ ደራርቦ አድርጎ በላዩ ላይ ጋቢ
ተከናንቦ ሊታከም የሚሄድ ብርድ በሽተኛ ይመስላል። ወደቤቱ
ልገባ ስል ተንደርድሮ መጥቶ በሁለት ሜትር ርቀት አቆመኝና
ሙቀቴን በአይኑ ለመለካት ከሞከረ በኋላ «ሳይህ ኮሮና የያዘህ
አትመስልም ግባ» አለኝ። ጥንቃቄው እየገረመኝ ወደቤቱ ስገባ
ልጆቹን ሳፋ ውስጥ በሳኒታይዘር ዘፍዝፏቸዋል
ገብቼ ሶፋው ላይ ስቀመጥ ሜትር አምጥቶ በጥንቃቄ ለካና
በሁለት ሜትር ርቀት በጥንቃቄ ተቀመጠ። ፍልቅልቋ ባለቤቱ
ከጓዳ መጣችና (ያው የኔ ነገር አይሆንላትም)
«ውይ ዜድዬ መጣህ እንዴ?» ብላ ልትጨብጠኝ ስትጠጋኝ
እንደተቀመጠ ሁለት ሜትር ዘሎ ተጠመጠመባት። ቀልቧ
የተገፈፈው ሚስቱ «ምን ሆነሃል አንተ ሰውዬ?» ስትለው
«በበሽታ ልትጨርሺን ነው እንዴ ሴትዮ የምን ሰላምታ ነው በዚህ
በከፋ ዘመን?» ብሎ እየተንቀተቀጠ ጮኸባት።
የጓደኛዬ አሳዬ ሁኔታ ምንም የጤና አልመሰለኝም። ኮሮና አስም
ያለበትን ሰው የበለጠ ይጎዳል የሚል ወሬ ከሰማ ወዲህ ለሽንት
ራሱ ከክፍሉ አይወጣም። የሆነ በሽታው እሱን ፈልጎ ኢትዮጵያ
የመጣ ነው ያስመሰለው። በዚያ ላይ በሽታውን ይከላከላል የተባለ
ነገር ሁሉ ይሞክራል። እስፖርት ጥሩ ነው ሲባል ከሰማ እዚያው
ሳሎኑ ውስጥ እስፖርት ይሰራል። ሚስቱ እንደነገረቺኝ ከሆነ
ባለፈው ገመድ እዘላለሁ ብሎ በዚያ ቁመቱ ሲዘል የገዛ ገመዱ
ጠልፎት ወድቆ የልጆቹ አምላክ ነው ያተረፈው።
ገዳም ያሉ ሰዎች ፌጦ ነጭ ሽንኩርትና ዚንጅብል በሽታውን
ይከላከላል ብለዋል የሚል ወሬ ሲሰማ አንድ ኪሎ ፌጦ በሁለት
እንጀራ በልቶ የሰውነቱ ሙቀት 45 ዲግሪ ደርሶ ነበር። መከረኛ
ሚስቱ በረዶ ውስጥ ዘፍዝፋው ነው ከሞት የተረፈው። ያም ሆኖ
አልተማረም። መድሃኒት ነው የተባለውን ሁሉ ይበላል። እስካሁን
ያልበላው ያለም ዋንጫ ብቻ ነው። አሁን ደሞ የደምበጫ አረቄ
ጥሩ ነው ብለውት በየቀኑ አንድ ጠርሙስ አረቄ ጨርሶ ያድራል
አሉ። ባለቤቱ እንደነገረቺኝ ከሆነ ተኮራምቶ አረቄውን ይጀምርና
ሞቅ እያለው ሲመጣ ጋቢውንና ፌስ ማስኩን ያወልቃል። ቀን
ሙሉ ሳኒታይዘር ውስጥ የሚዘፈዝፋቸውን መከረኛ ልጆቹንም ከሳፋ
ውስጥ ያወጣል። ወደመስከሩ ሲጠጋ ደግሞ
«ይሁን ብለን ነው እንጂ እንኳን ለኮሮና ለጣሊያንም
አልተንበረከክንም» ብሎ እየፎከረ ከቤት ይወጣና ያገኘውን ሁሉ
ወልዶ እንዳሳደገ ሰው አገላብጦ እየሳመ ዞሮ ዞሮ ይመለሳል
አለችኝ።😂😂

BY ሥዕል እንደሙዴ


Share with your friend now:
tgoop.com/draw_draw_draw/3462

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

Click “Save” ; On Tuesday, some local media outlets included Sing Tao Daily cited sources as saying the Hong Kong government was considering restricting access to Telegram. Privacy Commissioner for Personal Data Ada Chung told to the Legislative Council on Monday that government officials, police and lawmakers remain the targets of “doxxing” despite a privacy law amendment last year that criminalised the malicious disclosure of personal information. As five out of seven counts were serious, Hui sentenced Ng to six years and six months in jail. Hashtags are a fast way to find the correct information on social media. To put your content out there, be sure to add hashtags to each post. We have two intelligent tips to give you: Telegram channels fall into two types:
from us


Telegram ሥዕል እንደሙዴ
FROM American