tgoop.com/amenelectricaltechnology/2898
Last Update:
✅#በሀገራችን_ኢትዮጵያ_የመጀመሪያ_የሆነው_የኤሌክትሪካል_ኢቨንት_በድምቀት_ተከበረ❗️
=====
👉አሜን ኤሌክትሪካል ቴክኖሎጂ ከዩኤፍ ኬብልና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪካል መሀንዲሶች ማህበር ጋር በመተባበር የተዘጋጀውና በሀገራችን የመጀመሪያ የሆነው የኤሌክትሪካል ኢቨንት በደማቅ ሁኔታ ግንቦት 10/2017 ዓ.ም በኤግዚቪሽን ማዕከል ተከበረ።
ኢቨንቱም ኤሌክትሪክ ሥራ ተቋራጮችን፣አማካሪዎችን፣ ኤሌክትሪክ ባለሙያዎችን ከኤሌክትሪካል ኢንደስትሪው ጋር በማገናኘት ፣ የንግድ ሽርክናዎችን፣ የሥራ እድሎችን፣ የእውቀትና የልምድ ልውውጥን በመፍጠር ዘርፉን ለማሳደግ ያለመ ነበር ፡፡
በዕለቱም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኤሌክትሪካል ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ኢንጅነር ፋሲካ ጌቱ(የአሜን ኤሌክትሪካል ቴክኖሎጂ መስራች) ለዚህ ታላቅ ኢቨንት መሳከት ከፍተኛውን ድርሻ የተወጣውን ዩኤፍ ኬብልን፣ በዕለቱ ተሳታፊ የነበሩትን የክብር እንግዶችንና የኤሌክትሪክ ባለሙያውን በማመስገን ፕሮግራሙን አስጀምረዋል!
በመልክታቸውም "የኤሌክትሪክ ዘርፉ ታሟል መታከም ይፈልጋል!" ያሉ ሲሆን "ይህ የሆነበት ትልቁ ምክንያትም እንደዚህ ያሉ መድረኮች በሀገራችን ስላልተለመደ ነው" ብለዋል። አይይዘውም "በሌላው አለም እንደነዚህ አይነት መድረኮች የተለመዱ ሲሆን አምራቹን ከባለሙያው/ከተጠቃሚው ጋር ለማገናኘትና ዘርፉን ለማሳደግ አይነተኛ መፍትሄ ናቸው" ብለዋል።
በመቀጠልም ዩኤፍ ኬብል ስለሚያመርታቸው ጥራት ያላቸው የኤሌክትሪክ ዋየሮች ማብራሪያዎችን በኢንጅነር አብርሃም ሀይሉ አማካኝነት ካቀረበ በኋላ ኢንጅነር ፋሲካ ጌቱ ዘርፉን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ዘርፍ ችግሮችና መፍትሄዎች/Ethiopia's Electrical Sector Crisis and Strategic Solutions በሚል አርዕስት ፅሑፎችን ካቀረቡ በኋላ በዚህ ዙሪያ ውይይቶች ተደርገው የጥዋቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።
በከሰዓቱ ፕሮግራም ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪካል መሀንዲሶች ማህበር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ያደረገ ሲሆን በኢንጅነር ሰማኸኝ ሽታየ አማካኝነት በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ዙሪያ ጥናታዊ ፅሑፍ ካቀረቡ በኋላ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪካል መሀንዲሶች ማህበር ለዚህ ኢቨምትና ለዘርፉ ላደረጉት አስተዋፅዖ ለዩኤፍ ኬብል፣ ለአሜን ኤሌክትሪካል ቴክኖሎጂና ለኢንጅነር ሰማኸኝ ሽታየ የምስክር ወረቀት አበርክቷል።
BY Amen Electrical Technology Official®
Share with your friend now:
tgoop.com/amenelectricaltechnology/2898