tgoop.com/amennnnnnnnnnnnnnnnnnnn/8124
Last Update:
በዚህ ዓለም ሕግ ኹለት ተወዳዳሪ አካላት [ለምሳሌ የእግር ኳስ ተጫዋቾች] በስታዲየም ውስጥ ለመገናኘት ቀጠሮ ቢይዙ የየራሳቸው ደጋፊዎች አሉአቸው፡፡ ደጋፊዎቻቸው አብረው እየዘፈኑና እየፎከሩ ተወዳዳሪዎቹን እያበረታቱና እያሞገሱ፣ ተጋጣሚውንም እየተቃወሙ ወደ ስታዲዮሙ ይኼዳሉ፡፡ ስታዲዮሙ ውስጥ ሲገቡና ውድድሩ ሲጀምርም እስከ ውድድሩ ፍጻሜ ይህን ያደርጋሉ፡፡ ደጋፊዎቹ ይህን ቢያደርጉም ቅሉ ወደ ውድድር ሜዳው ወርደው ግን የተወዳዳሪዎቹን እግር ወይም እጅ ይዘው ማገዝ አይችሉም፡፡ የተቃራኒውንም ቡድን እግር ማደናቀፍና ወደ ኋላ መጎተት አይችሉም፤ አይፈቀድላቸውም፡፡
ደጋፊው እንዲህ ማድረግስ ይቅርና “በእንደዚህ ዓይነት ስልት ተጫወቱ” ማለትም አይችልም፡፡ “በእንደዚህ ዓይነት ስልት ተጫወቱ” ማለት የሚችለው አሠልጣኙ ራሱ ከመጫወቻ ሜዳ ውጭና በተሰጠው ቦታ ኾኖ ይህን ማለት ቢችልም ቅሉ ወደ ሜዳው ገብቶ ማገዝ አይችልም፡፡
በእኛ በክርስቲያኖች ዘንድ ግን እንደዚህ አይደለም፡፡ እኛ በዚህ ዓለም ከአጋንንትና ከጭፍሮቹ ጋር በምንጋደልበት ጊዜ እኛን የሚረዱን አባቶቻችንና እናቶቻችን መላእክትም አሉን፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ረዳቶቻችን ግን ከሩቅ ኾነው ቆመው የሚያዩን ሳይኾኑ ወደ ውጊያ ሥፍራው አብረውን የሚገቡ ናቸው፡፡ በአጠገባችን ኾነው ተጋጣሚያችንን ድል እንድናደርግ የሚያግዙን ናቸው፡፡ እነዚህ ረዳቶቻችንና ደጋፊዎቻችን ብቻ ሳይኾኑ ዋናው አሠልጣኝ (እግዚአብሔርም) ተጋጣሚያችንን በምን ዘዴ ድል መንሣት እንዳለብን ይነግረን ዘንድ በውጊያ ሥፍራው ዘወትር አብሮን ይኾናል፡፡ …
እንኪያስ ይህን ተገንዝበን ድል እናደርግ ዘንድ እንበርታ!
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - አምስቱ የንስሐ መንገዶች ገጽ 31-32)
BY አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር

Share with your friend now:
tgoop.com/amennnnnnnnnnnnnnnnnnnn/8124
