DMTSE_TEWAEDO Telegram 5154
                         †                         

[    የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት     ]

             [    ደብረ ዘይት   ]

ሊፈርድ የሚመጣውን ዳኛ - አማላጅ አትበል !

- በዓለ ደብረ ዘይት በሰቂለ ሕሊና በተመስጦ ልቡና የሚከበር ታላቅ በዓለ እግዚእ ነው። በግርማ መለኮት በክበበ ትስብእት ይመጣል። የሚመጣውም ሊፈርድ ነው። ያማልዳል የምትል ሁሉ መጽሐፍኽን ፈልግ።

----------------------------------------------

ቅዱስ ዳዊት ይመጣል ያለን እግዚአብሔርን ነው። "ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ኾኖ ይመጣል" እንዲል። [መዝ ፵፱፡፪]

ደግሞም "ይመጣልና በምድር ላይ ሊፈርድ ይመጣል ፤ እርሱም ዓለምን በጽድቅ አሕዛብንም በቅንነት ይፈርዳል" ይላል። [መዝ ፺፭፡ ፲፫]

ሲሠልስም  "ወንዞች በአንድነት በእጅ ያጨብጭቡ፣ ተራሮች ደስ ይበላቸው፤ በምድር ሊፈርድ ይመጣልና" ብሏል። [መዝ ፺፯፡ ፰]

ነቢየ ልዑል ኢሳይያስም "እነሆ እግዚአብሔር መዓቱን በቁጣ ዘለፋውንም በእሳት ነበልባል ይመልስ ዘንድ ከእሳት ጋር ይመጣል፤ ሠረገሎቹም እንደ ዐውሎ ነፋስ ይኾናሉ" ሲል ተናግሯል። [ኢሳ ፷፮፡ ፲፭]

ቅዱሳን መላእክትም "ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ [ክርስቶስ] ወደ ሰማይ ሲሔድ እንዳያችሁት እንዲሁ ይመጣል እሏቸው" ተብሎ ተጽፏል። [ሥራ ፩፡ ፲፩]

የመጀመሪያው መጽሐፍ ጸሐፊ ነቢዩ ሔኖክም "እነሆ ጌታ በሁሉ ላይ እንዲፈርድ . . . ከአእላፋት ቅዱሳኑ ጋር መጥቷል" በማለት ተናግሯል። [ሔኖ ፩፡ ] ሐዋርያው ይሁዳም አጽንቶታል። ይሁዳ ቁ ፲፬።

ከሁሉም በላይ የራሱ የጌታችን ምስክርነት ወደር አይገኝለትም።

"ከዚያች ወራትም መከራ በኋላ ወዲያው ፀሐይ ይጨልማል፥ ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም፥ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፥የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል፥ በዚያን ጊዜም የምድር ወገኖች ሁሉ ዋይ ዋይ ይላሉ፥ የሰው ልጅንም በኃይልና በብዙ ክብር በሰማይ ደመና ሲመጣ ያዩታል፤  መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከዐራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ" በማለት በማያወላዳ ቃል ነግሮናል። ማቴ ፳፬፡ ፳፱-፴፩፡፡

"የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፥ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል፤ አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለይ እርስ በርሳቸው ይለያቸዋል፥ በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል። የንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። . . .
በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘለዓለም እሳት ከእኔ ሒዱ" ይላቸዋል። ማቴ ፳፭፡ ፴፩-፵፩።

ይህንን ጌታ አማላጅ እያልህ መጠበቁ በየት እንደሚያቆምህ ዐውቀኽ ከአሁኑ ተመለስ።

እንኳን ለበዓለ ደብረ ዘይት አደረሳችሁ !

[  ዲ/ን ዓባይነህ ካሤ  ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
https://www.tgoop.com/dmse_tewado



tgoop.com/dmtse_tewaedo/5154
Create:
Last Update:

                         †                         

[    የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት     ]

             [    ደብረ ዘይት   ]

ሊፈርድ የሚመጣውን ዳኛ - አማላጅ አትበል !

- በዓለ ደብረ ዘይት በሰቂለ ሕሊና በተመስጦ ልቡና የሚከበር ታላቅ በዓለ እግዚእ ነው። በግርማ መለኮት በክበበ ትስብእት ይመጣል። የሚመጣውም ሊፈርድ ነው። ያማልዳል የምትል ሁሉ መጽሐፍኽን ፈልግ።

----------------------------------------------

ቅዱስ ዳዊት ይመጣል ያለን እግዚአብሔርን ነው። "ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ኾኖ ይመጣል" እንዲል። [መዝ ፵፱፡፪]

ደግሞም "ይመጣልና በምድር ላይ ሊፈርድ ይመጣል ፤ እርሱም ዓለምን በጽድቅ አሕዛብንም በቅንነት ይፈርዳል" ይላል። [መዝ ፺፭፡ ፲፫]

ሲሠልስም  "ወንዞች በአንድነት በእጅ ያጨብጭቡ፣ ተራሮች ደስ ይበላቸው፤ በምድር ሊፈርድ ይመጣልና" ብሏል። [መዝ ፺፯፡ ፰]

ነቢየ ልዑል ኢሳይያስም "እነሆ እግዚአብሔር መዓቱን በቁጣ ዘለፋውንም በእሳት ነበልባል ይመልስ ዘንድ ከእሳት ጋር ይመጣል፤ ሠረገሎቹም እንደ ዐውሎ ነፋስ ይኾናሉ" ሲል ተናግሯል። [ኢሳ ፷፮፡ ፲፭]

ቅዱሳን መላእክትም "ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ [ክርስቶስ] ወደ ሰማይ ሲሔድ እንዳያችሁት እንዲሁ ይመጣል እሏቸው" ተብሎ ተጽፏል። [ሥራ ፩፡ ፲፩]

የመጀመሪያው መጽሐፍ ጸሐፊ ነቢዩ ሔኖክም "እነሆ ጌታ በሁሉ ላይ እንዲፈርድ . . . ከአእላፋት ቅዱሳኑ ጋር መጥቷል" በማለት ተናግሯል። [ሔኖ ፩፡ ] ሐዋርያው ይሁዳም አጽንቶታል። ይሁዳ ቁ ፲፬።

ከሁሉም በላይ የራሱ የጌታችን ምስክርነት ወደር አይገኝለትም።

"ከዚያች ወራትም መከራ በኋላ ወዲያው ፀሐይ ይጨልማል፥ ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም፥ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፥የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል፥ በዚያን ጊዜም የምድር ወገኖች ሁሉ ዋይ ዋይ ይላሉ፥ የሰው ልጅንም በኃይልና በብዙ ክብር በሰማይ ደመና ሲመጣ ያዩታል፤  መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከዐራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ" በማለት በማያወላዳ ቃል ነግሮናል። ማቴ ፳፬፡ ፳፱-፴፩፡፡

"የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፥ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል፤ አሕዛብም ሁሉ በፊቱ ይሰበሰባሉ፤ እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለይ እርስ በርሳቸው ይለያቸዋል፥ በጎችን በቀኙ ፍየሎችንም በግራው ያቆማቸዋል። የንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። . . .
በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘለዓለም እሳት ከእኔ ሒዱ" ይላቸዋል። ማቴ ፳፭፡ ፴፩-፵፩።

ይህንን ጌታ አማላጅ እያልህ መጠበቁ በየት እንደሚያቆምህ ዐውቀኽ ከአሁኑ ተመለስ።

እንኳን ለበዓለ ደብረ ዘይት አደረሳችሁ !

[  ዲ/ን ዓባይነህ ካሤ  ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
https://www.tgoop.com/dmse_tewado

BY 🎤ድምፀ ተዋህዶ🎤


Share with your friend now:
tgoop.com/dmtse_tewaedo/5154

View MORE
Open in Telegram


Telegram News

Date: |

With the sharp downturn in the crypto market, yelling has become a coping mechanism for many crypto traders. This screaming therapy became popular after the surge of Goblintown Ethereum NFTs at the end of May or early June. Here, holders made incoherent groaning sounds in late-night Twitter spaces. They also role-played as urine-loving Goblin creatures. With the administration mulling over limiting access to doxxing groups, a prominent Telegram doxxing group apparently went on a "revenge spree." The Standard Channel Read now It’s easy to create a Telegram channel via desktop app or mobile app (for Android and iOS):
from us


Telegram 🎤ድምፀ ተዋህዶ🎤
FROM American