tgoop.com/amennnnnnnnnnnnnnnnnnnn/7673
Create:
Last Update:
Last Update:
#ንስሐ_እግዚአብሔር_ወደ_ሰው_የሚጠራውን_ጥሪ_ሰምቶ_ወደ_እርሱ_መመለስ_ነው!
ይህ በኅሊና ውስጥ ለሚደመጠው የ #እግዚአብሔር የጥሪ ድምፅ መልስ መስጠት ነው። የተቀደሰውን የ #መንፈስ_ቅዱስ ሥራ አለመቃወም የ #እግዚአብሔርን ጥሪ መስማት ነው። ልብን ማደንደንና የ #እግዚአብሔርን ቃል አለመቀበል የተቀደሰውን የ #መንፈስ_ቅዱስ ሥራ መቃወም ነው። የሐየ.7÷51። የ #እግዚአብሔርን መንፈስ አለማሳዘን የ #እግዚአብሔርን ጥሪ መስማት ነው። ኤፌ.4÷30። በአርባ (፵) እና በሰማንያ (፹) ቀን ስንጠመቅና የ #ሥላሴን ልጅነትን ስናገኝ የተቀበልነውን በውስጣችን የታተመውን #መንፈስ_ቅዱስ ከውስጣችን አለማጥፋትና የሚፃረረውን ኃጢያት ከመሥራት መጠበቅ የ #እግዚአብሔርን የጥሪ ድምፅ መስማት ነው። 1ኛተሰ.5÷19
#ይቀጥላል....
BY አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር
Share with your friend now:
tgoop.com/amennnnnnnnnnnnnnnnnnnn/7673